Search

Wednesday, May 29, 2013

ኢትዮጵያዊቷ ወጣት በአትላንታ 25 ዓመት እስር ተፈረደባት

ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ሮዳስ ተክሉ እዚህ አትላንታ ከተማ በዋለው የወንጀል ጉዳዮች ችሎት ቀርባ ጉዳይዋ ሲታይ ከቆየ በኋላ ባለፍው ሰኞ MAY 20/2013 ….. 25 ዓመት እስር ተፈረደባት። ሮዳስ ተክሉ ይህ የተፈረደባት የሰው ነፍስ በማጥፋቷ ወንጀሉንም መፈጸሟን በማመኗ ነው።
የኋላ ታሪኩ እንዲህ ነው። ፌብሩዋሪ 5 ቀን 2009 አመሻሽ ላይ በአትላንታ የተፈጸመው ወንጀል መላው የአትላንታ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን በቅርብ፣ ነገሩን የሰሙና በሌሎች ከተሞች ያሉትን ደግሞ በሩቅ ያስደነገጠ ነበር። 3754 ቢፈርድ ሃይዌይ የሚባለው የአትላንታ መንገድ ላይ የጸጉር መከርከሚያ ሱቅ ከፍቶ በመስራት ላይ የነበረው ኤርሚያስ አወቀ ፣ ማምሻውን ጭምር አምሽቶ እየሰራ ነበር። ከምሽቱ 8 ፒ ኤም አካባቢ ሮዳስ ተክሉ ሱቁ ድረስ መጣች።
የፖሊስ ሪፖርት እንደሚያሳየው ሮዳስ ሱቁ ድረስ ከመጣች በኋላ ጭቅጭቅ ተጀመረ። እሱ እንድትወጣለት ቢጠይቃትም አልወጣችም። ይልቁኑ በእጇ ሽጉጥ ይዛ ስለነበር ፣ ስልኩን አንስቶ 911 ደወለ፣ ስልኩን ላነሳችው ኦፕሬተር “አንዲት ሴት ሱቄ ድረስ መጥታ ልትገለኝ እያስፈራራችኝ ነው፣ መሳሪያ ይዛለች .. እያለ ገና ተናግሮ ሳይጨርስ ስልኩ ተቋረጠ። ከዚያ በኋላ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች የጥይት ድምጽ መስማታቸውን ይናገራሉ።
ፖሊስ ካለበት፣ ነገሩን የሰሙም በጸጉር ቤቱ አካባቢ ሲደርሱ ኤርሚያስ በደም ተነክሮ ወድቋል፣ ወዲያው ወደ ሆስፒታል ተወሰደ ፣ ሆስፒታል ሲደርስም ህይወቱ አለፈ። በወቅቱ አንዲት ሴት ከቤቱ ወጥታ ስትሄድ አይተናል ከሚል ጥቆማ ውጪ ማን ገደለው የሚለው ጥያቄ እንቆቅልሽ ሆነ።
በማግስቱ ፌብሩዋሪ 6 ግን ፖሊስ ሮዳስ ተክሉ የተባለችና የቀድሞ ፍቅረኛው ነች የተባለች ሴት በጥርጣሬ መያዙን አስታወቀ። እሷም ወደ እስር ቤት ተወሰደች። ኤርሚያስም የፖሊስ ምርመራ ከታወቀና ዶክተሮች የሞቱን መንስኤ ካስታወቁ በኋላ ፌብሩዋሪ 11 ቀን በርካታ የአትላንታ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በጸጉር ቤቱ ደጃፍ የሻማ ማብራት ሰነ ስር ዓት ተካሄደ፣ በማግስቱ ፌብሩዋሪ 12 ጸሎተ ፍትሃት ከተደረገለት በኋላ አገር ቤት ተወስዶ እንዲቀበር በተያዘለት ፕሮግራም ይሄዳል ሲባል ፣ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ ያስፈልገኛል በማለቱ እስከ ፌብሩዋሪ 24 ሳይላክ ቆየ። ፌብሩዋሪ 24 ቀን ግን አስክሬኑ ወደ አገር ቤት ለቀብር ተላከ።
ከዚያ በኋላ ዜናው በአድማስ ሬዲዮም ሆነ አትላንታ ባለው ድንቅ መጽሔት ከወጣ በኋላ በወቅቱ የወጣት ሮዳስ ተክሉ ቤተሰቦች “እሷ በግድያው የለችበትም፣ ይህንን ድርጊት እሷ ትፈጽማለች ብሎ ማሰብ ትክክል አይደለም” ሲሉ ተናግረው ነበር። ሆነም ቀረ ላለፉት አራት ዓመታት ነገሩ ከፍርድ ቤት እስር ቤት ፣ ከ እስር ቤት ፍርድ ቤት ሲንከባለል ቆየ፣ የ ኤርሚያስ አወቀ የቅርብ ቤተሰብ የሆኑት አቶ ላቀው ለአድማስ ሬዲዮ እንደገለጹት በመካከል ተጠርጣሪዋ ልጅ፣ በጠበቆቿ አማካኝነት “አእምሮዋ ትክክል አይደለምና ለፍርድ ልትቀርብ አይገባም” ብለው ሲከራከሩ የቆዩ ሲሆን፣ ዳኞቹም የ አ ዕምሮዋ ነገር በሃኪሞች እንዲታይ ፈቅደው ቆይተዋል። በኋላ ግን ችሎት መቆም እንደምትችል በመታመኑ ፣ ጉዳዩ በከሳሽ አቃቤ ህግ እና በተከሳሽ ሮዳስ ተክሉ ጠበቆች መካከል ክርክሩ ቀጥሎ አራት ዓመት ከፈጀ። እንደ አቶ ላቀው ገለጻ ፣ በመጨረሻ ላይ ሮዳስ ወንጀሉን መፈጸሟን እንድታምን ተጠይቃ “አዎ ፈጽሜያለሁ፣ ነገር ግን በደም ፍላትና ሳላስበው ያደረኩት ነው” ስትል በማመኗ ዳኛዋ 25 ዓመት ጽኑ እስራት ፈርደውባታል። ምናልባት ጥፋቷን ባታምን እና ነገሩ በክርክሩ ብትሸነፍ የሞት ፍርድ ሊጠብቃት ይችልም ነበር ብለዋል።
ዳኛዋ በፍርድ ውሳኔያቸው እንደገለጹት “ ኤርሚያስ ገበየሁን በ 10 ጥይት መግደል ሳይታሰብ፣ ባጋጣሚ የተደረገ አይደለም” ሲሉ ውሳኔያቸውን አጽንተዋል።
በተያያዘ ሁኔታ ሮዳስ ተክሉ እዚያው እስር ቤት እያለች አንዲት ሴት ልጅ መውለዷም ታውቋል። የወለደችው ግሬዲ ሆስፒታል በፖሊስ ታጅባ ሄዳ ሲሆን፣ ባሁኑ ሰአት ህጻኗን አንዲት ነርስ እዚያው ግሬዲ እያሳደገቻት መሆኑ ሲታወቅ፣ የህጻኗን አባት በተመለከተ ዳኛዋ “የቀረበልኝ የዲ ኤን ኤ ምርመራ ስለሌለ፣ በልጅቷ አባት ጉዳይ የምሰጠው አስተያየት የለም” ሲሉ መናገራቸውም ታውቋል። (ምንጭ አድማስ ሬዲዮ አትላንታ)

Racist Videos - The Funny Networks _ The Funny Networks


Tuesday, May 28, 2013

ኢትዮጵያ 290 ሚሊዮን ብር ያወጣችበትን ግዙፍ የስፖርት ማዕከል አስገንብታ ዛሬ አስመርቃለች::

የኢትዮጵያ ሁለገብ የወጣቶች  ስፖርት አካዳሚ ዛሬ  በይፋ ተመረቀ።
አካዳሚውን በይፋ የመረቁት ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እንዳሉት ፥ የሀገራችን ስፖርት ቀደም ሲል በአብዛኛው በግል ጥረትና ተነሳሽነት እንዲሁም በልምድ በመታገዝ ውጤት እንዲመዘገብ ረድቷል ።
ይሁንና ስፖርቱ ከሚጠይቀው ጥልቅና ሳይንሳዊ መሰረት ካለው አሰለጣጠን አንጻር የማሰልጠኛ ማእከሉ መከፈት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያመለከቱት።
አቶ ሀይለማርያም በንግግራቸው  የስፖርት ልማት የሰው ሀብት ልማታችን ዋናው አካል ሲሆን ፥ የአገሪቱ የስፖርት እድገትን የሚለካውም በአለም አቀፍ የስፖርት መድረክ በሚመዘገብ ውጤት ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ህብረተሰቡ ስፖርትን ለአካልና ለአእምሮ ጤንነት ማረጋገጫነት በስፋት ሲጠቀምበት ነው ብለዋል።
ከስድስት ዓመት በፊት ግንባታው የተጀመረው ይህ አካዳሚው ከ290 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል ተብሏል።
አካዳሚው በውስጡ ስታዲየም ፣ ጂምናዚየም ፣ የመማሪና የመኝታ ክፍሎች ፣አለም አቀፍ ደረጃን ያሟላ የመዋኛ ገንዳ  ያሟላ ሲሆን ፥ ለአገሪቱ የስፖርት እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል ።
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችም አካዳሚውን ጎብኝተዋል ።

