Search

Tuesday, September 24, 2013

የከተማ አስተዳደሩ በሚቀጥሉት 2 አመታት 130ሺ ቤቶችን ሊገነባ ነው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ህዝቡን በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስክ የላቀ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ከንቲባ ድሪባ ኩማ አስታወቁ፡፡

አስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸውን የልማት ስራዎች በመገምገም ለቀጣዩቹ 2 ዓመታት ለሚተገብራቸው የልማት እቅዶች አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

ከንቲባ ድሪባ ኩማ እንደገለጹት አስተዳደሩ ለስራ እድል ፈጠራ፣ ለመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ፣ ለማስፈጸም አቅም ግንባታና ለመልካም አስተዳደር ስራዎች ቅድሚያ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ በከተማዋ የሚታየውን ሰፊ የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለማሟላት በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ የተያዘውን 70ሺህ የመኖሪያ ቤት ግንባታ እቅድ ወደ 130ሺህ ከፍ በማድርግ የህብረተሰቡን የቤት ችግር ለመፍታት እየሰራ መሆኑን ከንቲባ ድሪባ አስረድተዋል፡፡

አስተዳደሩ በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት በጨርቃጨርቅ፣ በአግሮ ኢንዱስትሪ፣ በብረታብረትና በሌሎችም የማምረቻ ኢንዱስትሪ ዘርፎች ሰፋፊ ኢንዱስትሪዎችን ከመካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡

አስተዳደሩ በትምህርት ፣በጤናና በሌሎችም የማህበራዊና መሰረተ ልማት ዘርፎች የከተማዋን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ነው የገለጹት፡፡

ከንቲባ ድሪባ እንዳሉት በመልካም አስተዳደር ረገድም የከተማዋ ነዋሪዎች በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት በየዘርፉ ደረጃውን የተጠቀ አገልግሎት ማግኘታቸውን የሚያረጋግጥ ደረጃ ተዘጋጅቶ ባልተፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ የተጠያቂነት አሰራር ተግባራዊ ለማድረግም ዝግጁ ነው፡፡

የከተማው አስተዳደር የኑሮ ውድነትን ለመፍታት በዋነኛነት ለስራ እድል ፈጠራ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው መንግስት በየዓመቱ በብዙ ሚሊዮን ብር ወጪ ወደሀገር ውስጥ የሚያስገባቸው የፍጆታ ዕቃዎች ስርጭትን ህብረተሰቡ በቅርበት እንደሚከታተላቸው በማድረግ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል፡፡

በአስተዳደሩ በማዕከል፣ በክፍለ ክተማና በወረዳ በየደረጃው የሚገኙ የአስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተሳታፊ የሆኑበት የእቅድ ውይይት በየደረጃው ያሉ ሀላፊዎች፣ የመንግስት ሰራተኞችና ህዝቡ እንዲወያበት በማድረግ ወደ ተግባር እንደሚገባም አስታውቋል፡፡
Source - ERTA

Monday, September 23, 2013

የኬኒያ የፀጥታ ሀይሎች በዌስትጌት ታጋቾችን ለማስለቀቅ ዘመቻ ጀምሩ

ኬኒያ  መዲና ናይሮቢ የፀጥታ ሀይሎች በዌስትጌትየገበያ ማዕከል ውስጥ በአሸባሪ ቡድኑ አልሸባብ ታጣቂዎች ተይዘው የሚገኙ  ታጋቾችን ለማስለቀቅ ዘመቻ ጀምሩ ።
በአሁኑ  ወቅት  የፀጥታ ሀይሎቹ የገበያ ማእከሉን  የወረሩ ሲሆን ፥  ከስፍራውም የተኩስ ድምፅ  እየተሰማ ነው ።
ከ10 እስከ 15 የሚጠጉ የአልሸባብ ታጣቂዎች እስካሁን ከገበያ ማዕከሉ እስካሁን እንዳሉ ነው የተመለከተው።
ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ ጥቃት ፈፃሚዎቹን መንግስታቸው የገቡበት ገብቶ እንደሚይዛቸው ተናግረዋል።
አል ሸባብ  ለጥቃቱ  ሀላፊነቱን እንደሚወስድ አስታውቋል ።
ከከተማዋ  እየወጡ ያሉ ዘገባዎች  እንደሚያመለክቱት  እስካሁን  በሽብር ጥቃቱ 69 ዘጠኝ ሰዎች ተገድለዋል ።

በሶማሊያ  የሚገኘው የኬንያ ወታደራዊ ሀይል ጥቃትን ተከትሎ አልሸባብ በኬንያ ጥቃት ሊያደርስ እንደሚችል ለቢቢሲ መናገሩንም ዘገባው  አስታውሷል።
በደቡብ ሶማሊያ እ.እ.አ ከ2011 ጀምሮ አሸባሪውን አልሸባብ ለመታገል ከ4000 የማያንሱ የኬንያ ወታደራዊ ሀይል አባላት መሰማራታቸውንም ዘገባው አስታውሷል።

Thursday, September 19, 2013

ዋሊያዎቹ የአቋም መለኪያ ጨዋታ ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለብራዚሉ የዓለም ዋንጫ ለማለፍ በጥቅምት 3 እና በህዳር መጀመሪያ ለሚጠብቀው የናይጀሪያ ወሳኝ ጨዋታ ለዝግጅት የሚረዳውን የአቋም መለኪያ ጨዋታ ከጋናና ካሜሮን ጋር ሊያደርግ እንደሚችል ተገልጿል፡፡
ሁለቱ ሀገሮች  ከኢትዮጵያ ጋር ለመጫወት ፈላጎት ማሳየታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ አቶ ታረቀኝ አሰፋ ተናግረዋል፡፡
ጋናና ካሜሮን ወቅታዊ ብቃታቸው ጠንካራ የሚባል በመሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ላለበት ወሳኝ ጨዋታ ክፍተቱን ለመሙላት  ወሳኝ አጋጣሚ ይሆናል፡፡
ለወዳጅነት ጨዋታ የተመረጡት ሀገራት ከምዕራብ አፍሪካ መሆናቸው በአብዛኛው ከናይጀሪያ ጋር ተመሳሳይ የአጨዋውት ይዘት በመተግበር ለብሔራዊ ቡድኑ ሰፊ ልምድ እንደሚያካፍሉ ታምኖበት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዛምያ ጋር የአቋም መለኪያ ጨዋታ ሊያደርግ እንደሚችልም ተገልጿል፡፡     
የአቋም መለኪያ ጨዋታው መቸ እንደሚደረግ በትክክል ባይታወቅም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልምምዱን ነገ  እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት ከድልድሉ በኋላ ናይጀሪያን አሸንፈው ታሪክ ለመስራት መነሳሳታቸውን እየገለጹ ነው፡፡
በአንጻሩ የናይጀሪያ ብሔራዊ ቡድን አባላት ኢትዮጵያን በቀላሉ አሸንፈው እንደሚያልፉ ቢናገሩም ንግግራቸው በአሰልጣኝ ስቴፈን ኬሽ አልተወደደላቸውም፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን አቅለን ወደ ሜዳ አንገባም፣ እነርሱ እዚህ የደረሱት ጠንክረው በመስራታቸው እንጅ በስህተት አይደለምሲሉ ስቴፈን ኬሽ ለቢቢሲ ተናግረዋል፡፡
በአዝመራው ሞሴ

ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች ድልድል ይፋ ሆነ

በ2005 የትምህርት ዘመን የ12  ክፍል  የመሰናዶ  ፈተናን  ካለፉት 163ሺህ 406  ተማሪዎች መካከል  103 ሺህ 394 ተማሪዎች በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበዋል ።
ምደባው ዛሬ  በአገር አቀፍ የትምህርት ምዘና  ኤጀንሲ  የተማሪዎቹ  የዩኒቨርሲቲ  ድልደላ  ተካሂዷል ።
ተማሪዎችም የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ  በኤጀንሲው ድረ ገፅ www.nae.gov.et በመግባት “placement result” የሚለውን  በመጫን መመልከት ይችላሉ ።
ወይም በአጭር የፅሁፍ መልዕክት plr ፅፎ  የመለያ  ቁጥርን በማስከተል ለ8181 በመላክ የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ  ማወቅ  የችላሉ ብሏል ኤጀንሲው ።
ምደባው የተከናወነው የ70/30 ቀመርን ባሟላ  መልኩ ከጠቅላላ  ተፈታኞች  ደግሞ  40  በመቶዎቹ  በምህንድስና  ሳይንስ ዘርፍ እንዲገቡ ተደርጓል ።
በምደባው የሴቶችን ተሳትፍ  38 በመቶ  እንዲሆን ታሳቢ  ተደርጎ የተከናወነ ሲሆን ፥ የህክምና  ሳይንስን ምርጫቸው ያደረጉ  ተማሪዎች ደግሞ የመቁረጫ  ነጥብን  ለወንዶች 482  ለሴቶች ደግሞ 477 እንዲሆን  ተደርጓል ።
የምደባ  መመሪያው  በሚፈቅደው መሰረትም  የከፍተኛ  ትምህርት ተቋማትን የቅበላ  አቅምን ታሳቢ ተደርጎ ሴት ተማሩዎች ከወንዶች ጋር ተወዳድረው ከሚያገኙት በተጨማሪ 3 በመቶ እርስ በርሳቸው  ተወዳድረው ወደሚፈልጉት የትምህርት መስክ እንዲገቡ መደረጉን ነው  ኤጀንሲው የገለፀው ።
የሚያጠቡ እናቶች በአቅራቢያቸውና   ተመሳሳይ  ፆታ  ያላቸው  መንትያዎች በአንድ ቦታ እንዲመደቡ እንዲሁም ፥  የጤና  ችግር ያለባቸው  ባቀረቡት  ማስረጃ  መሰረት  ምላሽ  እንዲያገኙ  ተደርጓል ።
በዘንድሮው ድልደላ  በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የሴቶች  ቁጥር ተመጣጣኝ  እንዲሆን  ተደርጓል ።
በኮምፒውተር ታግዞ የተከናወነው ምደባ  የተማሪዎችን ውጤት ፣ የትምህርት መስክንና  የዩኒቨርሲቲ ምርጫን መሰረት በማድረግ  በውድድር ብቻ ተከናውኗል  ብሏል ኤጀንሲው ።
መቀሌ  ዩኒቨርሲቲ  7 ሺህ 312  ተማሪዎቸን  በመቀበል  ቀዳሚው  ሲሆን ፥ አዳማ   ዩኒቨርሲቲ 5 ሺህ 134  ተማሪዎች በመቀበል በሁለተኝነት ሲቀመጥ ፥  4 ሺህ 495 ተማሪዎችን የተቀበለው ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ  ሶስተኛ  ነው ።
ዝቅተኛ  ቁጥር  ያለው ተማሪ  የተቀበለው  ኮተቤ  መምህራን  ትምህርት  ኮሌጅ 955  ተማሪዎች  ተመድበውለታል ።