ከረሃብ ለመዳን ጥንዚዛና ምስጥ፣ አንበጣና ጉንዳን ብሉ UN: Eat more insects to fight hunger

ተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ዩኤን) ባለፈው ሳምንት ከሮም ከተማ ለአለማችን ረሃብተኞች አንድ ምክርና የምስራች ወሬ አሰራጭቷል። የምስራች ወሬው፣ “እነ ጥንዚዛን በመመገብ ከረሃብ መገላገል ይቻላል” የሚል ነው። በደግነት የለገሰን ምክር ደግሞ፣ ከረሃብ ለመዳን “ነፍሳትን ብሉ” ይላል። ዩኤን ይህን “ምክርና የምስራች” በይፋ ለመላው አለም ያበሰረው፣ የአለም ምግብና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) ባዘጋጀው ባለ 200 ገፅ ሰነድ አማካኝነት ነው። የሰነዱ ርዕስ እንዲህ ይላል፣ Edible insects፡ Future prospects for food and feed security። እነ ጉንዳን፣ የመጪው ዘመን የምግብ ዋስት ተስፋዎቻችን እንደሆኑ የሚሰብክ ሰነድ ነው። “ረሃብተኛ ሆኖ ለብዙ አመታት በተመፅዋችነት መቆየት፣ መጨረሻው ውርደት ሆነ? ‘ጥንዚዛ ብላ!’ የሚል የስላቅ ምላሽ የምንሰማበት ደረጃ ላይ ደረስን?” የሚል ጥያቄ የሚፈጠርባቸው የድሃ አገር ሰዎች መኖራቸው የማይቀር ነው። በእርግጥም፣ በርካታ አለማቀፍ የሚዲያ ተቋማት፣ ዜናውን የዘገቡት በስላቅ መንፈስ ነው።
“ዩኤን ለአለማችን ረሃብተኞች አንድ ምክር አለው - በራሪ ነፍሳትን መብላት…” በማለት ነው ያሁ-ኒውስ ዘገባውን የሚጀምረው። የአሶሼትድ ፕሬስ ዘገባም ተመሳሳይ ነው። “የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ረሃብን፣ የአለም ሙቀትንና ብክለትን ለመዋጋት አዳዲስ መሳሪያዎችን ታጥቋል” በማለት የሚጀምረው የአሶሼትድ ፕሬስ ዜና፣ የዩኤን መሳሪያዎችን ለማየት ከፈለግን ሩቅ መሄድ እንደማይኖርብን ይገልፃል። አካበቢያችንን ብንቃኝ በቂ ነው። የዩኤን “ዘመናዊ” መሳሪያዎች፣ በሄድንበት ቦታ ሁሉ በዙሪያችን የሚያንዣብቡና አፍንጫችን ስር ሳይቀር “በረራ” የሚያዘወትሩ ናቸው። ይህንን የስላቅ አገላለፅ በማስቀደም አሶሼትድ ፕሬስ ዘገባውን ሲቀጥል… በዩኤን እምነት፣ የአለም ረሃብተኞች የወደፊት ተስፋ በራሪ ነፍሳትን መመገብ እንደሆነ ይገልጻል።
በዩኤን ስር፣ ለረሃብተኞች የእርዳታ እህል በማጓጓዝ የሚታወቀው ፋኦ፣ በራሪ ነፍሳት ለመብል የሚስማሙ መሆናቸውን ሲያስረዳ “በራሪ ነፍሳት በፕሮቲን የበለፀጉ ናቸው” ብሏል። እናም፣ ዩኤን እና ፋኦ፣ ረሃብን ለመከላከል ተስፋቸውን የጣሉት በበራሪ ነፍሳት ላይ ነው። ግን የነፍሳት ጥቅም፣ ከምግብነትም የላቀ እንደሆነ የገለፁት ዩኤንና ፋኦ፣ ለአካባቢ ጥበቃ ግሩም መፍትሄ ይሆንልናል ብለዋል። በሬና ላም፣ በግና ፍየል ብዙ ሳር እየበሉ አካባቢን ያራቁታሉ፤ የተለያዩ የጋዝ አይነቶችን እያመነጩ አካባቢን ይበክላሉ ይላል ዩኤን። ስለዚህ፣ አካባቢን የማያራቁቱና የማይበክሉ በራሪ ነፍሳት፣ ቀለባችሁ ይሁኑ በማለት ምክሩን ለግሷል። 1900 ያህል የነፍሳት ዝርያዎች ለምግብነት ተስማሚ መሆናቸውን ዩኤን ጠቅሶ፣ ጉንዳን፣ ጥንዚዛ፣ አንበጣ፣ ዝንብ፣ ምስጥ፣ አባጨጓሬ እንዲሁም ሌሎች በራሪና ተስፈንጣሪ ነፍሳትን በምሳሌነት ዘርዝሯል። የዩኤን እና የፋኦ መግለጫ፣ በረሃብተኞች ላይ የተሰነዘረ ስላቅ ይመስላል ብለው የሚቆጡ መኖራቸው አይቀርም።

ነገር ግን ብዙም አይገርምም። እድሜ ልክ እርዳታ እየጠበቀ የሚኖር ረሃብተኛ፣ ውሎ አድሮ “ከራበህ ጥንዚዛ ብላ!” የሚል ምላሽ ማግኘቱ የማይቀር ነው። ውርደት ሊመስል ይችላል። ከሁሉም የከፋ ውርደት ግን፣ ራስን ለመቻል አለመጣርና አለመቻል ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፣ “ጥንዚዛና ዝንብ ተመገቡ” የሚለው ዘመቻ፣ በየጊዜው የሚያገረሽ የዩኤን እብደት ይመስላል። እናም፣ ለጊዜው ከተወራለት በኋላ፣ ወረቱ ሲያልቅ ተረስቶ ይቀራል ብለን እንገምት ይሆናል። ግን በዋዛ አይረሳም። ባለፉት 10 አመታት ለዘመቻው በጀት ሲመደብለት ቆይቷል። አሁንም ይመደብለታል። ለምን ቢባል… ዩኤንና ፋኦ ምላሽ አላቸው -ነፍሳትን የመመገብ ልምድ እንዲስፋፋና የህዝቡን ግንዛቤ ለማሳደግ (awareness raising) በጀት ይመድባሉ።
ሰነዶችን ለማዘጋጀትና ለማሰራጨት፣ በአባል አገራት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማካሄድ፣ አዳዲስ ህጎችንም ለማዘጋጀት ገንዘብ ያወጣሉ። አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት፣ በራሪ ነፍሳትን የማርባት ሥራ እንዲጀምሩም ይደጉማሉ። ዩኤንና ፋኦ፣ ይሄን ሁሉ የሚያደርጉት፣ “ረሃብተኞችን ለመደገፍ” ነው። በሌላ አነጋገር፣ ዩኤንና ፋኦ፣ ብዙ ገንዘብና ሃብት ሳያባክኑበት በፊት፣ “የበራሪ ነፍሳት ፕሮጀክታቸውን” በአጭር ጊዜ እንደዘበት ይረሱታል ተብሎ አይጠበቅም።

Monday, May 27, 2013

“ሰዎች እንብላ የሚሉት ከልባቸው ነው ወይስ እንደው ለነገሩ ያህል?” የዳሰሳ ጥናት ውጤት

ሰሞኑን ማህበረሰባዊ እሴቶቻችን ከሚባሉት በአንዱ ላይ የብድግ ብድግ ናሙና ወስጄ ጥናት እካሄድኩ ነበር፡፡ የጥናቱ ትኩረት የ “እንብላ ባህላችን” ሲሆን ጥናቱን ለማካሄድ ያስፈለገበት ምክንያትም እውነት ይህ ባህል አለ ወይስ ብዙዎች እንደሚሉት “ጎጂ ባህል” ከሚባሉት ተርታ ተሰልፏል የሚለውን እና አለ ከተባለም ሰዎች እንብላ የሚሉት ለአፋቸው ያህል ነው ወይስ ከልብ የሚለውን የምርምር ጥያቄ ለመመለስ ነበር፡፡
የጥናቱ ዘዴ ደግሞ ሰዎች ምግብ በሚመገቡባቸው አካባቢዎች ላይ ማንዣበብና ማፍጠጥ ወይንም ኦብዘርቬሽን ማካሄድ ነበር፡፡ ለጥናቱ  በናሙናነት ከተወሰዱ ተመጋቢዎች መሀል ታዲያ 70 በመቶ ያህሉ “አንብላ” አላሉም፡፡ ስለዚህ አብዛኞቹ “አንብላ ጎጂ ባህል ነው”  ከሚሉት ተርታ ይመደባሉ ማለት ነው የሚል መላ ምት ላይ መድረስ ተችሏል፡፡
ቀሪዎቹ 30 በመቶ ደግሞ ለአፋቸው ያህል እንብላ ቢሉም የዚህ ጥናት ባለቤት ግብዣቸውን ተቀብሎ ለተጨማሪ ምርምር ባደረገው ጥረት ያገኘው ውጤት አስደንጋጭ ነው፡፡ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት “አንብላ ባዮች” ከምግብ ሳህናቸው ላይ አንድ ሁለት ጠብደል ጠብደል ጉርሻዎች ብድግ ብድግ ሲደረጉ ከፊታቸው ላይ የነበረው ፈገግታ ሁላ በአንድ ጊዜ ድራሹ ይጠፋና በምልክቱ አይናቸው ማጉረጥረጥ ጀምሯል፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም “ ቀልድ አታውቅም እንዴ” የሚለውን ጥያቄ ከማንሳት ጀምሮ “ ፍሬንድ አንተም እዘዛ” በማለት የሰው በልቶ አያድሩም ተኝቶ አይነት አቋም ሲያራምዱ ተስተውሏል፡፡ እጃቸውን እንደመታጠብ ብለው በመጥፋትም የምግቡን ዋጋ አጥኚው ከፍሎ እንዲወጣ ያደረጉም አልታጡም፡፡
ይህ ጥናት ለናሙናነት የተጠቀመባቸው ሰዎች ቁጥር አናሳና አካባቢያዊ ስብጥሩም ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ የሀገሪቱን ገፅታ ወካይ ነው ማለት አያስደፍርም፡፡ ይሁንና ለሌሎች የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪዎች ጥናት መነሻ ሊሆን እንደሚችል አጥኚው ይተማመናል፡፡
ጥያቄው አሁንም ክፍት ነው፤   “ሰዎች እንብላ የሚሉት ከልባቸው ነው ወይስ እንደው ለነገሩ ያህል?”

በተጠረጠሩባቸው የሙስና ወንጀሎች የታሰሩት አቶ መላኩ ፈንታ መታመማቸው ተገለጸ

46 ኪሎ ግራም ወርቅ ይዘው 100 ሺሕ ብር የተሸለሙት ተጠርጣሪ ልታሰር አይገባም አሉ

‹‹እኔ በመታሰሬ መንግሥትም ፕሮጀክቶችም ይበደላሉ›› አርክቴክት በእግዚአብሔር አለበል

‹‹ለልጄ ወተት መግዣ ብቻ አንድ ሺሕ ብር ይሰጥልኝ››  የበምጫ ትራንዚት ባለቤት 
በተጠረጠሩባቸው የተለያዩ የሙስና ወንጀሎች ግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ በቁጥጥር ሥር ውለው በእስር ላይ የሚገኙት በሚኒስትርነት ማዕረግ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ መታመማቸውን ጠበቃቸው ግንቦት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው አስታወቁ፡፡

ጠበቃው አቶ መላኩ በአስቸኳይ ሕክምና እንዲደረግላቸው ጠይቀው፣ “እኚህ ሰው በጠና ስለታመሙ የታሪክ ተወቃሽ እንዳንሆን፤” ብለዋል፡፡

የአቶ መላኩን ጤንነት በሚመለከት ጠበቃው በዝርዝር ጠይቀው የሕመማቸው ዓይነትና ደረጃ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ባይረዱም፣ መልካቸው ቢጫ ሆኖ እንዳዩዋቸው ገልጸዋል፡፡ ለምን እንዳላነጋገሩዋቸው ሲጠየቁ በቂ ጊዜ እንዳልነበራቸው የገለጹት ጠበቃው ከእሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውን፣ ነገር ግን ሆስፒታል ይሂዱ ወይም አይሂዱ አለማወቃቸውንም አስረድተዋል፡፡

በአጃቢ ሆነው ሕክምና እንዲያገኙ ጠበቃው ላነሱት ጥያቄ፣ ስለመታመማቸው የሚገልጽ ማስረጃ ከክሊኒክ ወይም ከሆስፒታል እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ያለማስረጃ ትዕዛዝ መስጠት እንደማይቻል ፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡

አቶ መላኩ መንግሥት የሚያውቀውና በአገር ውስጥ ሕክምና የማይድን ሕመም እንዳለባቸውና በውጭ አገር እየታከሙ እንደነበር፣ ለፍርድ ቤቱ ራሳቸውና ጠበቃቸው ማስረዳታቸው የሚታወስ ነው፡፡

በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ለግንቦት 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ቀጥሮት የነበረውን የእነ አምባውሰገድ አብርሃ የምርመራ መዝገብን ተመልክቷል፡፡ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የናዝሬትና ሚሌ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆችን ጨምሮ 11 ተጠርጣሪዎች ቀረጥ በማጭበርበር፣ ክስ በማቋረጥ፣ የኮንትሮባንድ ዕቃ ሳይፈተሽ እንዲያልፍ በማድረግና ተገቢ ያልሆነ ሀብት በማከማቸት የሙስና ወንጀል መጠርጠራቸውን፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎትና ለተጠርጣሪዎቹ አስረድቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚያስችለውን የሰነድና የሰው ማስረጃዎችን መሰብሰቡንና ቃል መቀበል መጀመሩን የገለጸው መርማሪ ቡድኑ ቀሪ ሰነድ ማሰባሰብ፣ የምስክሮችን ቃል መቀበልና የተሰበሰቡ ሰነዶችን የመለየት ሥራ እንደሚቀረው በመግለጽ፣ ፍርድ ቤቱ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡

አቶ አምባውሰገድ የልብ ሕመምተኛ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት፣ መርማሪ ቡድኑ በብርበራ የሚፈልገውን ማስረጃ በመውሰዱና እሳቸውም ሊያጠፉት የሚችሉት ማስረጃ ስለሌለ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡ አቶ ቃለአብ ዘርአብሩክም የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡ የናዝሬት ጉምሩክ ሥራ አስኪያጅ አቶ ያዴሳ ሚደቅሳ ሥራ ከማስተባበር ውጭ ጣልቃ ገብተው የተጠረጠሩበትን ወንጀል እንዳልፈጸሙና ከተያዙ ሰባት ቀናት እንዳለፋቸው በማሳወቅ፣ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜን ተቃውመው የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል፡፡

በሕገወጥ መንገድ በሕገወጦች ተይዞ የነበረን 46 ኪሎ ግራም ወርቅ በመያዝ ከመንግሥት ምስጋናና 100 ሺሕ ብር ሽልማት ማግኘታቸውን የገለጹት የባለሥልጣኑ ባልደረባ አቶ እሸቱ ግረፍ ናቸው፡፡ በተመሰገኑበት ሥራ ሌላ ነገር ሊሠሩ እንደማይችሉ፣ መርማሪዎችም አሉ የተባሉ ሰነዶችን በብርበራ የወሰዱ በመሆናቸውና የሚቀር ነገር የሌለ በመሆኑ ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡

አቶ ጌታሁን ቱጂ፣ አቶ መላኩ ግርማ፣ አቶ አስፋው ሥዩም፣ አቶ ጌታነህ ግደይና አቶ ዮሴፍ አዳዊ የተባሉ የባለሥልጣኑ ሠራተኞች የተጠረጠሩበት ጉዳይ መርማሪ ቡድኑ ካለው ጋር የማይገናኝና የሥራ ድርሻቸውም የማይገናኝ መሆኑን በማስረዳት፣ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

አርክቴክት በእግዚአብሔር አለበል መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ ያስረዳው የመጠርጠሪያ ድርጊት ከእሳቸው ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር እንደሌለ ገልጸው፣ የመንግሥትና የግል የሆኑ ከ60 በላይ ፕሮጀክቶች እንዳሏቸው በማስረዳት፣ ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ ችግር እያጋጠማቸው በመሆኑ ዋስትና እንዲከበርላቸው ደጋግመው ጠይቀዋል፡፡

የባህር ዳርና የጎንደር ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን እንደሚያማክሩ የተናገሩት አቶ በእግዚአብሔር፣ ከ131 በላይ ደረጃ አንድ ተቋራጮችን ከማማከራቸውም በተጨማሪ፣ ክፍያ እንዲፈጸምላቸው እሳቸው የሥራውን ጥራት ማረጋገጥ ስላለባቸው ሥራ እየቆመ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ መንግሥትም ሆነ ሠራተኞች እንደሚበደሉ የገለጹት አርክቴክቱ፣ ሰነዶችን በሚመለከት ሁሉም ሰነዶች በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሚገኙ በመሆናቸው ሊሰውሩና ሊያጠፉ የሚችሉበት አጋጣሚ ስለሌለ፣ እሳቸውን አስሮ ማቆየቱ ምንም ጥቅም እንደሌለው ገልጸዋል፡፡

ሥራ ከሚበላሽና ሠራተኛ ከሚበተን ፍርድ ቤቱ ውክልና ለሌላ ሰው የሚሰጡበትን መንገድ እንዲያመቻችላቸው የጠየቁት አቶ በእግዚአብሔር፣ ከተጠረጠሩበት ወንጀል ጋር ግንኙነት የሌላቸው ሰነዶች እንደተያዙባቸው በመግለጽ እንዲለቀቁላቸው ጠይቀዋል፡፡ ክፍያ የሚፈጽሙት በየዕለቱ ቢሆንም ማህተምና ቼክ ስለተወሰደባቸው የሠራተኞች ደመወዝ፣ የገቢ ግብርና የጡረታ ክፍያ መክፈል አለመቻላቸውንም አስረድተዋል፡፡ አገር እያለሙ መሆኑን በመናገር በዋስ ሆነው ሥራቸውን እየሠሩ ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የጠየቁት አቶ በእግዚአብሔር፣ በመርማሪዎች እንደተነገራቸው ‹‹ሰው ታውቃለህ›› በሚል ብቻ መታሰራቸውን አስረድተዋል፡፡

የችሎቱን ታዳሚዎች ያሳዘነና ከንፈር ከማስመጠጥ አልፎ እንባ እስከ ማፍሰስ ያደረሳቸው የበምጫ ትራንዚት ባለቤት አቶ ዘለቀ ልየው ለፍርድ ቤቱ ያቀረቡት አቤቱታ ነው፡፡ አቶ ዘለቀ የጉምሩክ አስተላላፊ ትራንዚተር መሆናቸውን በጠበቃቸው በኩል ገልጸው፣ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ ስድስት ቀናት ቢሆናቸውም እስከ ግንቦት 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ቃላቸውን አለመስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 19 (4) መሠረት አንድ በቁጥጥር ሥር የዋለ ዜጋ ቃሉን እንዴት መስጠት እንዳለበት የተቀመጠው ድንጋጌም መጣሱን አመልክተዋል፡፡

ቢሯቸው መታሸጉንና በቢሯቸው ውስጥ ያለው ሰነድ ሳይለይ የሚያስፈልገውም ሆነ የማያስፈልገው ሰነድ አንድ ላይ በመታሸጉ፣ በእሳቸውም ላይ ሆነ በመንግሥት ላይ ጉዳት እንደሚያመጣ ተናግረዋል፡፡ ኤልሲ የተከፈተባቸው፣ ሥራ የተጀመረላቸውና ያልተጀመረላቸው ነጋዴዎች ብሔራዊ ባንክ ሄደው እንዳይጠይቁ መቸገራቸውን፣ ወደ አገር ውስጥ ያልገቡ ዕቃዎች ሰነዶች በሙሉ ስለተቆለፈባቸው ለወደብ የሚከፈለው በዶላር መሆኑንና ተጎጂው አገር ጭምር መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የታሸገባቸው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመሆኑ ድርጊቱ ሕገወጥ መሆኑን በመጠቆም እንዲከፈትላቸው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠበቃቸው ጠይቀዋል፡፡

ሕፃን ልጃቸው እሳቸው ሲያዙ ተመልክቶ እስካሁን በመሳቀቅ ላይ በመሆኑ እንዲያገኛቸው እንዲታዘዝላቸውም አመልክተዋል፡፡ ተጠርጣሪው እንዲናገሩ ጠይቀው ሲፈቀድላቸው እምባ እየተናነቃቸው፣ ‹‹እቤቴ አንድም ብር እንኳን ሳይተው መርማሪዎቹ ሁሉንም ገንዘብ ወስደውታል፡፡ የምጠይቀው ለልጄ ወተት መግዣ ብቻ አንድ ሺሕ ብር እንዲሰጡልኝ ነው፤›› ካሉ በኋላ መናገር አልቻሉም፡፡ የችሎቱ ታዳሚዎችም በተጠርጣሪው ንግግር የተወሰኑት ሲያለቅሱ የተወሰኑት ተክዘው ተስተውሏል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ከተናገሩ በኋላ ምላሽ እንዲሰጥ በፍርድ ቤቱ የታዘዘው መርማሪ ቡድኑ፣ አንዳንድ ጥያቄዎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች በመሆናቸው በቢሮ በኩል እንደሚፈቱ ተናግሯል፡፡ የዋስትና መብት ጥያቄን በሚመለከት ጉዳዩ ውስብስብ መሆኑን በመጥቀስ ቢለቀቁ ሰነድ፣ ምስክርና ሌሎች ማስረጃዎችን ሊያጠፉበት እንደሚችሉ በመግለጽ፣ ጥያቄያቸው ውድቅ እንዲደረግና የ14 ቀናት ጊዜ ምርመራ እንደፈቀድለት በድጋሚ ጠይቋል፡፡