Tuesday, September 17, 2013

ስለሺ ደምሴ ጋሽ አበራ ሞላ "ያምራል ሀገሬ"ን የሙዚቃ አልበም በብሄራዊ ቴአትር አስመረቀ

ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) "ያምራል ሀገሬ"ን በብሄራዊ ቴአትር አስመረቀ
አዲሱ የስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ)"ያምራል ሀገሬ"የሙዚቃ አልበም ጋሽ ሙላቱ አስታጥቄ፤የትዝታው ንጉስ ሙሃሙድ አህመድ፤አብርሃም ወልዴ እና በርካታ የሙዚቃ ባለሙያዎች፤አድናቂዎች በተገኙበት በብሄራዊ ቴአትር ትናንት ምሽት ተመርቋል፡፡የምርቃት ስነ ስርዓቱ በግብዣ ለተጠሩ እንግዶች ብቻ በመሆኑ በርካቶች በቴአትር ቤቱ መግቢያ ላይ ለመግባት አሰፍስፈው አምሽተዋል፡፡
የምርቃት ስነ ስርዓቱን ድምፃዊት ዘሪቱ ጌታሁን ‘’እንቁጣጣሽ’’ በተሰኘ የአዲስ አመት ዜማዋ ከፍታዋለች፡፡ዘሪቱ ከአርባ አመታት በፊት ያቀነቀነችውን ዜማ ዛሬም ከባህላዊ የሙዚቃ ባንድ ጋር በመድረክ ስትጫወት ለታዳሚው የተለየ ደስታን ፈጥራለች፡፡ዛሬም ድረስ ሙሉ የመጫወት አቅሟ አብሯት መኖሩን አሳይታለች፡፡
የ ‘’ኢትዮ ጃዝ’’ አባት እየተባለ የሚጠራው ሙላ አስታጥቄ በመክፈቻ ንግግሩ ስለሺ ደምሴ የኢትዮጵያን ማህበረሰባዊ ሙዚቃ እና የሙዚቃ መሳሪያዎች ጠብቆ ለማቆየት የሚያደርገውን ጥረት አመስግኗል፡፡
በመድረኩ ነግሶ ያመሸው ስለሺ ደምሴ ከአዲሱ የሙዚቃ አልበሙ በርከት ያሉ ስራዎችን ከ"ያምራል ሀገሬ" ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ጋር ተጫውቷል፡፡ስራዎቹ በባህላዊ ጭፈራ እና ክዋኔ የታጀቡ በመሆናቸው ማራኪ ትዕይንት ሆኖ አምሽቷል፡፡
ስለሺ ደምሴ በሙዚቃ ስራው በክራር አጨዋወቱ፤በዜማዎቹ እና ግጥሞቹ እጅጉን የተለየ አቀራረብ እና አጨዋወት የሚከተል የሙዚቃ ሰው ነው፡፡በብሄራዊ ቴአትር ከአዲሱ አልበሙ ባቀረባቸው ስራዎቹ እንቁጣጣሽን እና የሰርግ ዜማን ከተለመደው ለየት ባለ መንገድ በማቅረብ የአድናቂዎቹን ቀልብ ገዝቶ አምሽቷል፡፡

Monday, September 16, 2013

በአንበሳ ግቢ አንበሳ ሰው ገደለ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 6 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በአንበሳ ግቢ የአንበሶች ማቆያ ማዕከል ውስጥ ዛሬ ከጠዋቱ 1:30 ላይ የሞት አደጋ ተከሰተ።

አደጋው የተከሰተው አቶ አበራ ሲሳይ የተባሉት የአንበሶቹ መጋቢ የአንበሶቹን ማደሪያ እያጸዱ ባሉበት ወቅት ከጥንቃቄ ጉድለት ባልተዘጋው በር የገባው ቀነኒሳ የተባለው አንበሳ ለህልፈተ ህይወት ዳርጓቸዋል።

የግለሰቡን ህይወት ለማትረፍ በወቅቱ በስራ ላይ የነበሩ የግቢው ሰራተኞች ጥረት ቢያደርጉም ሳይሳካ መቅረቱ ለማወቅ ተችሏል።

የሟች አስከሬን ከአንበሶቹ ማደሪያ ወጥቶ ወደ ምኒሊክ ሆስፒታል ተወስዷል።

ተመሳሳይ አደጋ ከዚህ በፊት በ19 89 ዓ.ም መከሰቱ የሚታወስ ነው።

Soucre : FanaBC

Tuesday, September 10, 2013

ከኢትዮጵያ በማደጎ የወሰዷትን ልጅ ለሞት የዳረጉት አሜሪካውያን ቤተሰቦቿ ጥፋተኛ ተባሉ

 ኢትዮጵያዊቷን ሐና ዊሊያምስን በማደጎ ወደ አሜሪካ የወሰዳት ላሪ ዊሊያምስ በቀረበበት ሐናን የመግደል ክስ ጥፋተኛ ተባለ።
በ2008 ከኢትዮጵያ በማደጎነት የተወሰደችው ሐና ከፍተኛ ቅዝቃዜ ቦታ ላይ ተቆልፎባት በደረሰባት የጤና መታወክ ለሞት ሊዳርጋት እንደቻለ ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል።
ከጤና መታወክም ባለፈ ለቀናት ያለምግብ ከምድር በታች ባለ ቤት ውስጥ ተዘግቶባት በመቆየቷ ረሃብ ለሞቷ አንድ ምክንያት እንደሆነም ለፍርድ ቤቱ  አቃቤ ህግ ያቀረበው ማስረጃ ያመለክታል።
በዚህም መነሻነት አቃቤ ህግ ለፍርድ ቤቱ የ13 ዓመቷ ሐና ዊሊያምስን ተከሳሾቹ  አባቷ ላሪና ዊሊያምስና እናቷ ካሪ ዊሊያምስ  ከኢትዮጵያ በማደጎ በ2008 ያመጧት መሆኑን በማስረዳት ሰው በመግደል ክስ መስርቶባቸው ነበር።
ሐና በ2011 ግንቦት ወር ላይ  ቤተሰቦቿ መኖሪያ ጀርባ ባለ ምድር ቤት ለቀናት ተዘግቶባት መቆየቷና የቤቱ የቅዝቃዜ ምጣኔ 4 ዲግሪ ሴልሺየስ መሆኑ ለሞት ሊዳርጋት ችሏል።

ላሪ ዊልያምስና ካሪ ዊልያምስ ከሐና ሞት ከአራት ወራት በኋላ በቁጥጥር ስር ውለው ክሳቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ፥ ፍርድ ቤቱም ሰው በመግደል ወንጀል ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
በተመሳሳይ ተከሳሾቹ  በማደጎ የወሰዱት የ10 ዓመቱ የሐና ወንድም በተመሳሳይ የመደብደብ ፣ የርሃብና በምድር ቤት ተቆልፎበት እንደነበረም መርማሪዎች ደርሰውበታል።
ለዚህም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹን ህጻናት ላይ ጥቃት በማድረስና በአግባቡ ባለመንከባከብ ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
በቀጣዩ ወር የጥፋተኝነት ቅጣት ውሳኔ ፍርድ ቤት እንደሚያሳልፍባቸው ቀጠሮ የያዘ ሲሆን ፥ በተከሰሱበት የዋሽንግተን ግዛት ህግ መሰረት እስከ እድሜ ልክ እስራት ድረስ ሊቀጡ ይችላሉ።

Friday, August 30, 2013

የዩኒቨርሲቲና የመሰናዶ መግቢያ ውጤት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 24 ፣ 2005 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የትምህርት ሚኒስቴር ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና መሰናዶ መግቢያ ውጤትን ዛሬ ይፋ አደረገ።
የዩኒቨርሲቲ መግቢያና ወደ መሰናዶ ማለፊያ ነጥብን ለመወሰን  ፥ የዩኒቨርስቲዎችን ቀጣይ የመቀበል አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት መወሰኑንም ነው ሚኒስቴሩ የገለጸው።
የትምህርት ሚኒስቴር የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ ሳሙኤል እንዳሉት ፥ ዘንድሮ ወደ ዩኒቨርሲቲ የገቡ ተማሪዎች ቁጥር ከአምናው የ95 554 ብልጫ አሳይቷል።
በዚህም መሰረት 10ኛ ክፍል ተፈትነው ወደ መሰናዶ ለመግባት ፥ ለወንዶች 2.71  እና ከዛ በላይ ለሴቶች 2.29 እና ከዛ በላይ ።
ለሁሉም ክልሎች ማየትና መስማት ለተሳናቸው ፥ 2.14 እና ከዛ በላይ ፤ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች ለወንድ 2.29 እና ከዛ በላይ ፣ ለሴት 2.14።
ለግል ተፈታኞች ፤ ለወንድ 2.86 እና ከዛ በላይ ፣ ለሴት 2.29 እና ከዛ በላይ ሆኖ ተወስኗል።
12ኛ ክፍል ተፈትነው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት 265 መቁረጫ ነጥብ ሆኖ ተወስኗል።
ወደ ዩኒቨርሲቲዎች መግቢያ ነጥብም ፥ በተፈጥሮ ሳይንስ ፤ ወንድ 325 እና ከዛ በላይ እንዲሁም ለሴት 305 እና ከዛ በላይ።
ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች ወንድ 305 እና ከዛ በላይ ሴት 300 እና ከዛ በላይ መግቢያ ነጥብ ሆኗል።
ለግል ተፈታኞች ወንድ 330 እና ከዛ በላይ ሴት 320 እና ከዛ በላይ መግቢያ ነጥብ ይሆናል።
በማህበራዊ ሳይንስ ወንድ 285 እና ከዛ በላይ ሴት 280 ከዛ በላይ ሲሆን ፥ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች ፤ ወንድ 275 እና ከዛ በላይ ሴት 270 እና ከዛ በላይ መግቢያ ነጥብ ሆኖ ተወስኗል።
መስማት ለተሳናቸው 270 እና ከዛ በላይ ሲሆን ፥ ማየት ለተሳናቸው ደግሞ 230 እና ከዛ በላይ መግቢያ ነጥብ ይሆናል።
ለሁሉም የግል ተፈታኞች ደግሞ 290 እና ከዛ በላይ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ሆኖ ተወስኗል።
በዚህም መሰረት 265 መቁረጫ ነጥብ ያመጡ ተፈታኞች በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የማታ እንዲሁም፤  በግል ኮሌጆች እና ከፍትኛ የትምህርት ተቋማት በቀን መርሃ ግብር ትምህርታቸውን መከታተል ይችላሉ።
መንግስት እየተገበረ ያለው 70% በተፈጥሮ ሳይንስና እና 30% ማህበራዊ ሳይንስ እንደተበቀ ሆኖ ፥ በተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከገቡ ተማሪዎች መካከል 40.2% በኢንጅነሪንግ ትምህርት እንደሚመደቡም ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባም በቅርቡ ይፋ ይሆናል።
በትእግስት ስለሺ

Monday, August 26, 2013

Top 10 Most Spoken Languages In The World

Although there are over 6,000 languages in existence today, the vast majority of the world speaks less than 150. Of those 150, the usual suspects are all there, however there are a few that may surprise you; English drops to third place and Portuguese overtakes Bengali. Enough teasing, let’s get started.
01. Chinese (Mandarin) – 935 Million Native Speakers
Chinese (Mandarin) – 935 Million Native Speakers

Photo — Link
Of the more than 6.6 billion people in the world, 14.1% of them speak Mandarin Chinese. China has many dialects, but Mandarin Chinese is the most common and widely accepted of them all. It is the native language of roughly 935 million Chinese. 09 more after the break...


02. Spanish – 387 Million Native Speakers 
Spanish – 387 Million Native Speakers
Photo Link — Enokson
Saying “Hola” at spot number two is Spanish with 387 million speakers. This accounts for about 5.85% of the world getting the big bien venido upon entering this world. Also a common second language, for Americans and others, Spanish is quickly gaining ground as a world language partly due to it being widely thought of as the easiest language to learn.[livingbilingual.com/2013/06/11/learning-a-language-the-easiest-language-to-learn] While it has quite a ways to go before it overtakes Chinese, it’s already overtaken number #3… English.
03. English – 365 Million Native Speakers 
English – 365 Million Native Speakers
Photo Link — DonkeyHotey
If you’re reading this, you speak English to some degree (or you are really confused.) While behind Spanish, English is still the lingua franca of the world. It dominates business, trade, and America’s currency, the dollar, is still used on a global scale. Hollywood helps spread our lovely language throughout the world and helps it maintain it as a status language.
04. Hindi – 295 Million Native Speakers

Hindi – 295 Million Native Speakers
Photo Credit: Wikipedia
Hindi is the big-hitter in India. India has over 122 languages with 22 of them recognized by the constitution of India as official languages. Of them, Hindi has emerged as the big dog; the one everyone wants to play with. It is essentially a lingua franca in parts of, if not all of, India. Most Indians can speak or understand it to some degree. India has a lot of people, therefore a lot of people speak Hindi. Logical.
05. Arabic – 280 Million Native Speakers 
Arabic – 280 Million Native Speakers