ሌላው ፍርድ ቤቱ ችሎቱ ከመጀመሩ በፊት ለመርማሪ ቡድኑ ያነሳው ጥያቄ፣ ተጠርጣሪዎች ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበር ያዘዘውን ትዕዛዝ ኮሚሽኑ ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ቢታዘዝም፣ ለምን ሳይፈጽም እንደቀረ እንዲያብራራ ነበር፡፡ ኮሚሽኑ የተጠርጣሪዎችን ሕገ መንግሥታዊ መብት መከበር አለመከበር የመከታተል ግዴታ እንዳለበትም ፍርድ ቤቱ አስታውቋል፡፡

መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጠው ተጠርጣሪዎች በስድስት መዝገብ ተከፋፍለው የሚቀርቡ ናቸው፡፡ ሥራው ውስብስብ በመሆኑና ለብርበራ ተጠርጣሪው ጭምር የሚወጣበት ጊዜ በመኖሩ፣ ከሕግ አማካሪ ጋር የሚገናኙበትን ጊዜ ረቡዕና ዓርብ መደረጉን፣ የጊዜ ቀጠሮ ያላቸውንም በመለየት ከሕግ አማካሪዎቻቸው ጋር እያገናኘ መሆኑን ገልጿል፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መርማሪ ቡድኑ እንዳብራራው ጉዳዩ ውስብስብ መሆኑን ፍርድ ቤቱ መገንዘቡን ገልጾ፣ የተመርማሪዎች ዋስትና ጥያቄን ውድቅ ማድረጉን በማስረዳት ለመርማሪ ቡድኑ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ በመፍቀድ ለግንቦት 26 ቀን 2005 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን ማለትም በቤተሰብ፣ በሕግ አማካሪና በሐኪም የመጎብኘትና የማግኘት መብታቸውን በሚመለከት የማዕከላዊ እስረኛ ኃላፊ ኮማንደር ብርሃኑ አበበ ቀርበው እንዲያስረዱ በታዘዘው መሠረት ኮማንደሩ ግንቦት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. አስረድተዋል፡፡

ኮማንደር ብርሃኑ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ሁሉም የሕግ አማካሪዎች ደንበኞቻቸውን አግኝተዋል፡፡ በችሎት የተገኙም የሕግ አማካሪዎች ከአቶ ከተማ ከበደ ጠበቃ በስተቀር ሁሉም መገኘታቸውን መስክረዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎችና የሕግ አማካሪዎች የተገናኙበት ቀን ሪፖርት እንዲደረግና አቶ ከተማ ከበደን በሚመለከትም ጥብቅ ትዕዛዝ በማስተላለፍ ለግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ሪፖርት እንዲያደርጉ በድጋሚ አዟል፡፡     


Ethiopian Reporter
 

Wednesday, May 22, 2013

ለ 40 ቀን 40 ለሊት እንጾማለን ብለው ሚስትን ለሞት ዳረጉ ልጆቹም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል

ያለምንም እህል እና ውሃ ጾምን ለ 40 ቀን 40 ለሊት እንጾማለን ብለው ጾማቸውን የጀመሩት የቤተሰብ አባላት ለከፍተኛ ጉዳት እና ለሞት መዳረጋቸውን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።
በጎተራ ኮንደሚኒየም ውስጥ ይኖሩ የነበሩት እነዚህ ሰዎች በሃገራችን እምነት አንጻር ጾም ጸሎትን እያደረግን አምላክን በጸሎት እናስባለን በማለት ጾማቸውን መጀመራቸው ተገልጾአል ።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ ያለው ባል እና ከጂማ ዩኒቨርሲቲ በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቀች ሲሆን ።

ባል በባህርዳር በክሊኒክ ይሰራ የነበር ሲሆን ሚስትም በዚሁ የሙያ ስራ ተሰማርታ ወደ  ባህርዳር ማቅናቷ እና የልጆቿን አባት በፍቅር ግንኙነት ጀምራ ወደ ትዳር አለም አብራው እንደዘለቀች እና ሁለት ልጆችን አፍርተው የ9 አመት እና የስድስት አመት ልጆችንም ማፍራታቸው  የሪፖርተራችን ያጠናቅራል ።

ከምግብ እና ከውሃ ተለይተው ለልጆቻቸው ብቻ በጣም ጥቂት ምግብን በመያዝ በቤታቸው ዘግተው ለቀናቶች ሰንብተዋል ።

ሂደቱ ለ25 ቀናት የተጓዘ ሲሆን ባለቤቷ እያበሰለ ለልጆቹ ከሚያቀርበው ምግብ ለራሱ በጥቂቱ የሚቀምስ ሲሆን ለባለቤቱ ሲሰጣት ግን ምንም አይነት ነገር መመገብ አለመቻሏን እና ምንም አያገባህም በማለት ምላሽ ታክል እንደነበር ዘገባው ያመለክታ.

ሆኖም ግን 40ኛ ቀኑ ከመድረሱ አራት ቀን በፊት የእናት የአፍጠረን መለወጥ ያየችው ህጻን ከወላጅ እናቷ ተለይታ  ከታናሽ እህቷ ጋር በሶፋ ላይ መተኛት መጀመሯን እና ከዚያም በመስኮት እራበን ድረሱልን እያለች መጮኋን እና የጎረቤት ልጅ መጥታ በበር ቀዳዳ በተሰጣት ቁልፍ ከፍታ በመግባት ፣ሁለቱ ህጻናቶች ቆዳቸው ተጣብቆ በምግብ ጉዳት ምክንያት ከስተው የተገኙ ሲሆን ባል እራሳቸውን በመሳት በሆስፒታል በህክምና ክትትል ላይ ናቸው ሚስትዬዋ ግን በህይወት ሊተርፉ አለመቻላቸውን ዘገባው አክሎ ጠቁሞአል.

 

Tuesday, May 21, 2013

በጣና ሃይቅ በደረሰ የጀልባ መገልበጥ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይዎት አለፈ

ትናንት ከቁንዝላ ወደ ደልጊ 102 ሰዎችን አሳፋሮ ሲጓዝ የነበረ ጀልባ በመግለበጡ እስካሁን አምስት ሰዎች መሞታቸውን የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ደልጊ መዳረሻ ስፍራ በግምት 150 ሜትር ርቀት ላይ  ፥ ተሳፋሪዎችን ለማውረድ ሲቃረብ  ጀልባው የመገልበጥ አደጋ እንደደረሰበትም ነው የዓይን እማኞች የተናገሩት።
የመምሪያው ሀላፊ ኮማንደር ዘመነ አመሸ ለባልደረባችን ኤልያስ ተክለወልድ እንደነገሩት ፥ የአደጋው መንስኤ እስካሁን በእርግጠኝነት ባይታወቅም  ፤ ተሳፋሪዎቹ ለመውረድ እየተዘጋጁ ሰለነበር በአንድ ስፍራ መከማቸታቸው የሚዛን መዛባት አስክትሎ ለአደጋው ምክንያት ሊሆን ይችላል ተብሏል።
ፋሲለደስ በመባል የምትጠራውን ጀልባ ሲያሽከረክር  የነበረው ካፒቴን በህይወት የተረፈ ሲሆን ፥ ለፖሊስ በሰጠው ቃልም ይህኑኑ አረጋግጧል ነው ያሉት።
በአሁኑ ወቅት ምናልባትም በህይወት የተረፈ ካለ እና ተጨማሪ አስከሬኖችን የማፈላለጉ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ይህ አይነቱ አስከፊ አደጋ ሲያጋጥም የመጀመሪያው ነው ያሉት ኮማንደር ዘመነ ፥ በቀጣይ ትክክለኛውን መረጃ በማጣራት ምክንያቱን ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን ብለዋል።
 (ኤፍ ቢ ሲ)

Monday, May 20, 2013

ቅዳሜ ኢትዮጵያ ከ ሱዳን ጋር ለምታደርገው ጨዋታ የተጫዋቾች ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ
ግንቦት 12 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ አፍሪካ ህብረት የተመሰረተበትን 50 ኛ አመት  ክብረ በአል ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያ ከሱዳን በምታደርገው ጨዋታ ላይ የሚካፈሉ ተጫዋቾችን ስም ዝርዝር የኢትዮጵያ  ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ይፋ አደረጉ ፡፡
በዚህም መሰረት የተመረጡት ተጫዋቾች ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ደጉ ደበበ ፣አበባው ቡጣቆ፣ቢያድግልኝ ኤልያስ፣አሉላ ግርማ፣ሽመልስ በቀለ ፣አዳነ ግርማ ፣ያሬድ ዝናቡ፣ዮናታን ብርሀነና ተስፋዬ አለባቸው ናቸው ፡፡
ከ ደደቢት ሲሳይ ባንጫ ፣ ስዩም ተስፋዬ ፣ብርሃኑ ቦጋለ፣አይናለም ሃይሉ፣አክሊሉ አየነው ፣አዲስ ህንጻ፣በሃይሉ አሰፋ ፣ጌታነህ ከበደ ፣ምን ያህል ተሾመ ፣ዘነበ ከበደ(አዩካ) ና ዳዊት ፍቃዱ ሲሆኑ ፥
ከ ኢትዮጵያ ቡና ጀማል ጣሰው፣አስቻለው ግርማ ፣ፖክ ጅምስ እና ኤፍሬም አሻሞ፥
ከ መብራት ሃይል አስራት መገርሳ እና መስፍን ወንድሙ፥
ከ መከላከያ ጥላሁን ወልዴ ፥
ከ ኢትዮጵያ መድህን ሳለሃዲን ባርጌቾ፥
ከ ሀዋሳ ከነማ ወንድሜነህ ዘሪሁን፥
ከ ሰበታ ከነማ ደረጀ አለሙ እና ከ ሲዳማ ቡና ደግሞ ሞገስ ታደሰ  ሆነዋል ፡፡
ተጫዋቾቹ ከነገው ግንቦት 13 ማለዳ ጀምሮ በ ፌዴሬሽኑ ጽህፈት ቤት ተገኝተው ሪፖርት እንዲያደርጉም  አሰልጣኙ ጥሪያቸውን አስተላለፈዋል፡፡

የግሉን ዘርፍ በሙስና ወንጀል ተጠያቂ የሚያደርግ አዋጅ ሊወጣ ነው

አዲስ አበባ ፣ግንቦት 10 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን የግሉን  ዘርፍ  በሙስና ወንጀል ተጠያቂ የሚያደርግ አዋጅ  ለመደንገግ በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ ከህብረተሰቡ እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ መክሯል።
አዋጁ ህዝባዊ ድርጅቶች ናቸው ተብለው በሚታሰቡ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች  በግል ኩባንያዎች  እና በአክሲዮን ማህበራት ውስጥ የሚፈፀሙ የሙስና የወንጀል ድርጊቶችን  ተጠያቂ የሚያደርግ አንቀፅ ተካቶበታል ።
ይህም የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ወይንም የአክሲዮን ማህበርን ወይንም የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን በሚያደራጅ ሰው ወይም ኮሚቴ በድርጅቱ ውስጥ በማስፈፀም ሂደት የህዝብ ሃብት እንዳይባክን ለመከላከልም የሚያስችል  ነው ተብሏል። 
በእነዚህ የህዝብ ድርጅቶች ውስጥ የተቀጠሩ ቋሚና ጊዜያዊ ተራ ሰራተኞችም ቢሆኑ በሙስና ወንጀል ውስጥ ከተገኙ ህጉ ተፈፃሚ ይሆንባቸዋል ።
በሚስጢር ሊጠበቁ የሚገቡ የካዝና የመጋዘን ወይም ውድ እቃ የሚቀመጥባቸው የመሳሰሉ ሳጥኖችን ቁልፎች ሆን ብሎ ወይንም በቸልተኝነት ለሌላ ሰው  አሳልፎ በመስጠት ድርጅቶች እንዲመዘበሩ ያደረጉ ሰራተኞችን ለመቅጣትም  በአዋጁ ጠንካራ ድንጋጌዎች እንዲካተቱበት ተደርጓል።
የአዋጁ መውጣትም በእነዚህ የህዝብ ድርጅቶች ላይ የሚታዩ ብልሹ አሰራሮችን በማስተካከል ህጋዊ መስመርን ተከትለው እንዲተዳደሩ ያግዛልም ተብሎ ታስቧል።
በ ታደሰ ብዙዓለም ።
       

ሶሪያውያን እናቶች በሴት ልጆቻቸው ላይ ጨክነዋል

በሶሪያ መላ የታጣለትን የእርስበርስ ጦርነት በመሸሽ ወደ ዮርዳኖስ የተሰደዱ እናቶች፣ ህይወት ፈተና ሆኖባቸው ሴት ልጆቻቸውን “ለጊዜያዊ ትዳር” እየሸጡ ነው፡፡ ስደተኛ ወላጆች በሴት ልጆቻቸው ላይ መጨከን እንደጀመሩ የዘገበው ሲኤስ፣ ኑሮን ለመግፋት የሚያስችላቸው ብቸኛ አማራጭ ሆኖ ያገኙት ሴት ልጆቻቸውን በሺዎች በሚቆጠሩ ዶላሮች ለጋብቻ መሸጥ ነው፡፡ ከዮርዳኖስም ሆነ በሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ጋብቻ ፈላጊ ወንዶች ለሴቷ ቤተሰቦች ገንዘብ የሚሰጡበት ባህል አለ፡፡ ይሄም ሆኖ ግን የሰሞኑ የዮርዳኖስ ስደተኛ ካምፖች “የጋብቻ ገበያ”፣ እርግጥም ወንዶች ሴቶችን ለዘላቂ ትዳር የሚገዙበት አይደለም፡፡ አብዛኛዎቹ “ትዳሮች” ከሳምንታት የዘለቀ ዕድሜ እንደማይኖራቸው የገለፀው ዘገባው፤ ይልቁንም “የወሲብ ገበያ” ሊባል የሚችል መሆኑን አስረድቷል፡፡
ይህንን የሴት ልጆች ሽያጭ ከሚያቀላጥፉትና ራሳቸውን “የጋብቻ ደላላ” ብለው ከሚጠሩት መካከል ሶሪያዊቷ ስደተኛ ኡም ማጄጅ አንዷ ናት፡፡ ኡም ማጄድ ከሰሞኑ እየጦፈ በመጣው የስደተኛ ልጃገረዶች ሽያጭ ገበያ ፋታ አጥታለች፡፡ የሞባይል ስልኳ በገዢዎች ጥሪ ተጨናንቋል፡፡ ኡም ማጄድ ከወላጆች ጋር በመነጋገር ለሽያጭ ከምታቀርባቸው ሴቶች ጠቀም ያለ ኮሚሽን ታገኛለች፡፡ ክብረ ንጽህናዋ ያልተገረሰሰ ልጃገረድ በሰሞኑ ገበያ እስከ 5ሺህ ዶላር ታወጣለች፡፡ አያ የተባለችዋ የ17 አመቷ ሶሪያዊት ስደተኛ አያ፤ ከቤተሰቦቿ ጋር በስደት ወደ ዮርዳኖስ ከመጣች አንድ አመት ያህል ሆኗታል፡፡
ይሄም ሆኖ ግን የስደት ኑሮ ለእሷም ሆነ ለቤተሰቧ አሳር ሲሆንባቸው፣ ብቸኛውን አማራጭ ለመውሰድ ተገደዱ፡፡ አያ ለ70 አመት ሳኡዲ አረቢያዊ “ትዳር ፈላጊ” ሽማግሌ በ3ሺህ 500 ዶላር ተሸጠች፡፡ ትዳር ፈላጊው ሽማግሌ ግን ከሙሽሪት አያ ጋር የመሰረተውን ትዳር ለማፍረስ የፈጀበት የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ “ከእሱ ጋር ያሳለፍኩት አንድ አመት ልክ እንደ አስፈሪ ቅዠት ነበር፡፡ ግማሹን ወር በመራር ለቅሶ ነው ያሳለፍኩት፡፡ ከቤተሰቦቼ ጋር እንድገናኝና እንዳወራ አይፈቅድልኝም ነበር፡፡ ምርጫ አልነበረኝምና በሰቀቀን ነበር የምኖረው” ብላለች - አያ ስለ ሽያጩ ትዳሯ ስትናገር፡፡
እንዲህ ለጋ ልጃገረዶችን ለገበያ አቅርባ የምታሻሽጠው ኡም ማጄድ እየሰራችው ስላለችው ነገር ሃፍረትም ሆነ ፀፀት አይሰማትም፡፡ “መኖር የምችልበት ብቸኛው መንገድ ይህ “ስራ” ነው፡፡ ሶሪያውያን ስደተኞች በዮርዳኖስ ሌላ ስራ መስራትና ገቢ ማግኘት አንችልም፡፡ ስለዚህ ምን ማድረግ እንችላለን?...እንስረቅ?...እንግደል?” ትላለች ማጄድ፡፡ የሚገርመው ግን “አንቺስ የ13 አመት ልጃገረድ ልጅሽን ለመሸጥ ትፈቅጃለሽ?” ለሚለው የጋዜጠኞች ጥያቄ የሰጠችው መልስ ነው፡፡ “በፍፁም አላደርገውም!... ልጆቼን ከምሸጥ አይኖቼን አውጥቼ ብሸጣቸው እመርጣለሁ!” ነው ያለችው ማጄድ፡፡

Friday, May 17, 2013

ከሽሮ ችርቻሮ ወደ ባለአምስት ኮከብ ሆቴል ባለንብረትነት ተሸጋገሩ

ከ200 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተሠራው ሆቴላቸው ቅዳሜ ይመረቃል
በደቡብ ክልል ሐዋሳ ከተማ አንዲት ወይዘሮ ከሽሮ ችርቻሮ ሸያጭ ተነስተው በ200 ሚሊዮን ብር ወጪ ያሠሩት ባለአምስት ኮከብ ሆቴል፣ የፊታችን ቅዳሜ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የሆቴሉ ቃል አቀባይ በተለይ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ወይዘሮ አማረች ዘለቀ የተባሉ የአምስት ወንዶች ልጆች እናት ያሠሩት ይኼው ሆቴል፣ የተለያዩ ደረጃዎች ያሉዋቸው 70 የመኝታ ክፍሎች ሲኖሩት በደቡብ ክልል በዓይነቱ የመጀመርያው ነው ተብሏል፡፡


ሆቴሉ ባለ አሥር ፎቅ መንታ ሕንፃዎች ሲኖሩት፣ ከ250 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ሰዎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ከቃል አቀባዩ ማብራሪያ ለመረዳት ተችሏል፡፡
ወይዘሮ አማረች እዚህ ደረጃ ላይ ሊደርሱ የቻሉት ባለቤታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ እጃቸው ላይ በነበረው የአስቤዛ ገንዘብ ሽሮ ገዝተው በችርቻሮ መሸጥ በመጀመራቸው መሆኑ ታውቋል፡፡ ይህ ዓይነቱ እንቅስቃሴያቸው ከጥቂት ዓመታት በኋላ እየጐለበተ መጥቶ በመሐል ሐዋሳ ላይ “ሴንትራል” የሚል መጠሪያ ያለው አንድ መለስተኛ ሆቴል አቋቁመዋል፡፡ በዚህም ሳይገቱ ይህንኑ መለስተኛ ሆቴላቸውን ወደ ባለአምስት ኮከብ ሆቴል ለማሳደግ መብቃታቸውን ቃል አቀባዩ አስረድተዋል፡፡

Uganda to learn Ethiopia’s development experience

Uganda would like to draw lessons from Ethiopia’s experience in road infrastructure development, members of parliament from that country have said.
An experience sharing forum was held on Monday in Addis Ababa between the MPs and officials of Addis Ababa Roads Authority.
On the occasion, Authority General Manager, Engineer Fekade Haile briefed the MPs on the opportunities and challenges in the sector as well as the present state of the city’s road network.
The MPs commended the Authority for the remarkable achievements it made within a short period of time. 
Source:http://www.ertagov.com/

ዩጋንዳዊው ጋዜጠኛ ስለ ኢትዮጲዊያን ጸባይ የታዘበው በጣም ቁጥቦች ተጠራጠሪዎች


ዩጋንዳዊው ጋዜጠኛ ስለ ኢትዮጲዊያን ጸባይ የታዘበው በጣም ቁጥቦች ተጠራጠሪዎች ምክኒያታዊ የመሆን እና ስሜትን የመቆጣጠር ችግር ያለባቸው ስሜታዊ ቃላትን የሚጠቀሙ, ስድብ ያለበት አገላለጽ የሚያበዙ
ኢትዮጲያ ከሌላው አለም ተለይታ በእግዚያብሔር የተሰራች የሚመስላቸው ሀገራቸውን በጣም የሚወዱ፤ ለሃገራቸው ለመሰዋት የሚሽቀዳደሙ በውበትም፤በእውቀትም ከእነሱ የሚበልጥ ያለ የማይመስላቸው
.......
በምን ያህሉ ይስማማሉ?