Photo — Link
Obviously, as astute as you all are, you know this statistic is a bit skewed. Modern Standard Arabic (MSA) is the common language used for news broadcasts and official stuff, however most Arabic-speaking folk speak a dialect of Arabic; Egyptian Arabic, Moroccan Arabic, Algerian Arabic, etc. If these were fragmented off, none of them would easily make the top 10, however, luckily for Arabic, they are all lumped together for official purposes. You got lucky this time, Arabic. Arabic is also one of the hardest languages to learn for English speakers.
06. Portuguese – 204 Million Native Speakers 
Portuguese – 204 Million Native Speakers
Photo Credit: Wikipedia
From Brazil to Portugal, the Portuguese know how to party. They also know how to multiply. From a relatively smaller number of countries, this rabbit-like mammals get it done when it comes to producing little Portuguese speakers.
07. Bengali – 202 Million Native Speakers 
Bengali – 202 Million Native Speakers
Photo Credit: Wikipedia
I bet you didn’t see Bengali coming… in fact, I bet you don’t know what Bengali is. Let me educate you. Bengali is the language native to the southeastern region of Asia known as Bengal. Think Bangladesh. While numbers vary for the ‘native speakers’ of this language, it’s still in a solid place among the top 10 most spoken languages in the world.
08. Russian – 160 Million Native Speakers 
Russian – 160 Million Native Speakers
Photo Credit: Wikipedia
Russian, or Russki as I like to call it (I don’t know why) is a Slavic language that gives me fits when I try to learn it. Written in the Cyrillic alphabet, it looks and sounds foreign to most English speakers. The Russians know how to be cold and decline words. And be tough. And intimidating.
09. Japanese – 127 Million Native Speakers 
Japanese – 127 Million Native Speakers
Photo Credit: Wikipedia
Perhaps the most polite language on the top 10, Japanese is famous for it’s difficulty in addressing various levels of people with regards to their status and respect level. Seemingly two different languages are used for addressing elders and people of authority vs. that annoying kid down the street. With it’s unique writing system, it appears to be really foreign to a large portion of the world. However, to 127 million people, it’s pure comfort.
10. Punjabi – 96-130 Million Native Speakers 
Punjabi – 96-130 Million Native Speakers
Photo Credit: Wikipedia
Ahh Punjabi, what would a top 10 list be without you? Punjabi “…is an Indo-Aryan language spoken by 130 million (2013 estimate) native speakers worldwide making it the 10th most widely spoken language in the world.”
It’s clear to see that the vast majority of languages are comprised of only the top fraction of a percent. Of the 6,000+ languages spoken today, this list of 10 makes up for roughly 45% or so of the total population of the earth. As the world becomes smaller, we lose a lot of the underrepresented languages out there. Whether you consider this a natural part of civilization, or a tragedy, it is happening. There are large efforts out there to support and help preserve near-extinct languages, but it will remain an uphill battle as more and more people jump on the bandwagon to speak one of the more ‘common’ languages.
Author Jeffrey Nelson of LivingBilingual.com

Wednesday, August 7, 2013

Gedion Zelalem

 Zelalem holds German as well as Ethiopian nationality. Zelalem moved with his family from Berlin to the United States in 2006.

The Promising midfielder Gedion Zelalem,who is eligible to play for Ethiopia but has represented Germany at U15 and U16 levels, is regarded within the club as a prodigious talent.

Gedion Zelalem Meets Drogba

Google has dedicated its home page for the 81st birthday of Abebe Bikila

When you see a cartoon of a runner on the Google home page today, don’t ignore it. It is someone you well know. Someone Ethiopia is always proud of.
Google has dedicated its front Page for Abebe Bikila’s 81st birthday. It was on August 7, 1932 the barefoot runner was born.

While trying to access http://www.google.com.et every one will come across a cartoon of the two times marathon champion close to the finishing line on the track.
The picture is linked to various online resources with information, videos and pictures of the athlete. Abebe won two gold medals in the 1960 Rome Marathon and Tokyo 1964.
Ethiopia has become well known in athletics since then. A lot of great runners has followed his foot stape and won a lot of medals not only for the nation but also for the entire continent, Africa.
Google dedicates its home page for commemorating the birthday of influential and famous people of the world, every day.

ፍርድ ቤቱ ኢንተርኮንቲነንታል ሆቴልን ጨምሮ ለሙስና ተጠርጣሪ ንብረቶች ጠባቂ በመሰየሙ ላይ ብይን ሰጠ

ፍርድ ቤቱ ኢንተርኮንቲነንታል ሆቴልን ጨምሮ ለሙስና ተጠርጣሪ ንብረቶች ጠባቂ በመሰየሙ ላይ ብይን ሰጠ

አዲስ አበባ ፣ ሀምሌ 30 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድቤት ሁለተኛ የወንጀል ችሎት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር በዋሉ ግለሰቦች የኩባንያዎቻቸውን ንብረት ጠባቂ ለመሰየም በቀረበለት አቤቱታ ላይ ብይን ሰጠ።

ንብረታቸውን እንዲጠብቅ ወይም እንዲያስተዳድር ገለልተኛ ወገን ይሰየምላቸው የተባሉ ኩባንያዎች ንብረትነቱ የአቶ ስማቸው ከበደ የሆነው የኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል እና ዲ ኤች ሲሜክስ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እንዲሁም የአቶ ከተማ ከበደ ንብረት የሆነው ኬኬ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ፣ የአቶ ነጋ ገብረእግዚአብሄር ንብረት የሆኑት ነፃ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና ባሳፋ ትሬዲንግ ናቸው።
የፌደራሉ ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቢ ህግና የተጠርጣሪ ጠበቆች በጋራ ተሰማምተው የሚያቀርቧቸው አስተዳዳሪዎችን ፍርድ ቤቱ ለመቀበል ቀጠሮ ሰጥቶ የነበር ቢሆንም ፥ ሁለቱም ወገኖች ተስማምተው አስተዳዳሪ ባለማቅረባቸው ፍርድ ቤቱ ዛሬ በሰጠው ብይን ተስማምተው እስከሚያቀርቡ እስከ መስከረም 22 ቀን 2006 ዓ.ም ድረስ ንብረቱ በነበረበት ሁኔታ ይቆይ በማለት አዟል።

የተጠርጣሪ ተወካዮች እስከ መስከረም 22 ቀን 2006 ዓ.ም ንብረቶች ይባክናሉ ሰራተኞችም ደሞዝ አልተከፈላቸውም የሚሉ ምክንያቶችን አቅርበዋል ለችሎቱ ።

ፍርድ ቤቱ ሁለቱ ወገኖች ተስማምተው ሃሳባቸውን በማመልከቻ ፍርድ ቤቱ በሚፈቅደው አሰራር መሰረት ካመለከቱ ፥ ብይኑ ተሰብሮ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብሏል።

የ40/ 60 የጋራ መኖሮያ ቤት ምዝገባ ነሃሴ 6 ይጀመራል

የ40/ 60 የጋራ መኖሪያ ቤት ምዝገባ ነሃሴ 6 የሚጀመር ሲሆን ፥ ምዝገባው  እና የቁጠባ ደብተሩ  እንደ 10/90 እና 20/80  በባንክ ሳይሆን ፤ በአዲስ አበበባ ከተማ በሚገኙ 116 ወረዳዎች የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ገለጸ።
አገልግሎቱ በባንክ እንዳይሆን መደረጉ   የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን  ተሰልፈው ጊዜያቸውን እና  ጉልበታቸውን  የሚያባክኑ ተጠቃሚዎችን  ያግዛል ብሏል ባንኩ።
በዚህ በ 40/ 60 የቤት ፕሮግራም ተጠቃሚ  የቤቱን 40 በመቶ  መቆጠቡ በማረጋገጥ ፥  ቀሪውንና 60 በመቶ የሚሆነውን ደግሞ ከባንክ በሚያገኘው ብድር አማካኝነት  የቤት ባለቤት ይሆናል ።
መቆጠቡ ብቻ ሳይሆን ቤት ፈላጊው  በመመሪያው መሰረት ሌሎች መስፈርፈቶችንም ማሟላት የሚጠበቅበት ሲሆን ፥ ከሁለት አመት በላይ በዚሁ በአዲስ  አበባ ከተማ ነዋሪ ሆኖ ፣ እድሜው ከ 18 አመት በላይ ሊሆን ይገባል የሚለው ደግሞ ቀዳሚው መስፈርት ነው።
ፕሮግራሙ የመንግስት ቋሚ ሰራተኞች ሆነው  በከተማው በሚገኙ በማናቸውም ተቋማት ፣ በፌደራል የመንግስት  መስሪያ ቤቶች እና ልማት ድርጅቶች እንዲሁም ፤ በኦሮሚያ ክልልየተለያዩ ቢሮዎች የሚሰሩ ሆነው በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩትንም ያጠቃልላል።
ከ 18 አመት በላይ ሆነው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮዽያውያን ወይም የውጭ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያንም   ከፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ የሚከለክላቸው አሰራር እንደሌለም ተመልክቷል።
 የአዲስ አበበባ ነዋሪ ሆነው ለሁለት ተከታታይ አመታት በስራ ምክንያትም ይሁን በህክምና እና በሌሎች ሁኔታዎች ከከተማዋ ውጭ የኖሩበትን ህጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉትም መመዝገብ እንደሚችሉ ባንኩ ለንባብ ያበቃው በራሪ ጽሁፍ ይጠቁማል።
ከነሃሴ 6 እስከ 17,   2005 ለሚካሄደው ለዚህ ፕሮግራም ባንኩ ካለፈው ከ10/90 እና 20/80 ልምድ በመቀመር ፥ አዲስ አሰራር በመዘርጋቱ ፤ ለተሳታፊዎች ቀድሞ ቅጾች እንዲደርሱ ይደረጋል ፤ለዚህም ሲባል ከ8 መቶ ሺህ በላይ ቅጾች መዘጋጀታቸውን ነው የባንኩ የብድር ግምገማ ፖርትፎሊዮ ምክትል ፕሬዝደንት አቶ የኋላ ገሰሰ የገለጹት ።
በ40/ 60 የጋራ መኖሪያ ቤት ለመመዝገብም ለአንድ መኝታ 1 ሺህ 33 ብር የቁጠባ ደብተሩ ሲከፈት የሚከፈል ሲሆን ፥ ከዚያ በላይ እከፍላለለሁ የሚል ደንበኛም መክፈል ይችላል ተብሏል ፤ ባለሁለት መኝታ ቤት እንዲሁ 1 ሺህ 575 ብር ፣ ባለ ሶስት መኝታ ቤት 2 ሺህ 453 ብር ለመጀመሪያ ወር መቆጠብ ግድ ይላል።
ደንበኞች  በየወሩ ለተከታታየ 5 አመታት ለመቆጠብ የሚገደዱ  ሲሆን ፥  ቤቱን ከመረከባቸው በፊት ያሉት  ሁለት አመታት እንደ እፎይታ ጊዜ ተቆጥሮላቸው ፤  በቤቱ ዋጋ ላይ የሚታሰብ የሁለት አመት ወለድ መክፈል ይጠበቅባቸዋል ፤ በዚህ ፕሮግራም 6 መቶ ሺህ የሚጠጉቤት ፈላጊዎች ይሳተፉበታል ተብሎም ተገምቷል።
Source - FanaBC

Friday, June 21, 2013

MESSAGE FOR THE SINGLE LADIES AND GENTS

A Very Touching Story..,,

A poor boy was in love with a rich man daughter….One day the boy proposed to her and the girl said…”Hey! Listen, your monthly salary is my daily hand expenses..How can I be involved with you..?

How could you have thought of that? I can never love you, so forget about me and get engaged to someone else at your level”

But somehow the boy could not forget her so easily…..Some time 10 years later they stumbled into each other in a shopping mall.

The lady again said….,”Hey.. ! You! How are you? Now I’m married and do you know how much my husband’s salary is..? $15,700 per month! Can you beat that? And he is also very smart”

The guy’s eyes got wet with tears on hearing those words from the same lady….

A few seconds later, her husband came around but before the lady could say a word her husband seeing the guy, said……
“Sir you’re here and you’ve met my wife..” Then he said to his wife,”This is my boss, I’m also one of those working on his $100 million project!

And do you know a fact my dear? My boss loved a lady but he couldn’t win her heart….That’s why he has remained unmarried since.

How lucky would that lady have been, if she had married this my boss now? These days, who would love someone that much he said all these to his wife.

በምንያህል ተሾመ ጉዳይ ለህዝብ ይፋ ያልሆነው ምስጢር!!