ሙሉውን የሚከተለውን ሊንክ ተጭነው ያድምጡት

Thursday, May 16, 2013

አንጋፋዋ ድምጻዊ አበበች ደራራ አረፈች

ለረጂም ዓመታት በራስ ቴአትር በድምጻዊነት ስትሰራና ለአድማጮችዋ ዜማዎችን ስታቀርብ
ኖራ በስተመጨረሻው ወደ እስራኤል ሀገር ከትማ ስትኖረ የነበረችው ታዋቂዋ ድምጸ
መልካሟ አበበች ደራራ ዛሬ ሜይ 16 ቀን ባደረባት ህመም ሳቢያ ሕይወቷ አልፏል፡፡
አበበች ደራራ በሕመም ተይዛ ለበርካታ ወቅት በአልጋ ላይ ከመቆየቷም ባሻገር ጨርሶ
ከሰዎች ጋር ግንኙነት አቋርጣ በሽታዋን ለብቻዋ ስታስታምም እንደነበረች በቅርብ
የሚያውቋት ይናገራሉ፡፡ የአበበች ደራራ አስከሬን በኖረችበት የቴል አቪቭ ከተማ በዛሬው እለት ከቀኑ 3.00PM
ላይ ወደ ቀብር በወዳጅ ዘመዶች ታጅቦ በመሄድ ሥርአተ ቀብርዋም ተ ፈጽሟ ል   ፡ ለወዳጅ ዘመዶቿ መጽናናትን ፈጣሪን ይስጣቸው
ዘንድ እለምናለ

በረከት በቀለ (ፍልፍሉ) ጨምሮ 12 ኮሜዲያኖች ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው

በረከት በቀለ (ፍልፍሉ) ጨምሮ 12 ኮሜዲያኖች ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው ።
እያንጓለለ በሚለው አዲሱ የኮሜዲ(ቀልድ)ስራቸው ክስ የተመሰረተባቸው 13 ኮሜዲያን በመጭው ማክሰኞ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ።አሳቡዮገዳ የሚባል የእምነት ተቋም ውስጥ ክስ የተመሰረተባቸው በረከት በቀለ (ፍልፍሉ) ተመስገን ተመላኩ ፣ጥላሁን እልፍነህ ፣ዋነሶች ፣ሙሉ ቀን ተሾመ (የቴዎድሮስ ተሾመ ታናሽ ወንድም)እና ሌሎችም የሚገኙበት ክስ ነው ።ኮሜዲያኑ የተከሰሱት እያንጓለለ በሚለው አዲስ የፊልም አልበማቸው ላይ የአሳቡዩገዳ የእምነት ተቋምን የዝሙት ማካሄጃ አስመስለው አቅርበዋል በሚል እና የእምነት ተቋሙ አምልኮቱ ይጠቀምባቸዋል የሚላቸውን ስኒ ፣ጀበና፣ ማጨሻ በሚያጣጥል እና በሚያናንቅ መልኩ ተጠቅመውበታል በሚል ነው ክሱ የተመሰረተው።

ኮሜዲያኖቹ የፍርድቤት መጥሪያ የደረሳቸው ሲሆን የፊታችን ማክሰኞ ፍርድቤት ቀርበው ክሱ ጉዳያቸውን የሚታይበትን ሂደን ለመከታተል ነው።በዚህ በጉዳዩ ዙሪያ ያናገርነው እና በሰሜን አሜሪካ ለተወሰነ ጊዜያት ኑሮውን ያደረገው በረከት በቀለ ፍልፍሉ እንደገለጸው ከሆነ የክሱ ሂደትም ሆነ ሁኔታው እሱን እና ጓደኞቹን ያስገረመ ከመሆኑም በላይ ለጉዳዩ ምንም ጥልቀት እውቀት እንደሌለው እና የቀልድ ስራውን ሰርቶ ከሃገር ለስራ ግዳይ መውጣቱን ለማለዳ ታይምስ ዝግጅት ክፍል በስልክ ባደረገው መግለጫ ተናግሮአል። እኛ የማንኛውንም የእምነት ተቋም አንነቅፍም ነገር ግን መቀለድ ማለት ሆኖ መገኘት አይደለም እና ህረተሰብን ለማስደሰት እና ለማዝናናት ስንል የምንሰራቸው ቁምነገር እና ፌዞች ከክፉ ነገር ጋር ተያይዘው ሊቀርቡ የሚታዩ ሊሆን አይገባም ሲል ጠቅሶአል:

Monday, May 13, 2013

በባህር ዳር አንድ ግለሰብ ባልታወቀ ምክንያት 12 ሰዎችን ገደለ

አዲስ አበባ ፣ግንቦት 5 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በባህር ዳር ከተማ ልዩ ስሙ አባይ ማዶ በተባለ አከባቢ ፥ አንድ ግለሰብ 12 ሰዎችን ገደለ ፡፡

ከስፍራው የደረሰን መረጃ ግለሰቡ ሰክሮ እንደነበር ነው የሚያመለክተው ።

የባህር ዳር ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር ደረጀ አቻምየለህ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ፥ ግለሰቡ በውል ባልታወቀ ምክንያት በመንገድ ላይ በከፈተው ተኩስ ከሞቱት 12 ሰዎች በተጨማሪ ሌሎች ሁለት ሰዎች ክፉኛ ቆስለዋል ።

በሰዓቱም ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትል ሲያደርግ እንደነበርና በመጨረሻም ራሱን በወንዝ ውስጥ በመወርወር ህይወቱን እንዳጠፋ ነው ያመለከቱት ።

ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ የፌደራል ፖሊስ አባል መሆኑን የገለፁት ኮማንደሩ ፥ ድርጊቱን የፈፀመበት ምክንያት ግለሰባዊ እንደሆነ አመልክተዋል ።

Source: FBC

Saturday, May 11, 2013

የፌዴራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቁጥጥር ስር የዋሉትን የ13 ተጠርጣሪዎችን ስም ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራሉ የስነ-ምግባር ጸረ ሙስና ኮሚሽን በቁጥጥር ስር የዋሉትን  የ 13 ተጠርጣሪዎች ስም በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል ፡፡  በዚህም መሰረት ኮሚሽኑ ከፍርድ ቤት ህጋዊ የብርበራና የእስስር ትእዛዝ በማውጣት

1. የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር   አቶ መላኩ ፈንታን

2. ምክትል ዳይሬክተሩ አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ
3.እሸቱ ወልደሰማያት - በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
4.አስመላሽ ወልደማሪያም- የቃሊቲ ጉምሩክ ኃላፊ
5.ጥሩነህ በርታ- በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የተወረሱ ንብረቶች አስተዳደር ቡድን መሪ
6.አምኘ ታገለ- የናዝሬት ጉምሩክ ኃላፊ
7.ሙሉጌታ ጋሻው- በኦሮሚያ ልዩ ዞን መሀንዲስ
8.ከተማ ከበደ- የኬኬ ትሬዲንግ ባለቤት
 9.ስማቸው ከበደ- የኢንተርኮንቴንታል ሆቴል ባለቤት
  10.ምህረት አብ አብርሀ- ባለሀብት
  11.ነጋ ገብረእግዚአብሄር- የነፃ ትሬዲግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለቤት
   12.ዘሪሁን ዘውዴ -ትራንዚተርና ደላላ
    13.ማርሸት ተስፉ - ትራንዚተርና ደላላ  በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጓል።

የገቢዎች ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታና ሌሎች ተጠርጣሪዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ

ግንቦት 3 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴራሉ የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን የገቢዎች ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታን እንዲሁም፣ምክትል ዳይሬክተሩን አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስን ጨምሮ 12 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ።
 በግለሰቦቹ ላይ በቂ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች የተሰባሰቡ ሲሆን ጉዳዩ ለፍርድ ቤት እስኪቀርብም ድረስ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲቆዩ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱንም ኮሚሽኑ ገልጿል።
የፌዴራሉ የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን በህዝብና በመንግስት ንብረት ላይ የሚፈጸሙ የሙስና ወንጀሎችን ተከታትሎ አስፈላጊውን መረጃ ካሰባሰበ በኋላ በህግ ፊት አቅርቦ በማስጠየቅ ሙስናን የመከላከልና የመቆጣጠር ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠው አካል ሲሆን ፥ ከዚሁ መሰረታዊ ግንዛቤና ቁርጠኝነት በመነሳትም ኮሚሽኑ ከተለያዩ መንግስታዊ አካላትና ከመላው የሃገራችን ህዝብ ጋር በመደጋገፍ በተጠርጠሪዎች ላይ ህጋዊ ስርዓትን ተከትሎ ምርመራ ያካሂዳል።
በዚህም መሰረት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተለያዩ ባለ ጉዳዮችና ከንግዱ ማህበረሰብ እንዲሁም፣ከልዩ ልዩ መንግስታዊና ህዝባዊ አካላት ጥቆማዎችን ሲቀበል ቆይቷል።ጥቆማዎቹ በአንዳንድ የገቢዎችና ጉምሩክ መስሪያ ቤት ኃላፊዎችና ሰራተኞች እንዲሁም ፥በግል ንግድ በተሰማሩ ህገ ወጥ አካሄድን በሚያዘወትሩ ግለሰቦች ላይ  ያተኮሩ ነበሩ።
ኮሚሽኑ ከህዝቡ  የተቀበላቸውን እነዚህን ጥቆማዎች መነሻ በማድረግም ከብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ጥናት ሲያደርግ ቆይቷል።በጥናቱም በቂ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ሰብስቧል።
ኮሚሽኑ እንዳለው ጉዳዩ ለፍርድ ቤት እስኪቀርብ ድረስ ተጠርጣሪዎቹ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር እንዲቆዩ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚህም መሰረት ከፍርድ ቤት ህጋዊ የብርበራና የእስር ትዕዛዝ በማውጣት፣የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታን እንዲሁም፣ምክትል ዳይሬክተሩ አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ 12 ያህል ተጠርጣሪዎች ናቸው፥በቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረገው።
ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣን መነሻ በማድረግ ተጨማሪ ምርመራውን እንዳጠናቀቀ ህጋዊ ስርዓቱን ተከትሎ ተጠርጠሪዎቹን ከተሟላ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ጋር ለመደበኛው ፍርድ ቤት እንደሚያቀርብ ገልጿል።
ኮሚሽኑ ወደፊትም በጉደዩ ላይ እንዳስፈላጊነቱ ተጨማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጥ አመልክቷል።
በዚህ አጋጣሚም መላው የሃገራችን ህዝብ መንግስት ሙስናን ለመዋጋት ለሚያደርገው ጥረት የተለመደ ትብብሩን እንዲቀጥል ጠይቋል።

በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 12 ባለሥልጣናት በቁጥጥር ሥር ዋሉ

አዲስ አበባ ግንቦት 03/2005 የፌዴራል የሥነ ምግባር ጸረ-ሙስና ኮሚሽን በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለት የመንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት የሚገኙባቸውን በቁጥጥር ሥር አዋለ፡፡ ኮሚሽኑ ከሕዝብ የተቀበላቸውን ጥቆማዎች መሠረት በማድረግ ከብሄራዊ ደህንነነትና የመረጃ አገልግሎት ጋር በመተባበር በጥናት ተሰማርቶ ከቆየ በኋላ በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ 12 ባለሥልጣናትን ነው። በተጠርጣሪዎች ላይ በቂ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን በመሰባሰቡ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት እስኪቀርብ ድረስ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንዲቆዩ ተደርጓል፡፡ በዚህ መሠረት ትናንት ግንቦት 2/2005 ከፍርድ ቤት ህጋዊ የብርበራና የእስር ትዕዛዝ በማውጣት የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፋንታ እንዲሁም የኢትዮጵያ የባሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ የሚገኙባቸው 12 ያህል ተጠርጣሪዎች በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሥር ቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ኮሚሽኑ በዓዋጅ የተሰጠውን ሥልጣን መነሻ በማድረግ ተጨማሪ ምርመራውን እንዳጠናቀቀ ሕጋዊ ሥርዓቱን ተከትሎ ተጠርጣሪዎቹን ከነሙሉ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎቹ ለመደበኛው ፍርድ ቤት እንደሚያቀርብ ማስታወቁን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡

Friday, May 10, 2013

የቤት ፈላጊዎች መስፈርትና የምዝገባ መመሪያ ይፋ ተደረገ

የአዲስ አበባ የኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ቢሮ የቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ  የ 40 በ 60 ፣ የ 10 በ90 እና 20 በ80 የጋራ መኖሪያ  ቤት ፈላጊዎች ማሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታና የምዝገባ ስነ ስርአት ይፋ አደረገ ፡፡ በዚህም መሰረት የ 10 በ 90 እና የ 20 በ 80  ምዝገባ ከሰኔ 3 እስከ 21 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙት በሁሉም ወረዳዎች ይደረጋል ፡፡
የ 40 በ 60 ምዝገባ ደግሞ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ  ከሀምሌ 5 እስከ 17  የሚካሄድ ሲሆን በማህበር ለሚደራጁ ደግሞ ምዝገባው  ከ ሀምሌ 15 እስከ 30 የሚካሄድ ይሆናል ፡፡
ለመንግስስት ሰራተኞች ደግሞ በተለየ ሁኔታ  117 ወረዳ በሚል ምዝገባው ለብቻ የሚካሄድ መሆኑን ቢሮው ጨምሮ አሳውቋል ፡፡
ለምዝገባ ብቁ ለመሆንም በቢሮው የሚከተሉት መስፈርቶች ተቀምጠዋል ፡፡
* እድሜው/ዋ ከ 18 አመት በላይ የሆነ
* በከተማው ውስጥ ቢያንስ ለሁለት ተከታታይ አመታት የኖረና እየኖረ ያለ።
* የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ሆኖ ነገር ግን ለሁለት ተከታታይ አመታት በስራ ወይም በትምህርት ምክንያት ከከተማዋ ውጪ  የኖረበትን ህጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችልና ፥ ማስረጃው ቦታውን ለምን ያክል ጊዜ እንደቆየ ወይም እንደሚቆይ በዝርዝር ካቀረበ ብቁ ይሆናል፡፡
 (ኤፍ.ቢ.ሲ)

የአርባ ስልሳ የቤት ምዝገባ ዝርዝር መግለጫ ዛሬ ይሰጣል

በአዲስ አበባ የአስር ዘጠና፣ የሃያ ሰማንያና የአርባ ስልሳ የቤት ፈላጊዎች ምዝግባን በሚመለከት ዛሬ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫው  በከንቲባው ጽህፈት ቤት የሚሰጥ ሲሆን ፥ ምዝገባው መቼ እንድሚጀመር ፣ በማን አንደሚፈፀምና ተመዝጋቢዎቹ ማሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች  እና ሌሎች ዝርዝር መረጃዎችም  በመግለጫው  ይዳሰሳሉ ተብሏል።
ምንጭ ኤፍ.ቢ.ሲ

Wednesday, May 8, 2013

Ethiopia Aims To Host Africa's Tallest Building

Ethiopia’s capital city, Addis Ababa, may boast Africa’s tallest building by 2017. While a 58-story building had been announced, plans unveiled by a private Chinese developer now call for a 99-story office-hotel tower. Guangdong Chuanhui Group has not revealed the building's estimated cost or other details, including financial arrangements or the names of the architect and engineer.
The site for the Chuanhui International Tower is at the new Addis Ababa Exhibition Centre. The developer says it has acquired the 41,000 sq meter site and the building plans have been approved.
If built, it would supersede by 225 m Africa’s current tallest tower: the 50-story Carlton Centre in Johannesburg.
With a population of about 2.8 million, Addis Ababa is the country's commercial and industrial center, according to the website of the Addis Ababa Chamber of Commerce and Sectoral Associations. Further, the capital is the seat of the African Union (AU) and the United Nations' Economic Commission for Africa and hosts more than 92 embassies and consulates. Several other international organizations also have headquarters or branch offices there.
Skyscraperpage.com lists 17 buildings taller than 12 stories in Addis Ababa; the previous tallest building identified by the site is the proposed 52-story Commercial Bank of Ethiopia headquarters, designed by Henn Architekten, Universal Consultants.
Other tall buildings under construction include the 22-story KK Tower, whose architect has not been identified, and the 14-story African Union Grand Hotel, whose architect is Simon Barakat Architects. Both projects started construction in 2011 and are expected to be completed this year.
While floors three to 55 of the proposed supertower are designed for offices, floors 78 to 94 have been set aside for a 217-room Regency Hotel, according to a statement by Chuanhui, Guangdong Province, China.
Further, Chuanhui has allocated 2,600 sq m for an exhibition hall and ballroom. Occupying 27,000 sq m, the ground floors and basement have been earmarked for retail. A public library will occupy another 1,500 sq m. There will be underground parking for 1,100 vehicles, and 10,000 sq m of the site is reserved for green space.
If completed, the tower would be renamed the Meles Zenawi International Centre to honor the memory of former Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi.
The tower project is one of several projects Chuanhui has planned through its Sino-Ethiopian Chuanhui Investment Holding Group. One project is to establish the so-called Chuanhui Industry Zone, which aspires to be the largest cement production zone in Ethiopia. Another project is to build a large automotive and maintenance center, and yet another is to create a diesel-generator supply-maintenance center jointly with the Guangdong Chuanhui Group and the Shangdong Zibo Diesel Generator Corp.
Guangdong Chuanhui, Science and Technology Development Group Co. Ltd., referred to as the Chuanhui Group, was founded in 1989. It is one of the Guangdong Province’s earliest private group companies.

Tuesday, May 7, 2013

Anti-gay group hopes death penalty will soon be introduced for homosexuality

An anti-gay organisation has expressed hopes that the death penalty for homosexuals will soon be introduced in Ethiopia, and held a conference to discuss the “disastrous” effects of homosexuality in the country.
According to the Huffington Post, United For Life Ethiopia, an Evangelical Christian organisation which receives funding from the UK and the US, expressed hopes that homosexuality would soon be made punishable by the death penalty.
A workshop was also reportedly held by the group which revolved around the discussion of the “disastrous” and “evil” consequences homosexuality has on the country.
It was attended by government officials, religious leaders, health professionals, charities and members of the public.
Homosexuality is currently illegal in Ethiopia, and the UN Refugee Agency notes that typical imprisonment penalties range from ten days up to three years.
The ten year penalty can be given when someone convicted “uses violence, intimidation or coercion, trickery or fraud, or takes unfair advantage of the victim’s inability to offer resistance.”
Last year, Ethiopian government officials, religious leaders and civil representatives declared their opposition to LGBT rights and condemned homosexuality as a western epidemic during an anti-gay conference.
A popular Ethiopian daily newspaper last year alleged that the United States and Europe were plotting to export, spread and promote homosexuality in Ethiopia.
In an article published by Yenga daily, homosexuality was described as rapidly-growing “infestation” whose “carriers” were “estimated” to have reached 16,000.