በቀጣዩ ዓመት በብራዚል በሚደረገው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ምድብ ማጣሪያ በምድብ አራት የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ባለፈው እሁድ አምስተኛ የምድብ ጨዋታውን በአዲስ አበባ ደቡብ አፍሪካን በማሸነፍ ለመጨረሻው ዙር ውድድር ማለፉን ቢያረጋግጥም በተጨዋችነት ተገቢነት ጉዳይ በእጁ የገባውን ዕድል መልሶ ማጣቱን የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ አረጋግጠዋል። ‹‹ስህተት ፈፅመናል›› ሲሉም ተናግረዋል። የብሄራዊ ቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ከሜዳ ውጪ ከቦትስዋና ጋር በሜዳችን ላይ በተደረገ ጨዋታ ሁለት ቢጫ ካርድ በማየቱ ምክንያት ከቦትስዋና ጋር በተደረገ የመልስ ጨዋታ ማረፍ ሲገባው ተሰልፎ በመጫወቱ ብሄራዊ ቡድኑ በእጁ የገባውን ዕድል መልሶ ሊያጣ መቻሉን አቶ ሳህሉ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት አስረድተዋል። በፊፋ ህግ አንድ ተጨዋች ሁለት ቢጫ ካርድ ከተመለከተ አንድ ጨዋታ ማረፍ ይኖርበታል። ይህን ደግሞ የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተከታትሎ ማስፈፀም አለበት፡፡ ፊፋ በተለያዩ ምክንያቶች ሳይልክ ቢቀር እንኳን አላሳወክም ተብሎ ሊጠየቅ አይችልም።

ይህም ሆኖ ግን ፊፋ ከቦትስዋናው ጨዋታ 14 ቀን ቀደም ብሎ ምንያህል በቅጣት መሰለፍ እንደሌለበት ለፌዴሬሽኑ አስታውቋል። ባለፈው ረቡዕ ደግሞ መከራከሪያ ነጥብ ካላችሁ በማለት ጉዳዩን በድጋሚ ለማየት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ይሁን እንጂ ፌዴሬሽኑ የመከራከሪያ ነጥብ በማጣቱ ዝምታን መርጧል፡፡ በፊፋ ህግ ለጥያቄው በሁለት ቀን ውስጥ ምላሽ ካልተሰጠ ቅጣቱ ትክክል እንደሆነ ተቆጥሮ ለተጋጣሚው ቡድን ፎርፌ ይሰጣል። በዚህ ህግና ስርዓት መሰረትም ኢትዮጵያ ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ የመጨረሻውን የምድብ ጨዋታ ውጤት መጠበቅ ግድ ሆኖባታል፡፡ ኢትዮጵያ አሁንም ከምድቡ ለማለፍ የተሻለው ዕድል አላት። ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በመረጃ ልውውጥ ችግር ምክንያት ስህተት ሊፈፀም እንደቻለና ለዚህም የቡድን መሪው አቶ ብርሃኑ ከበደ፤አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻውና የአሰልጣኝ ቡድኑ፤ምንያህል ተሾመና አቶ አሸናፊ እጅጉ በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ ቢጫና ቀይ ካርድን ተከታትሎ የማስፈፀምና የማሳወቅ ሀላፊነት ግን የማን እንደሆነ በግልፅ አልተገለፀም። በዋናነት ትኩረት ተሰጥቶት ሲነገር የነበረው ከፊፋ የተላከው መረጃ መድረስ ላለበት አካል ደርሷል አልደረሰም ነው። በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሁሉም ሃላፊነቴን ተወጥቻለው ከማለት ውጪ ችግሩ የእኔ ነው የሚል ወገን ግን አልተገኘም። በዚህም ምክንያት ፌዴሬሽኑ ጉዳዩን ይበልጥ አጠናክሮ በመመርመር በቅርቡ የቅጣት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አስታውቋል። በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ምንያህል ሁለት ቢጫ ለማየቱ መረጋገጫ ሆኖ የቀረበው ከፊፋ የተላከው መረጃ ብቻ ነው። ከኢትዮጵያ ወገን የቀረበ ወይም የተያዘ ምንም መረጃ የለም። እንደ ፊፋ ሁሉ የብሄራዊ ቡድኑ የአሰልጣኝ ቡድን ለፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ወይም ቴክኒክ ክፍል ቢጫና ቀይን በተመለከተ መረጃ ሊሰጥ ቢገባም አልሰጠም። ዋና መረጃ ሊሆን ይገባ የነበረውም ይህ የአሰልጣኝ ቡድኑ የሚያቀርበው መረጃ ነው። ይህ መረጃ ተይዞ ቢሆን ኖሮ ይህ ሁሉ ችግርና ውዝግብ ባልተፈጠረ ነበር። የመረጃ ልውውጡ ባህልና ስርዓት እንዲሁም የጋራ ተጠያቂነቱ ስለሚኖር ምንያህልን በቦትስዋና ጨዋታ ለማሳረፍ የፊፋን ደብዳቤ ባልጠበቅን ነበር፡፡ ቀድሞውኑ መረጃው ስለሚኖር ሰጥተኸኛል አልሰጠኸኝም የሚል ክርክር ባልተነሳ ነበር። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች ሁሌም ቢጫ ለማየታቸው እንደማረጋገጫ እየተደረገ ሲያዝ የነበረው ከፊፋ የሚላከው ደብዳቤ ነው። ግን ስህተት ነው፡፡ ፊፋ ዕሮብ ዕለት ለፌዴሬሽኑ የመከራከሪያ ነጥብ ካላችሁ በማለት ደብዳቤ የላከው ሀገሮች የራሳቸውን ቢጫና ቀይ ካርድ የመያዝ ሃላፊነትና ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ ምናልባት የዕለቱ ዳኛ እና ኮሚሽነር ሪፖርት ሲያደርጉ ቁጥር ወይም ስም ተሳስተው ከሆነ በሚል ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት ለማጣራት ነው። እዚህ ጋር ነገሩን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ዘንድሮ በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ቡና ክለብ ላይ የተከሰተውን እናንሳ ፌዴሬሽኑ የ1ኛ ዙር መጠናቀቅን አስመልክቶ በተደረገ ግምገማ ወቅት እያንዳንዱ ክለብ የተመለከተውን ቢጫ ካርድ ለየክለቦቹ ሰጠ በዚህ ሰነድ ላይ የቡናው ሲሳይ ደምሴ የተመለከተው ሦስት ቢጫ ነው ይላል የቡድኑ አሰልጣኞች የያዙት ደግሞ አራት ቢጫ ይላል ክለቡ ፅህፈት ቤት ጋር ያለው ሰነድ ጋር ሲጣራ ደግሞ በርግጥም አራት ቢጫ ሆነ እናም በቀጣይ ጨዋታ ሲሳይ ደምሴ ቡና ከጊዮርጊስ ሲጫወት ሌላ ቢጫ በማየቱ እንዲያርፍ ተደረገ። ይህ ሲሆን ታዲያ ፌዴሬሽኑ ሲሳይ ማረፍ አለበት ብሎ ደብዳቤ አላከም። ነገር ግን በደንቡ መሰረት ቡና ራሱ ተከታትሎ ማሳረፍ ስለነበረበት እንዲያርፍ አድርጓታል፡፡ የምንያህል ጉዳይም መሆን የነበረበት እንዲህ ነው። ከፊፋ በላይ መረጃው ሊኖር የሚገባው ፌዴሬሽኑ ጋር በተለይም የአሰልጣኝ ቡድኑ ጋር ነው፡፡ ምንያህል በቦትስዋና ጨዋታ ተገቢ ተጨዋች እንዳልሆነ ለማወቅ የፊፋን ደብዳቤ መጠበቅ ባላስፈለገ ነበር። ይህ ሃላፊነት በዋናነት ደግሞ ሊሆን የሚገባው የዋና አሰልጣኙ ነው፡፡ በየትኛውም ክለብ ያለው አሰራር ይህ ነው፡፡ ዋናው አሰልጣኝ ይህን ሃላፊነት መዝግቦ እንዲይዝ የጨዋታ ቀን ለረዳት አሰልጣኙ ወይም ለቡድን መሪው ይሰጣል። ከጨዋታው በኋላም ያንን በመቀበል በራሱ ሰነድ ላይ ያሰፍራል ግልባጩንም ከሌሎች የጨዋታ ሪፖርቶች ጋር አያይዞ ለቴክኒክ ክፍሉ ወይም ለፅህፈት ቤቱ ያሳውቃል፡፡ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ውስጥ የነበረው አሰራር ግን ከእዚህ የተለየ ነው፡፡ ዋናው አሰልጣኝም ሆነ ረዳቱና የቡድን መሪው የጨዋታ ቀን ቢጫና ቀይን በተመለከተ ምንም አይነት መረጃ እንደማይዙና ይህ ብቻ አይደለም ስለ እያንዳንዱ ጨዋታና ተጨዋች በተመለከተ ለፌዴሬሽኑ ሪፖርት እንደማያቀርቡና በፌዴሬሽኑ በኩልም የመጠየቁ ባህል እንደሌለ ባደረግነው ማጣራት ለማረጋገጥ ችለናል፡፡

አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው የብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ከሆኑ ሁለት ዓመት የሞላቸው ቢሆንም ማን ምን ያህል ተጫወተ የሚሉና መሰል ጥያቄዎች ቢጠየቁ መረጃ በግለሰቦች እንጂ በፌዴሬሽኑ የለም፡፡ ለብሄራዊ ቡድኑ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ይወጣል ያ ሁሉ ብር የወጣበት ውድድርና መረጃ ግን በስርዓትና በተደራጀ መልኩ ተይዞ አይቀመጥም፡፡ የብሄራዊ ቡድኑ ሃላፊነት ሙሉ ለሙሉ ለአቶ ሰውነት ቢሰጥም በተመዘገበው ጥሩም ሆነ መጥፎ ውጤት ዙሪያ የፌዴሬሽኑ ሃላፊዎች ከአሰልጣኙ ጋር በየጊዜው ግምገማና ውይይት አያደርጉም፡፡ እንዲያውም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን የብሄራዊ ቡድኑን የአሰልጣኞች ቡድን እንቅስቃሴ በቅርብ የሚከታተለው ከፌዴሬሽኑ ይልቅ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ነው፡፡ የፌዴሬሽኑ ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ ሰኞ ዕለት ከቀኑ 10፡00ሠዓት እስከ ምሽት 2፡30 ሠዓት ድረስ በጉዳዩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ውይይትና ግምገማ አድርጓል፡፡ በዚህ ወቅትም የምንያህልን ቢጫ በተመለከተ ፊፋ ከላከው ውጪ በአሰልጣኝ ቡድኑ አባላት ወይም በፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት የተያዘ መረጃ እንዳለ ጠይቋል። ከማንም ምንም ሊቀርብ ግን አልቻለም፡፡ የፌዴሬሽኑ አመራሮች በቁጣ የአሰልጣኝ ቡድኑን አባላት እና ፅህፈት ቤቱን እንዴት የራሳችሁን መረጃ አትይዙም ሃላፊነቱስ የማን ነው ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ በዚሁ ወቅትም ይህ ሃላፊነት የአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው መሆኑ ተገልፆል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ከቅጥር ውላቸው ጋር ተያይዞ በተሰጣቸውና ሐምሌ 1/2004ዓ.ም ፈርመው በወሰዱት የስራ መዘርዝር ተራ ቁጥር 20 በኢንተርናሽናል ውድድር ወቅት ቢጫና ቀይ ካርድን በተመለከተ ተከታትሎ መዝግቦ የመያዝና የማስወሰን ሃላፊነት የእሳቸው መሆኑ ሰፍሯል። አሰልጣኝ ሰውነት ግን የስራ መዘርዝሩን እንዳላዩትና ሃላፊነቱም የእሳቸው ሊሆን እንደማይገባ ይዘው እንደማያውቁና ወደፊትም እንደማይዙ ተናግረዋል የፌዴሬሽኑ ሃላፊዎችም በአሰልጣኙ ንግግር ክፉኛ በመቆጣት አምርረው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የእኛን ተጨዋቾች ብቻ ሳይሆን የተጋጣሚ ተጨዋቾችን ቅጣት ሳይቀር ተከታትለህ ልትይዝ ይገባል በማለት ሁሉም አቋም ሲይዙ አቶ ሰውነት ጉዳዩን እንዳለሳለሱት ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በጉዳዩ ዙሪያ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንቶችና ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው አስተያየት እንዲሰጡን ተንቀሳቃሽ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ብንደውልም ምላሽ ልናገኝ አልቻልንም። ሰኞ ዕለት በተደረገው ውይይትና ግምገማ ቢጫና ቀይ ካርድን መዝግቦ የመያዙ ሃላፊነት ለማን እንደተሰጠና መሠረታዊ ችግሩ ምን እንደሆነ ቢታወቅም ይህ ግን በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ይፋ አልተደረገም፡፡ በማንም በኩል ይፋ እንዳይደረግና በምስጢር እንዲያዝም ትዕዛዝ እንደተሠጠ ከታማኝ ምንጮቻችን ለማወቅ ችለናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በተፈጠረው ስህተት ዙሪያ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ትናንት የፌዴሬሽኑን ከፍተኛ ሃላፊዎች ጠርቶ አነጋግሯል፡፡ የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አብዲሳ ያደታ ትናንት ረፋድ ላይ የፌዴሬሽኑን ሃላፊዎች በፅህፈት ቤታቸው ረዥም ሰዓት በመውሰድ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያና መረጃ እንዲሰጡዋቸው ጠይቀዋል። ይሁን እንጂ ምን ውሳኔ እንዳሳለፉ ጥረት ብናደርግም ለማወቅ አልቻልንም።

Wednesday, June 19, 2013

Betty may Get kicked out of Big Brother Africa

Elikem Kumordzi, one of Ghana’s representatives in the ongoing Big Brother Africa The Chase reality show could be exiting the show come Sunday.