Sunday, May 5, 2013

የእርድ በሬ ከባሌ ሲመጣ እስከ 3ሺ ብር ተጨምሮበት ይሸጣል


የእርድ በሬ ከባሌ ሲመጣ እስከ 3ሺ ብር ተጨምሮበት ይሸጣል አምና በዚህ ጊዜ የሽንኩርት ዋጋ በአንድ ኪሎ እስከ 19 ብር ደርሶ ሕዝቡን ሁሉ እያንጫጫ ነበር፡፡ ሰሞኑን ግን አንድ ኪሎ እስከ 9 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ የፍየል፣ የበግና የቅቤ ዋጋ ግን ንሯል፡፡ በሾላ ገበያ አንድ ፍየል ጉድ በሚያሰኝ የማይታመን ዋጋ መሸጡን በአካባቢው ያገኘናቸው ደላሎች ነግረውናል 5,500 ብር፡፡ በጥቅሉ ግን፣ የዘንድሮ ገበያ ከአምናው ጋር ሲነፃፀር ጥሩ መሆኑን ያነጋገርናቸው ሸማቾች ነግረውናል፡፡ ገበያው የሚጧጧፈው ቅዳሜ ዕለት ስለሆነ ትክክለኛውን የገበያ ሁኔታ መናገር እንደሚከብድ የተናገሩ አንዳንድ ነጋዴዎች በበኩላቸው፤ የሁለትና የሦስት መቶ ብር መጠነኛ ጭማሪ ቢኖርም ገበያው የተረጋጋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሾላ ገበያ አንድ አዛውንት ከሾላ የከብት ገበያ በግ ገዝተው እያስጐተቱ ወደቤታቸው ያመራሉ፡፡ “ስንት ገዙት?” አልኳቸው፡፡
በአጭሩ 1,200 ብር ብለው ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡ መካከለኛ ዕድሜ ያለው ፈርጠም ያለ ሰው ትልቅ ፍየል እያስነዳ ሲሄድ አስቁሜው “ስንት ገዛኸው?” አልኩት፡፡ ይሄ ተጫዋች ነው፡፡ “እስቲ ገምት” አለኝ፡፡ “ከብት” ገዝቼ እንደማላውቅ ነገርኩት፡፡ “2,000 ብር” ካለኝ በኋላ “ከገበሬዎች ነው የገዛሁት፡፡ የነጋዴዎቹን ዋጋ አትችለውም፡፡ ከገበሬዎቹ ገዝተው ነው የሚያተርፉብህ፡፡ ወደ ላይ ውጣና ገበሬዎቹን ለማግኘት ሞክር” ብሎኝ ሄደ፡፡ የሾላ ገበያ መግቢያው አካባቢ ነጋዴዎች፤ በጐችና ፍየሎችን ከወዲያ ወዲህ ይነዳሉ፡፡ ላዳ ታክሲዎች ከመንገዱ ግራና ቀኝ ቆመው ገዢ ይጠባበቃሉ፡፡ ትናንሽና ትላልቅ የቤት መኪኖች የመንገዱን ጠርዝ ይዘው ተደርድረዋል፡፡ ነጣ ያለውን በግ ወገብ ያዝ ያዝ አድርጌ “ስንት ነው?” አልኩት፡፡ ነጋዴው ፈርጠም ብሎ “30” አለኝ፡፡አልገባኝም፡፡ ግር መሸኘቴን አይቶ “3ሺህ” አለኝ፡፡ ፈርጠም ያለውን ዳለቻ በግ ደግሞ በጣቴ እያመለከትኩ “ያ ስንት ነው?” በማለት ጠየቅሁ፡፡
“35” አለኝ፡፡ ሦስት ሺህ 500 ብር ማለቱ ነው፡፡ የዋጋ ጥሪው የመሸጫ ዋጋ ባይሆንም ከክርክር በኋላ ትልቁን በግ እስከ 3ሺህ ብር እንደሚያደርሱት ሰምቻለሁ፡፡ መካከለኛና አነስ ያለ በግ 1500 ብር ይገኛል፡፡ መካከለኛና አነስ ያለ ፍየል፣ ከ2ሺ እስከ 2500 ብር ይሸጣሉ፡፡ በሾላ ገበያ ነጭ የአደአ ማኛ ጤፍ በኩንታል ከ1600 እስከ 1680 ብር ሲሆን፣ ሰርገኛ ጤፍ እንደየደረጃው በኪሎ 14 ወይም 15 ብር ነው፡፡ በቆሎ፤ ከ5 እስከ 6 መቶ ብር፣ ስንዴ ከ8 እስከ 9መቶ ብር፣ ገብስ ከ7 እስከ 9መቶ ብር ሲሸመት ሰንብቷል፣ የውጭው ሩዝ በኪሎ 14 ብር፣ የአገር ውስጥ ደግሞ ከአስር እስከ 12 ብር ይገኛል፡፡ ፉርኖ ዱቄት በኪሎ 11 ብር ገደማ ነው፡፡ ጐመን ዘር የተፈጨ በጣሳ ሃያ ብር፣ ነጭ ሽንኩርት በኪሎ 25 ብርና ዝንጅብል 15 ብር ሲሆን፤ ቡና የይርጋጨፌ በኪሎ 98 ብር፣ የሐረር መቶ ብር፣ የወለጋ 95 ብር፣ የጅማ 80 ብር ለግብይት ቀርቦ ነበር፡፡
ፈንዲሻ ደግሞ ሩብ ኪሎ 15 ብር ሲሸጥ ውሏል፡፡ ቅቤ ሸኖ ለጋ በኪሎ 175 ብር፣ መካከለኛው 155 ብር፣ የበሰለ 145 ብር ሲሸጥ ሰንብቷል፡፡ እንቁላል 2.40 ብር፣ ቀይ ሽንኩርት የአበሻ 13 ብር፣ ባሮ 8 ብር ሲሸጥ አይተናል፡፡ በሾላ ገበያ የቡና፣ የቅቤ፣ የሽንኩርት፣ የዕንቁላል ዋጋ የተመኑት ይመስላል - ሲዞሩ ቢውሉ የዋጋ ለውጥ የለውም፤ በሁሉም ቦታ ተመሳሳይ ነው፡፡ ዶሮ እንደየዓይነቱ ከ120 እስከ 150 ሲሸጥ ነበር፡፡ እናትና ልጅ ዶሮ ገዝተው ሌላ ነገር ለመሸመት ሲዞሩ አግኝቼ፤ “ገበያ እንዴት ነው?” አልኳቸው፡፡ ልጅቷ ትንሽ አመንትታ፣ “ጥሩ ነው” አለች፡፡ “አምና ሽንኩርት እስከ 19 ብር ሲሸጥ ነበር፡፡ ዛሬ 8 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ ዶሮም ጥሩ ነው፡፡ እነዚህን ዶሮዎች (እግሯ ስር ወዳሉት ዶሮዎች እያመለከተች) እያንዳንዱ 120 ብር ነው የተገዛው፡፡ ጥሩ ነው የሚመስለው” አለችኝ፡፡ ሦስት ዶሮዎች ገዝቶ ወደ ቤታቸው ሲያመሩ ያገኘኋቸው ጐልማሳ፤ አንዱን ዶሮ በ150 ብር፣ ሌሎቹን ሁለት ዶሮዎች በ130ብር ሂሳብ መግዛታቸውን ነግረውኛል፡፡ የሴት ዶሮ ዋጋ 80 ብር ነበር፡፡ ታዲያ የነጋዴዎቹ ጥሪ ከ120 እስከ 170ብር ይደርሳል፡፡ ገርጂ ገበያ ሁለት ትላልቅ ዶሮዎች አንጠልጥለው ያገኘኋቸው አዛውንት እያንዳንዱን በ120 ብር እንደገዙ ነግረውኛል፡፡ “እነዚህ የጐጃም ናቸው፡፡ ከታች ከወደጉራጌ የመጡት 150ብር ይባላሉ፡፡ ኧረ ዘንድሮስ ተመስገን ነው” አሉኝ፡፡
ጠና ያሉ ሁለት ዘመናዊ ሴቶች ትልልቅ የሚባሉ አራት ዶሮዎች በ160 ብር ሂሳብ እንደገዙ ነግረውኛል፡፡ የተለያዩ ዶሮዎችን ዋጋ ስጠይቅ ቆይቼ፤ አንዱን ነጋዴ “ዘንድሮ የዶሮ ገበያ እንዴት ነው?” አልኩት፡፡ “አሁን ገበያው ስላልጦፈ ምን ይታወቃል?” ገበያውኮ ገና ነው” አለኝ ረቡዕ ዕለት፡፡ በገርጂ ወደተሠራው ዘመናዊ የአትክልትና ፍራፍሬ ማዕከልም ጐራ ብያለሁ፡፡ ቀይ ሽንኩርት በኪሎ ከ7 እስከ 8.50 ሲሸጥ፣ ፎሶሊያ በኪሎ ከ12 አስከ 15 ብር፣ ቲማቲም ከ12 እስከ 13 ብር፣ ቃሪያ በኪሎ 24 ብር፣ ካሮት 14 ብር፣ ድንች ሰባት ብር፣ ነጭ ሽንኩርት ከ22 እስከ 24 ብር፣ ዝንጅብል ከ12 እስከ 14 ብር ይሸጣል፡፡ ከማዕከሉ ገዝታ የምትወጣ አንዲት ጋዜጠኛ አግኝቼ፣ “የገበያ ማዕከሉ ዋጋ እንዴት ነው?” አልኳት፡፡ “ያስወድዳሉ፡፡ በፒያሳ የአትክልት ተራ ዋጋ የማገኝ መስሎኝ ነበር፡፡ ግን አይደለም፡፡ ሽንኩርት ከ7.50 እስከ 8 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ በዚህ ዋጋማ በሰፈሬም አገኛለሁ፡፡ ሸክም ብቻ ነው የተረፈኝ፡፡ አትክልት ተራ እስከሆነ ድረስ ቅናሽ ማሳየት ነበረበት” በማለት አማርራለች፡፡ ካዛንቺስ ገበያ በዚህ ገበያ ዕንቁላል 2.50፣ ሸኖ ለጋ ቅቤ 200 ብር፣ ዶሮ ከ150 እስከ 175 ብር፣ ሽንኩርት ደግሞ 7 ብር ሲሸጥ ነበር፡፡ ከሳምንት በፊት ግን፣ ሽንኩርት በአራት ብር፣ ሸኖ ለጋ ቅቤ 140 ብር ተሸጧል፡፡ ነጋዴዎቹ ለዋጋው መጨመር የሚሰጡት ምክንያት፣ ዝናቡ ዘግይቷል የሚል ነው፡፡