The Ghanaian has found his head on the chopping block after Monday’s nominations session, having received four nominations.

Elikem seemed to be on the lips of some of the Rubies housemates including his onetime crush, Tanzanian, Feza, who said Elikem is not being true to himself and the other housemates.

South African representative Angelo told Big Brother Elikem could not be trusted because he has also been trying to get people to vote for certain people and that did not go down well him.

Botswana’s Oneal also said his reason for nominating the Ghanaian was that he is guilty of being associated with Zimbabwean, Pokello, and that neither one of them can be trusted.

After nominations in the Rubies house Monday, Elikem and Malawian Natasha had four each while Elikem’s new love Pokello had five.

Lovebirds, Sierra Leonean Bolt and Ethiopian Betty are also up for possible eviction in the Diamond house. Bolt had four nominations while Betty had three. Kenyan, Annabel and Tanzanian, Nando had three nominations each.

Ghana's other representative, Selorm (Selly) Ghalley was however lucky as she received only one nomination. Pokello nominated her due to their never-ending feud.

As stipulated in the show’s rules, the Head of House in the two houses has the power to save or replace nominated housemates after the nominations session.

Bassey, Head of House in the Rubies after pondering over the nominated housemates opted to save Pokello and replaced her with Oneal.

Annabel, Head of House in the Diamond House settled on saving herself from possible eviction. She put up Motamma in her place.

This means that at least two of seven nominated housemates - Bolt, Natasha, Oneal, Betty, Elikem and Motamma – will be packing their bags home come Sunday.























Tuesday, June 18, 2013

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፊፋን ክስ አመነ




አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሰኔ 1 ቀን 2005 ዓ.ም ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡
ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ  አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ከፊፋ ደብዳቤ ደርሶት እንደነበርም ገልጿል፡፡
የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህ መሰረት የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ ፣ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ፣ ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ እና የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች ጥፋተኛ ተብለዋል።
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በጥፋተኞቹ ላይ በቅርቡ ተገቢውን ቅጣት በመውሰድ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የቡድኑ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ፥ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በጨዋታውም አሸንፈን ወደ አለም ዋንጫ እንደምንሳተፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል አሰልጣኙ፡፡
በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ እና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣትም ያስጥላል፡፡

Monday, June 17, 2013

Public Opionion on Betty and Bolt-DW.DE | 14.06.2013

ዶ/ር ቴዎድሮስ ከግብፁ አቻቸው ጋር ባደረጉት ውይይት ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ቀሩ

ዲስ አበባ፣ ሰኔ 10 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከግብፁ አቻቸው ሞሃመድ ካመል አሚር ጋር ተወያዩ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በማለዳው የውይይት ክፍለ ጊዜያቸው ከስምምነት መድረስ ሳይችሉ ተለያይተዋል።

ከሰዓት በኋላም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ  እንደሚወያዩም ይጠበቃል።

ሌሎች የተፋሰሱ ሃገራት የማይቀበሉትንና ግብፅ በቅኝ ግዛት ዘመን በ1929 እና1959 በተደረጉ ውሎች መሰረት የዓባይን ውሃ በበላይነት የልጠቀም ጥያቄን ታሰማለች።

Thursday, June 13, 2013

Man injured when police tried to shoot Hayna

ኮንዶሚኒየም ፎቅ ላይ የወጣውን ጅብ ለማስወጣት በተከፈተ ተኩስ አንድ ወጣት ቆሰለ

በመስከረም አያሌው
በሐያት ኮንዶሚኒየም ሶስተኛ ፎቅ ላይ ወጥቶ አልወርድም ያለውን ጅብ ለማስወጣት በተተኮሰ ጥይት አንድ ወጣት ቆስሎ ሆስፒታል ገባ።
በህንጻው ላይ የሚኖሩ የአይን እማኞች እንደገለፁት፤ ከትናንት በስቲያ ከምሽቱ አራት ሰዓት ገደማ ወደ ህንጻው በማምራት ሶስተኛ ፎቅ አንድ መኖሪያ ቤት በር ላይ የተኛውን ጅብ ትላንት ለማስወጣት አምስት ጥይቶች ተተኩሰው ጅቡ የተገደለ ሲሆን፤ በአካባቢው የነበረ አንድ ወጣት በነጠረ ጥይት ሆዱ ላይ ተመትቶ ሆስፒታል ገብቷል። ፎቁ ላይ የወጣው ጅብ እስከ ትናንት ከረፋዱ አራት ሰዓት ገደማ ድረስ እዚያው ፎቁ ላይ መቆየቱን የተናገሩት ነዋሪዎቹ ጅቡን እንዳዩት በማስፈራራት ለማስወጣት ቢሞክሩም አልቻሉም። ነዋሪዎቹ ለፖሊስ ስልክ ደውለው ያሳወቁ ሲሆን፤ ፖሊስም “ለአካባቢ ጥበቃ በስልክ ጉዳዩን አሳውቀናል” በማለቱ ጅቡ እዚያው ሊያድር ችሏል።
ጅቡ በህንጻው ላይ እስካለበት ጊዜ ድረስ ፎቁ ላይ የነበሩ ነዋሪዎች ከቤታቸው ሳይወጡ መቆየታቸውን የገለፁ ሲሆን፤ ትናንት ጠዋት ላይም አንዳንድ ወላጆች በዱላ እና በአንዳንድ ነገሮች ጅቡን እየተከላከሉ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላካቸውን ገልፀዋል። ጅቡ በህንፃው ላይ ሌሊቱን ሙሉ በማሳለፉ ከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ ሆነው ማደራቸውን የገለፁት የህንጻው ነዋሪዎች፤ ጅቡ ከቦታው እስከተነሳበት ሰዓት ድረስም እንደልባቸው በህንጻው ላይ ለመንቀሳቀስ መቸገራቸውን ገልጸዋል። በህንጻው ላይ እንዲህ አይነቱ ነገር ሲፈጠር ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን የገለፁት ነዋሪዎቹ፣ በሁኔታው በጣም መደናገጣቸውን ገልጸዋል።
ጅቡ በህንጻው ላይ ሌሊቱን ሙሉ ካሳለፈ በኋላ እስከ ትናንት ረፋድ አራት ሰዓት ድረስ እዚያው የቆየ ሲሆን፤ አራት ሰዓት ተኩል አካባቢ በፖሊስ አማካይነት በአምስት ጥይቶች ተገድሎ ከህንጻው ላይ ሊወርድ ችሏል።n
(ምንጭ፡-ሰንደቅ ጋዜጣ 8ኛ ዓመት ቁጥር 405 ሰኔ 5/2005)

Thursday, June 6, 2013

ነባር የ20/80 ቤት ተመዝጋቢዎች ዝርዝር ይፋ ሆነ

የጋራ መኖሪያ ቤቶች ምዝገባ በወረዳና በተመረጡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ይካሄዳል

የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፈላጊዎች በወረዳና በተመረጡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ምዝገባ እንደሚያካሄዱ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዛሬ ግንቦት 28/2005 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ በአዲስ አበባ በተለያዩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መርሃ ግብር የሚመዘገቡ የከተማዋ ነዋሪዎች በወረዳና በተመረጡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መሆኑን ገልጿል፡፡
ነባር ተመዘጋቢዎች ዳግም እንዲመዘገቡ የተፈለገው መረጃውን ለማጥራትና የቤት ፍላጎታቸውን መቀየር ለሚፈልጉ ለማመቻቸት ነው ብለዋል በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የመኖሪያ ቤቶች ልማትና የመንግስት ህንጻዎች ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሀላፊ አቶ አማረ አስግዶም፡፡
የመንግስት ሰራተኞች 20 በመቶ ቅድሚያ የማግኘት እድል ተሰጥቷቸዋል፡፡ ለመመዝገብ ሲሄዱም የቀበሌ መታወቂያ ከሌላቸው የታደሰ የሰራተኛ መታወቂያ መያዝ እንዳለባቸው አቶ አማረ ተናግረዋል፡፡
በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በውክልና በ40/60ና በቤቶች ስራ ማህበራት መርሃ ግብር ብቻ መመዝገብ ይችላሉ፡፡
ከሰኔ 3 እስከ ነሐሴ 17/2005 ዓ.ም በ10/90፣ 20/80 አዲስና ነባር፣ በቤቶች ስራ ማህበራትና በ40/60 ቤት ፈላጊዎች ምዝገባ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ቅጾች በአዲስአበባ ቤቶች ልማት ኤጀንሲ መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን መንግስቱ ተናግረዋል፡፡
በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ኤጀንሲው ከሚያቀርባቸው የመመዝገቢያ ቅጾች ውጭ ቅጾች እየተሸጡ በመሆኑ ቤት ፈላጊዎች በምዝገባ ወቅት በመመዝገቢያ ወረዳዎች በሚሰጣቸው ቅጾች ብቻ መጠቀም እንዳለባቸው አቶ መስፍን አሳስበዋል፡፡
ቤት ፈላጊዎች ለምዝገባ ከመምጣታቸው በፊት የቁጠባ ሂሳብ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መክፈት የግድ መሆኑንና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚታየውን መጓተት ለማስተካከልም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ምዝገባው በከተማዋ በ116 ወረዳዎችና ከ177 በላይ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በዚህ የበጀት አመት 95 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ ሲሆን 24 ሺህ ቤቶች ተጠናቀዋል፡፡

ከሰኔ 3/2005 ዓ/ም ጀምሮ በሚካሄደው ምዝገባ ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን በላይ ቤትፈላጊዎች ይመዘገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ፡፡
ሪፖርተር ፡-አዝመራው ሞሴ

Wednesday, June 5, 2013

ለቤት ምዝገባ የሚያስፈልገውን የባንክ ሂሳብ ለመክፈት የሚስተዋለውን ሰልፍ ለማቅለል መፍትሄ ማዘጋጀቱን ባንኩ ገለፀ


ኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በ10/90 እና በ20/80 የመኖሪያ ቤት መርሃ ግብር መሰረት  ለመመዝገብ የሚያስፈልገውን ዝግ የባንክ ሂሳብ ለመክፈት በየቅርንጫፎቹ እየተስተዋለ ያለውን ሰልፍ ለማቅለል መፍትሄ እያዘጋጀሁ ነው አለ፡፡
ባንኩ  እንዳለው የሚስተዋለውን ረዥም ሰልፍ ለማስቀረት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከሁለት ሰአት እስከ ምሽቱ 11 ሰአት  የሚካሄደውን ምዝገባ በምሽትም ማድረግና እሁድን ተጨማሪ የስራ ቀን ማድረግም ከመፍትሄዎቹ መካካል ናቸው፡፡
ያም ሆኖ ህብረተሰቡ እስከ ሰኔ 21 ድረስ ዝግ ሂሳቡን መክፈትና ጎን ለጎንም ምዝገባውን በማካሄድ ሰልፉን ማቅለል ይችላልም ተብሏል፡፡
ባንኩ በትናንትናው እለት የቁጠባ ደብተር መስጠት የጀመረ ሲሆን ፥ በእለቱም ከ14 ሺህ የሚበልጡ ሰዎች የቁጠባ ሂሳብ ከፍተዋል፡፡ ይህ ቁጥር እስከዛሬ ረፋድም 40 ሺህ መድረሱን የባንኩ ባለስልጣናት ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ቁጥር ውስጥም 2 ሺህ የሚሆኑት ብቻ ለ10/90 ሲመዘገቡ ቀሪዎች ደግሞ 20/80ን ምርጫቸው አድርገዋል ተብሏል፡፡
ሰኞ ለሚጀመረው የቤቶች ምዝገባ ከ4 ሺህ በላይ መዝጋቢ ሰራተኞች የተዘጋጁ ሲሆን ፥ በመብራት መቋረጥ ምክንያት ምዝገባው እንዳይቋረጥም በየምዝገባ ጣቢያዎቹ ጀነሬተሮች ተዘጋጅተዋል፡፡
የ 10/90 የቤት ፕሮግራም ከዚህ በፊት ያልነበረ በመሆኑ ፥ በዚህ የቤት መርሃ ግብር የሚመዘገቡ ነዋሪዎች በሚቀጥለው አመት በሚጠናቀቁት  24 ሺህ ቤቶች ቅድሚያ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
በነዚህ የቤት መርሃ ግብሮች የሚመዘገቡ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም በሚገኙበት አገር የገንዝብ ኖት እንዲቆጥቡም በአዲስ አበባ ቤቶች ኤጀንሲ በኩል መልእክት ተላልፏል፡፡

Monday, June 3, 2013

በአዲሱ የቤት ፈላጊዎች ምዝገባ ህገወጦችን ለጠቆመ 15 በመቶ ወሮታ ይከፈለዋል

የምዝገባ መረጃዎቹ በጠ/ሚኒስትሩ ቢሮ የመረጃ ማጠራቀምያ ቋት ይገባሉ
የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ባወጣው አራት አይነት የመኖሪያ ቤቶች ምዝገባ፤ ህገወጥ መረጃዎችን ያቀረቡና በህገወጥ መንገድ የተመዘገቡ ወገኖች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ ያስታወቀ ሲሆን፣ ህገወጦችን ለሚጠቁሙ ዜጐች 15 በመቶ ወሮታ የሚከፈልበት አሠራር ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መሥፍን መንግስቱ ከትናንት በስቲያ ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጡት ማብራሪያ፤ ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ችግር በሚታይባት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተጀመረው ፕሮግራም ይህ አብዛኛውን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ እንደሚታሰብ ገልፀዋል፡፡
የከተማዋ ነዋሪዎች በእኩልና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ የቤት ችግራቸውን እንዲያቃልሉ ታስቦ በከፍተኛ ጥንቃቄ የቤት ፈላጊዎች ምዝገባው እንደሚካሄድ ጠቁመው፤ በህገወጥ መንገድ ለመመዝገብ በሚሞክሩና ከወጣው መስፈርት ውጪ ተመዝግበው በሚገኙ ዜጐች ላይ የማያዳግም ጥብቅ እርምጃም እንደሚወሰድ ተናግረዋል፡፡ እነዚህን ህገወጦች ለሚመለከተው አካል ለሚጠቁሙ ወገኖችም የ15% ወሮታ ለመክፈል የሚያስችል አሠራር ለማውጣት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አቶ መስፍን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ ምዝገባው በከፍተኛ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች የሚከናወን መሆኑን የተናገሩት ሃላፊው፤ መረጃዎቹ በኔትወርክ እንዲያያዙና በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ በሚገኝ የመረጃ ማጠራቀሚያ ቋት ውስጥ እንዲገቡ ለማድረግ የሚያስችል አሠራር መደራጀቱንም ገልፀዋል፡፡
መስተዳድሩ የመኖሪያ ቤት ፈላጊዎች የመመዝገቢያ ቀናትን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ ቤት ፈላጊዎች በተሰጠው የጊዜ ገደብ ብቻ ቀርበው እንዲመዘገቡ አሳስቧል፡፡ በወጣው ፕሮግራም የ10/90 እና 20/80 ወይም የኮንዶሚኒየም ቤቶች ተመዝጋቢዎች ከሰኔ 3 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ምዝገባቸውን የሚያካሂዱ ሲሆን፣ በ1997 ዓ.ም ተካሂዶ በነበረው የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምዝገባ ተመዝግበው እስከ አሁን ድረስ እጣው ያልወጣላቸው ዜጐች በዚህ ምዝገባ እንደ አዲስ ሊመዘገቡ እንደሚገባም ተገልጿል፡፡ የቀድሞ የኮንዶሚኒየም ምዝገባ በአዲሱ ምዝገባ ተሻሽሎ የሚከናወን ሲሆን ከዚህ በኋላ የ1997 ዓ.ም ምዝገባ ዋጋ እንደማይኖረው ተጠቁሟል፡፡
ቤት ፈላጊዎች ከተመዘገቡ በኋላ በድጋሚ በሚካሄደው የማጣሪያ ምዝገባ የጣት አሻራ እንዲሰጡ እንደሚደረግና ለዚህም የሚያገለግሉ የመሣሪያዎች ግዢ እየተከናወነ እንደሆነ ዋ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ተመዝጋቢዎች እንደየሚመዘገቡበት የቤት ልማት ዓይነት መቆጠብ የሚገባቸውን የገንዘብ መጠን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ በመቆጠብ የባንክ ደብተር መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ነባር የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች፣ በአዲሱ ምዝገባ ለባለ ሶስት መኝታ ቤት 685 ብር፣ ለባለ ሁለት መኝታ ቤት 561 ብር፣ ለባለ አንድ መኝታ ቤት 274 ብር እንዲሁም ለስቱዲዮ 151 ብር በቅድሚያ ሊቆጥቡ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ ለአዲሱ የ20/80 ወይም የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምዝገባ ለባለ ሶስት መኝታ ቤት 489 ብር፣ ለባለ ሁለት 401 ብር እንዲሁም ለባለ አንድ 196 ብር መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡ በቀድሞ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምዝገባ ተመዝግበው እጣ ያልወጣላቸውና በዚህ ምዝገባ እንደ አዲስ የሚመዘገቡ ነባር ተመዝጋቢዎች ከአዲሶቹ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንደሚስተናገዱም ተገልጿል፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች የተዘጋጀው የ10/90 የስቱዲዮ ቤቶች ደግሞ 187 ብር በቅድሚያ መቆጠብ የሚገባ ሲሆን፣ የእነዚህ ቤቶች ግንባታ በአብዛኛው እየተጠናቀቀ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ የ40/60 ቤቶች ምዝገባ ተጠቃሚ የሚሆኑት የተሻለ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች አካላት እንደሆኑ የተናገሩት አቶ መስፍን፤ ሙሉ ክፍያ ለሚከፍሉ ተመዝጋቢዎች ቅደሚያ እንደሚሰጥም ጠቁመዋል፡፡ የእነዚህን ቤቶች ምዝገባ በተመለከተ በባንክ በኩል መመሪያዎች ወጥተው ተፈፃሚ እንደሚደረጉም ሃላፊው ገልፀዋል፡፡ የማህበራት ምዝገባም በቡድን እየተደራጁ በሚመጡ ወገኖች ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመው፤ በምዝገባ ወቅት የቤቱ ዋጋ 50% እና መሬት ተዘጋጅቶ የግንባታ ፈቃድ ከመሰጠቱ በፊት 50% በዝግ ሂሳብ የሚቀመጥ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡ ለ40/60 ቤቶች ምዝገባው ከነሐሴ 6 እስከ ነሐሴ 17 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ የሚከናወን ሲሆን ማህበራት ደግሞ ከሐምሌ 15 ቀን እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ምዝገባቸውን እንደሚያከናውኑ ተጠቁሟል፡፡ በአዲሱ የቤት ፈላጊዎች ምዝገባ በቀን ከ100ሺ በላይ ሰዎች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አቶ መስፍን ተናግረዋል፡፡ የመንግስት ሠራተኞችን በተመለከተ በልዩ የምዝገባ አሠራር በየመ/ቤቶቻቸው በኩል እንዲከናወን መወሰኑም ተገልጿል፡፡

Saturday, June 1, 2013

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ ወደቆ ያገኘውን 3.4 ሚሊዮን ብር ለባለቤቱ አስረከበ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአንድ መንገደኛ የጠፋ 184 ሺህ ዶላር ወይም ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ  ለባለቤቱ አስረከበ፡፡
በኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽዳት ስራ የሚሰራው ብርሃኑ ጀምበሩ የተባለው የ21 አመት ወጣት ሥራውን ሲያከናውን የተጠቀለለ እቃ ያገኛል ፥ብርሃኑ ጥቅሉ  ገንዘብ መሆኑን ቢያቅም ለበላይ ኃላፊዎች ማስረከቡን ይናገራል፡፡
የገንዘቡ ባለቤት በኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ንግድ የተሰማሩና ዜግነታቸው ጋምቢያዊ የሆነው መንገደኛ ወደ ሆንግ ኮንግ ጉዞ ሲያደርጉ ባለፈው ማክሰኞ ምሽት ነበር በተሳፈሩበት አውሮፕላን ላይ ገንዘባቸውን ረስተው የወረዱት፡፡
ለክፍያ ያዘጋጁት ገንዘብ  ከአንጎላ ዋና ከተማ ሉዋንዳ ተሳፍረው ሆንግኮንግ እስኪደርሱ ድረስም መጥፋቱን  አላወቁም ነበር፡፡ግለሰቡ ገንዘባቸው መጥፋቱን ባወቁ ቅፅበት ግን፥ ለአየር መንገዱ አግባብ ባለው መስመር ገንዘባቸው መጥፋቱን ያሳውቃሉ፡፡
በዚህም በትናንትናው እለት ካሉበት ቦታ መጥተው ገንዘባቸውን ለመረከብ በቅተዋል፡፡በኢትዮጵያ አየር መንገድ ታሪክም ይህን የሚያክል ከፍተኛ ገንዘብ ለባለቤቱ ሲመለስ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው ተብሏል፡፡

Wednesday, May 29, 2013

ኢትዮጵያዊቷ ወጣት በአትላንታ 25 ዓመት እስር ተፈረደባት

ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ሮዳስ ተክሉ እዚህ አትላንታ ከተማ በዋለው የወንጀል ጉዳዮች ችሎት ቀርባ ጉዳይዋ ሲታይ ከቆየ በኋላ ባለፍው ሰኞ MAY 20/2013 ….. 25 ዓመት እስር ተፈረደባት። ሮዳስ ተክሉ ይህ የተፈረደባት የሰው ነፍስ በማጥፋቷ ወንጀሉንም መፈጸሟን በማመኗ ነው።
የኋላ ታሪኩ እንዲህ ነው። ፌብሩዋሪ 5 ቀን 2009 አመሻሽ ላይ በአትላንታ የተፈጸመው ወንጀል መላው የአትላንታ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን በቅርብ፣ ነገሩን የሰሙና በሌሎች ከተሞች ያሉትን ደግሞ በሩቅ ያስደነገጠ ነበር። 3754 ቢፈርድ ሃይዌይ የሚባለው የአትላንታ መንገድ ላይ የጸጉር መከርከሚያ ሱቅ ከፍቶ በመስራት ላይ የነበረው ኤርሚያስ አወቀ ፣ ማምሻውን ጭምር አምሽቶ እየሰራ ነበር። ከምሽቱ 8 ፒ ኤም አካባቢ ሮዳስ ተክሉ ሱቁ ድረስ መጣች።
የፖሊስ ሪፖርት እንደሚያሳየው ሮዳስ ሱቁ ድረስ ከመጣች በኋላ ጭቅጭቅ ተጀመረ። እሱ እንድትወጣለት ቢጠይቃትም አልወጣችም። ይልቁኑ በእጇ ሽጉጥ ይዛ ስለነበር ፣ ስልኩን አንስቶ 911 ደወለ፣ ስልኩን ላነሳችው ኦፕሬተር “አንዲት ሴት ሱቄ ድረስ መጥታ ልትገለኝ እያስፈራራችኝ ነው፣ መሳሪያ ይዛለች .. እያለ ገና ተናግሮ ሳይጨርስ ስልኩ ተቋረጠ። ከዚያ በኋላ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች የጥይት ድምጽ መስማታቸውን ይናገራሉ።
ፖሊስ ካለበት፣ ነገሩን የሰሙም በጸጉር ቤቱ አካባቢ ሲደርሱ ኤርሚያስ በደም ተነክሮ ወድቋል፣ ወዲያው ወደ ሆስፒታል ተወሰደ ፣ ሆስፒታል ሲደርስም ህይወቱ አለፈ። በወቅቱ አንዲት ሴት ከቤቱ ወጥታ ስትሄድ አይተናል ከሚል ጥቆማ ውጪ ማን ገደለው የሚለው ጥያቄ እንቆቅልሽ ሆነ።
በማግስቱ ፌብሩዋሪ 6 ግን ፖሊስ ሮዳስ ተክሉ የተባለችና የቀድሞ ፍቅረኛው ነች የተባለች ሴት በጥርጣሬ መያዙን አስታወቀ። እሷም ወደ እስር ቤት ተወሰደች። ኤርሚያስም የፖሊስ ምርመራ ከታወቀና ዶክተሮች የሞቱን መንስኤ ካስታወቁ በኋላ ፌብሩዋሪ 11 ቀን በርካታ የአትላንታ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በጸጉር ቤቱ ደጃፍ የሻማ ማብራት ሰነ ስር ዓት ተካሄደ፣ በማግስቱ ፌብሩዋሪ 12 ጸሎተ ፍትሃት ከተደረገለት በኋላ አገር ቤት ተወስዶ እንዲቀበር በተያዘለት ፕሮግራም ይሄዳል ሲባል ፣ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ ያስፈልገኛል በማለቱ እስከ ፌብሩዋሪ 24 ሳይላክ ቆየ። ፌብሩዋሪ 24 ቀን ግን አስክሬኑ ወደ አገር ቤት ለቀብር ተላከ።
ከዚያ በኋላ ዜናው በአድማስ ሬዲዮም ሆነ አትላንታ ባለው ድንቅ መጽሔት ከወጣ በኋላ በወቅቱ የወጣት ሮዳስ ተክሉ ቤተሰቦች “እሷ በግድያው የለችበትም፣ ይህንን ድርጊት እሷ ትፈጽማለች ብሎ ማሰብ ትክክል አይደለም” ሲሉ ተናግረው ነበር። ሆነም ቀረ ላለፉት አራት ዓመታት ነገሩ ከፍርድ ቤት እስር ቤት ፣ ከ እስር ቤት ፍርድ ቤት ሲንከባለል ቆየ፣ የ ኤርሚያስ አወቀ የቅርብ ቤተሰብ የሆኑት አቶ ላቀው ለአድማስ ሬዲዮ እንደገለጹት በመካከል ተጠርጣሪዋ ልጅ፣ በጠበቆቿ አማካኝነት “አእምሮዋ ትክክል አይደለምና ለፍርድ ልትቀርብ አይገባም” ብለው ሲከራከሩ የቆዩ ሲሆን፣ ዳኞቹም የ አ ዕምሮዋ ነገር በሃኪሞች እንዲታይ ፈቅደው ቆይተዋል። በኋላ ግን ችሎት መቆም እንደምትችል በመታመኑ ፣ ጉዳዩ በከሳሽ አቃቤ ህግ እና በተከሳሽ ሮዳስ ተክሉ ጠበቆች መካከል ክርክሩ ቀጥሎ አራት ዓመት ከፈጀ። እንደ አቶ ላቀው ገለጻ ፣ በመጨረሻ ላይ ሮዳስ ወንጀሉን መፈጸሟን እንድታምን ተጠይቃ “አዎ ፈጽሜያለሁ፣ ነገር ግን በደም ፍላትና ሳላስበው ያደረኩት ነው” ስትል በማመኗ ዳኛዋ 25 ዓመት ጽኑ እስራት ፈርደውባታል። ምናልባት ጥፋቷን ባታምን እና ነገሩ በክርክሩ ብትሸነፍ የሞት ፍርድ ሊጠብቃት ይችልም ነበር ብለዋል።
ዳኛዋ በፍርድ ውሳኔያቸው እንደገለጹት “ ኤርሚያስ ገበየሁን በ 10 ጥይት መግደል ሳይታሰብ፣ ባጋጣሚ የተደረገ አይደለም” ሲሉ ውሳኔያቸውን አጽንተዋል።
በተያያዘ ሁኔታ ሮዳስ ተክሉ እዚያው እስር ቤት እያለች አንዲት ሴት ልጅ መውለዷም ታውቋል። የወለደችው ግሬዲ ሆስፒታል በፖሊስ ታጅባ ሄዳ ሲሆን፣ ባሁኑ ሰአት ህጻኗን አንዲት ነርስ እዚያው ግሬዲ እያሳደገቻት መሆኑ ሲታወቅ፣ የህጻኗን አባት በተመለከተ ዳኛዋ “የቀረበልኝ የዲ ኤን ኤ ምርመራ ስለሌለ፣ በልጅቷ አባት ጉዳይ የምሰጠው አስተያየት የለም” ሲሉ መናገራቸውም ታውቋል። (ምንጭ አድማስ ሬዲዮ አትላንታ)

Racist Videos - The Funny Networks _ The Funny Networks


Tuesday, May 28, 2013

ኢትዮጵያ 290 ሚሊዮን ብር ያወጣችበትን ግዙፍ የስፖርት ማዕከል አስገንብታ ዛሬ አስመርቃለች::

የኢትዮጵያ ሁለገብ የወጣቶች  ስፖርት አካዳሚ ዛሬ  በይፋ ተመረቀ።
አካዳሚውን በይፋ የመረቁት ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ እንዳሉት ፥ የሀገራችን ስፖርት ቀደም ሲል በአብዛኛው በግል ጥረትና ተነሳሽነት እንዲሁም በልምድ በመታገዝ ውጤት እንዲመዘገብ ረድቷል ።
ይሁንና ስፖርቱ ከሚጠይቀው ጥልቅና ሳይንሳዊ መሰረት ካለው አሰለጣጠን አንጻር የማሰልጠኛ ማእከሉ መከፈት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያመለከቱት።
አቶ ሀይለማርያም በንግግራቸው  የስፖርት ልማት የሰው ሀብት ልማታችን ዋናው አካል ሲሆን ፥ የአገሪቱ የስፖርት እድገትን የሚለካውም በአለም አቀፍ የስፖርት መድረክ በሚመዘገብ ውጤት ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ህብረተሰቡ ስፖርትን ለአካልና ለአእምሮ ጤንነት ማረጋገጫነት በስፋት ሲጠቀምበት ነው ብለዋል።
ከስድስት ዓመት በፊት ግንባታው የተጀመረው ይህ አካዳሚው ከ290 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል ተብሏል።
አካዳሚው በውስጡ ስታዲየም ፣ ጂምናዚየም ፣ የመማሪና የመኝታ ክፍሎች ፣አለም አቀፍ ደረጃን ያሟላ የመዋኛ ገንዳ  ያሟላ ሲሆን ፥ ለአገሪቱ የስፖርት እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል ።
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችም አካዳሚውን ጎብኝተዋል ።

ከረሃብ ለመዳን ጥንዚዛና ምስጥ፣ አንበጣና ጉንዳን ብሉ UN: Eat more insects to fight hunger

ተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ዩኤን) ባለፈው ሳምንት ከሮም ከተማ ለአለማችን ረሃብተኞች አንድ ምክርና የምስራች ወሬ አሰራጭቷል። የምስራች ወሬው፣ “እነ ጥንዚዛን በመመገብ ከረሃብ መገላገል ይቻላል” የሚል ነው። በደግነት የለገሰን ምክር ደግሞ፣ ከረሃብ ለመዳን “ነፍሳትን ብሉ” ይላል። ዩኤን ይህን “ምክርና የምስራች” በይፋ ለመላው አለም ያበሰረው፣ የአለም ምግብና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) ባዘጋጀው ባለ 200 ገፅ ሰነድ አማካኝነት ነው። የሰነዱ ርዕስ እንዲህ ይላል፣ Edible insects፡ Future prospects for food and feed security። እነ ጉንዳን፣ የመጪው ዘመን የምግብ ዋስት ተስፋዎቻችን እንደሆኑ የሚሰብክ ሰነድ ነው። “ረሃብተኛ ሆኖ ለብዙ አመታት በተመፅዋችነት መቆየት፣ መጨረሻው ውርደት ሆነ? ‘ጥንዚዛ ብላ!’ የሚል የስላቅ ምላሽ የምንሰማበት ደረጃ ላይ ደረስን?” የሚል ጥያቄ የሚፈጠርባቸው የድሃ አገር ሰዎች መኖራቸው የማይቀር ነው። በእርግጥም፣ በርካታ አለማቀፍ የሚዲያ ተቋማት፣ ዜናውን የዘገቡት በስላቅ መንፈስ ነው።
“ዩኤን ለአለማችን ረሃብተኞች አንድ ምክር አለው - በራሪ ነፍሳትን መብላት…” በማለት ነው ያሁ-ኒውስ ዘገባውን የሚጀምረው። የአሶሼትድ ፕሬስ ዘገባም ተመሳሳይ ነው። “የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ረሃብን፣ የአለም ሙቀትንና ብክለትን ለመዋጋት አዳዲስ መሳሪያዎችን ታጥቋል” በማለት የሚጀምረው የአሶሼትድ ፕሬስ ዜና፣ የዩኤን መሳሪያዎችን ለማየት ከፈለግን ሩቅ መሄድ እንደማይኖርብን ይገልፃል። አካበቢያችንን ብንቃኝ በቂ ነው። የዩኤን “ዘመናዊ” መሳሪያዎች፣ በሄድንበት ቦታ ሁሉ በዙሪያችን የሚያንዣብቡና አፍንጫችን ስር ሳይቀር “በረራ” የሚያዘወትሩ ናቸው። ይህንን የስላቅ አገላለፅ በማስቀደም አሶሼትድ ፕሬስ ዘገባውን ሲቀጥል… በዩኤን እምነት፣ የአለም ረሃብተኞች የወደፊት ተስፋ በራሪ ነፍሳትን መመገብ እንደሆነ ይገልጻል።
በዩኤን ስር፣ ለረሃብተኞች የእርዳታ እህል በማጓጓዝ የሚታወቀው ፋኦ፣ በራሪ ነፍሳት ለመብል የሚስማሙ መሆናቸውን ሲያስረዳ “በራሪ ነፍሳት በፕሮቲን የበለፀጉ ናቸው” ብሏል። እናም፣ ዩኤን እና ፋኦ፣ ረሃብን ለመከላከል ተስፋቸውን የጣሉት በበራሪ ነፍሳት ላይ ነው። ግን የነፍሳት ጥቅም፣ ከምግብነትም የላቀ እንደሆነ የገለፁት ዩኤንና ፋኦ፣ ለአካባቢ ጥበቃ ግሩም መፍትሄ ይሆንልናል ብለዋል። በሬና ላም፣ በግና ፍየል ብዙ ሳር እየበሉ አካባቢን ያራቁታሉ፤ የተለያዩ የጋዝ አይነቶችን እያመነጩ አካባቢን ይበክላሉ ይላል ዩኤን። ስለዚህ፣ አካባቢን የማያራቁቱና የማይበክሉ በራሪ ነፍሳት፣ ቀለባችሁ ይሁኑ በማለት ምክሩን ለግሷል። 1900 ያህል የነፍሳት ዝርያዎች ለምግብነት ተስማሚ መሆናቸውን ዩኤን ጠቅሶ፣ ጉንዳን፣ ጥንዚዛ፣ አንበጣ፣ ዝንብ፣ ምስጥ፣ አባጨጓሬ እንዲሁም ሌሎች በራሪና ተስፈንጣሪ ነፍሳትን በምሳሌነት ዘርዝሯል። የዩኤን እና የፋኦ መግለጫ፣ በረሃብተኞች ላይ የተሰነዘረ ስላቅ ይመስላል ብለው የሚቆጡ መኖራቸው አይቀርም።

ነገር ግን ብዙም አይገርምም። እድሜ ልክ እርዳታ እየጠበቀ የሚኖር ረሃብተኛ፣ ውሎ አድሮ “ከራበህ ጥንዚዛ ብላ!” የሚል ምላሽ ማግኘቱ የማይቀር ነው። ውርደት ሊመስል ይችላል። ከሁሉም የከፋ ውርደት ግን፣ ራስን ለመቻል አለመጣርና አለመቻል ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፣ “ጥንዚዛና ዝንብ ተመገቡ” የሚለው ዘመቻ፣ በየጊዜው የሚያገረሽ የዩኤን እብደት ይመስላል። እናም፣ ለጊዜው ከተወራለት በኋላ፣ ወረቱ ሲያልቅ ተረስቶ ይቀራል ብለን እንገምት ይሆናል። ግን በዋዛ አይረሳም። ባለፉት 10 አመታት ለዘመቻው በጀት ሲመደብለት ቆይቷል። አሁንም ይመደብለታል። ለምን ቢባል… ዩኤንና ፋኦ ምላሽ አላቸው -ነፍሳትን የመመገብ ልምድ እንዲስፋፋና የህዝቡን ግንዛቤ ለማሳደግ (awareness raising) በጀት ይመድባሉ።
ሰነዶችን ለማዘጋጀትና ለማሰራጨት፣ በአባል አገራት የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማካሄድ፣ አዳዲስ ህጎችንም ለማዘጋጀት ገንዘብ ያወጣሉ። አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት፣ በራሪ ነፍሳትን የማርባት ሥራ እንዲጀምሩም ይደጉማሉ። ዩኤንና ፋኦ፣ ይሄን ሁሉ የሚያደርጉት፣ “ረሃብተኞችን ለመደገፍ” ነው። በሌላ አነጋገር፣ ዩኤንና ፋኦ፣ ብዙ ገንዘብና ሃብት ሳያባክኑበት በፊት፣ “የበራሪ ነፍሳት ፕሮጀክታቸውን” በአጭር ጊዜ እንደዘበት ይረሱታል ተብሎ አይጠበቅም።

Monday, May 27, 2013

“ሰዎች እንብላ የሚሉት ከልባቸው ነው ወይስ እንደው ለነገሩ ያህል?” የዳሰሳ ጥናት ውጤት

ሰሞኑን ማህበረሰባዊ እሴቶቻችን ከሚባሉት በአንዱ ላይ የብድግ ብድግ ናሙና ወስጄ ጥናት እካሄድኩ ነበር፡፡ የጥናቱ ትኩረት የ “እንብላ ባህላችን” ሲሆን ጥናቱን ለማካሄድ ያስፈለገበት ምክንያትም እውነት ይህ ባህል አለ ወይስ ብዙዎች እንደሚሉት “ጎጂ ባህል” ከሚባሉት ተርታ ተሰልፏል የሚለውን እና አለ ከተባለም ሰዎች እንብላ የሚሉት ለአፋቸው ያህል ነው ወይስ ከልብ የሚለውን የምርምር ጥያቄ ለመመለስ ነበር፡፡
የጥናቱ ዘዴ ደግሞ ሰዎች ምግብ በሚመገቡባቸው አካባቢዎች ላይ ማንዣበብና ማፍጠጥ ወይንም ኦብዘርቬሽን ማካሄድ ነበር፡፡ ለጥናቱ  በናሙናነት ከተወሰዱ ተመጋቢዎች መሀል ታዲያ 70 በመቶ ያህሉ “አንብላ” አላሉም፡፡ ስለዚህ አብዛኞቹ “አንብላ ጎጂ ባህል ነው”  ከሚሉት ተርታ ይመደባሉ ማለት ነው የሚል መላ ምት ላይ መድረስ ተችሏል፡፡
ቀሪዎቹ 30 በመቶ ደግሞ ለአፋቸው ያህል እንብላ ቢሉም የዚህ ጥናት ባለቤት ግብዣቸውን ተቀብሎ ለተጨማሪ ምርምር ባደረገው ጥረት ያገኘው ውጤት አስደንጋጭ ነው፡፡ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት “አንብላ ባዮች” ከምግብ ሳህናቸው ላይ አንድ ሁለት ጠብደል ጠብደል ጉርሻዎች ብድግ ብድግ ሲደረጉ ከፊታቸው ላይ የነበረው ፈገግታ ሁላ በአንድ ጊዜ ድራሹ ይጠፋና በምልክቱ አይናቸው ማጉረጥረጥ ጀምሯል፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም “ ቀልድ አታውቅም እንዴ” የሚለውን ጥያቄ ከማንሳት ጀምሮ “ ፍሬንድ አንተም እዘዛ” በማለት የሰው በልቶ አያድሩም ተኝቶ አይነት አቋም ሲያራምዱ ተስተውሏል፡፡ እጃቸውን እንደመታጠብ ብለው በመጥፋትም የምግቡን ዋጋ አጥኚው ከፍሎ እንዲወጣ ያደረጉም አልታጡም፡፡
ይህ ጥናት ለናሙናነት የተጠቀመባቸው ሰዎች ቁጥር አናሳና አካባቢያዊ ስብጥሩም ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ የሀገሪቱን ገፅታ ወካይ ነው ማለት አያስደፍርም፡፡ ይሁንና ለሌሎች የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪዎች ጥናት መነሻ ሊሆን እንደሚችል አጥኚው ይተማመናል፡፡
ጥያቄው አሁንም ክፍት ነው፤   “ሰዎች እንብላ የሚሉት ከልባቸው ነው ወይስ እንደው ለነገሩ ያህል?”

በተጠረጠሩባቸው የሙስና ወንጀሎች የታሰሩት አቶ መላኩ ፈንታ መታመማቸው ተገለጸ

46 ኪሎ ግራም ወርቅ ይዘው 100 ሺሕ ብር የተሸለሙት ተጠርጣሪ ልታሰር አይገባም አሉ

‹‹እኔ በመታሰሬ መንግሥትም ፕሮጀክቶችም ይበደላሉ›› አርክቴክት በእግዚአብሔር አለበል

‹‹ለልጄ ወተት መግዣ ብቻ አንድ ሺሕ ብር ይሰጥልኝ››  የበምጫ ትራንዚት ባለቤት 
በተጠረጠሩባቸው የተለያዩ የሙስና ወንጀሎች ግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ በቁጥጥር ሥር ውለው በእስር ላይ የሚገኙት በሚኒስትርነት ማዕረግ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ መታመማቸውን ጠበቃቸው ግንቦት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው አስታወቁ፡፡

ጠበቃው አቶ መላኩ በአስቸኳይ ሕክምና እንዲደረግላቸው ጠይቀው፣ “እኚህ ሰው በጠና ስለታመሙ የታሪክ ተወቃሽ እንዳንሆን፤” ብለዋል፡፡

የአቶ መላኩን ጤንነት በሚመለከት ጠበቃው በዝርዝር ጠይቀው የሕመማቸው ዓይነትና ደረጃ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ባይረዱም፣ መልካቸው ቢጫ ሆኖ እንዳዩዋቸው ገልጸዋል፡፡ ለምን እንዳላነጋገሩዋቸው ሲጠየቁ በቂ ጊዜ እንዳልነበራቸው የገለጹት ጠበቃው ከእሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውን፣ ነገር ግን ሆስፒታል ይሂዱ ወይም አይሂዱ አለማወቃቸውንም አስረድተዋል፡፡

በአጃቢ ሆነው ሕክምና እንዲያገኙ ጠበቃው ላነሱት ጥያቄ፣ ስለመታመማቸው የሚገልጽ ማስረጃ ከክሊኒክ ወይም ከሆስፒታል እንደሚያስፈልግ በመግለጽ ያለማስረጃ ትዕዛዝ መስጠት እንደማይቻል ፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡

አቶ መላኩ መንግሥት የሚያውቀውና በአገር ውስጥ ሕክምና የማይድን ሕመም እንዳለባቸውና በውጭ አገር እየታከሙ እንደነበር፣ ለፍርድ ቤቱ ራሳቸውና ጠበቃቸው ማስረዳታቸው የሚታወስ ነው፡፡

በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ለግንቦት 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ቀጥሮት የነበረውን የእነ አምባውሰገድ አብርሃ የምርመራ መዝገብን ተመልክቷል፡፡ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የናዝሬትና ሚሌ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆችን ጨምሮ 11 ተጠርጣሪዎች ቀረጥ በማጭበርበር፣ ክስ በማቋረጥ፣ የኮንትሮባንድ ዕቃ ሳይፈተሽ እንዲያልፍ በማድረግና ተገቢ ያልሆነ ሀብት በማከማቸት የሙስና ወንጀል መጠርጠራቸውን፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎትና ለተጠርጣሪዎቹ አስረድቷል፡፡

ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚያስችለውን የሰነድና የሰው ማስረጃዎችን መሰብሰቡንና ቃል መቀበል መጀመሩን የገለጸው መርማሪ ቡድኑ ቀሪ ሰነድ ማሰባሰብ፣ የምስክሮችን ቃል መቀበልና የተሰበሰቡ ሰነዶችን የመለየት ሥራ እንደሚቀረው በመግለጽ፣ ፍርድ ቤቱ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡

አቶ አምባውሰገድ የልብ ሕመምተኛ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት፣ መርማሪ ቡድኑ በብርበራ የሚፈልገውን ማስረጃ በመውሰዱና እሳቸውም ሊያጠፉት የሚችሉት ማስረጃ ስለሌለ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡ አቶ ቃለአብ ዘርአብሩክም የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡ የናዝሬት ጉምሩክ ሥራ አስኪያጅ አቶ ያዴሳ ሚደቅሳ ሥራ ከማስተባበር ውጭ ጣልቃ ገብተው የተጠረጠሩበትን ወንጀል እንዳልፈጸሙና ከተያዙ ሰባት ቀናት እንዳለፋቸው በማሳወቅ፣ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜን ተቃውመው የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል፡፡

በሕገወጥ መንገድ በሕገወጦች ተይዞ የነበረን 46 ኪሎ ግራም ወርቅ በመያዝ ከመንግሥት ምስጋናና 100 ሺሕ ብር ሽልማት ማግኘታቸውን የገለጹት የባለሥልጣኑ ባልደረባ አቶ እሸቱ ግረፍ ናቸው፡፡ በተመሰገኑበት ሥራ ሌላ ነገር ሊሠሩ እንደማይችሉ፣ መርማሪዎችም አሉ የተባሉ ሰነዶችን በብርበራ የወሰዱ በመሆናቸውና የሚቀር ነገር የሌለ በመሆኑ ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡

አቶ ጌታሁን ቱጂ፣ አቶ መላኩ ግርማ፣ አቶ አስፋው ሥዩም፣ አቶ ጌታነህ ግደይና አቶ ዮሴፍ አዳዊ የተባሉ የባለሥልጣኑ ሠራተኞች የተጠረጠሩበት ጉዳይ መርማሪ ቡድኑ ካለው ጋር የማይገናኝና የሥራ ድርሻቸውም የማይገናኝ መሆኑን በማስረዳት፣ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

አርክቴክት በእግዚአብሔር አለበል መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ ያስረዳው የመጠርጠሪያ ድርጊት ከእሳቸው ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር እንደሌለ ገልጸው፣ የመንግሥትና የግል የሆኑ ከ60 በላይ ፕሮጀክቶች እንዳሏቸው በማስረዳት፣ ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ ችግር እያጋጠማቸው በመሆኑ ዋስትና እንዲከበርላቸው ደጋግመው ጠይቀዋል፡፡

የባህር ዳርና የጎንደር ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን እንደሚያማክሩ የተናገሩት አቶ በእግዚአብሔር፣ ከ131 በላይ ደረጃ አንድ ተቋራጮችን ከማማከራቸውም በተጨማሪ፣ ክፍያ እንዲፈጸምላቸው እሳቸው የሥራውን ጥራት ማረጋገጥ ስላለባቸው ሥራ እየቆመ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ መንግሥትም ሆነ ሠራተኞች እንደሚበደሉ የገለጹት አርክቴክቱ፣ ሰነዶችን በሚመለከት ሁሉም ሰነዶች በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሚገኙ በመሆናቸው ሊሰውሩና ሊያጠፉ የሚችሉበት አጋጣሚ ስለሌለ፣ እሳቸውን አስሮ ማቆየቱ ምንም ጥቅም እንደሌለው ገልጸዋል፡፡

ሥራ ከሚበላሽና ሠራተኛ ከሚበተን ፍርድ ቤቱ ውክልና ለሌላ ሰው የሚሰጡበትን መንገድ እንዲያመቻችላቸው የጠየቁት አቶ በእግዚአብሔር፣ ከተጠረጠሩበት ወንጀል ጋር ግንኙነት የሌላቸው ሰነዶች እንደተያዙባቸው በመግለጽ እንዲለቀቁላቸው ጠይቀዋል፡፡ ክፍያ የሚፈጽሙት በየዕለቱ ቢሆንም ማህተምና ቼክ ስለተወሰደባቸው የሠራተኞች ደመወዝ፣ የገቢ ግብርና የጡረታ ክፍያ መክፈል አለመቻላቸውንም አስረድተዋል፡፡ አገር እያለሙ መሆኑን በመናገር በዋስ ሆነው ሥራቸውን እየሠሩ ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ የጠየቁት አቶ በእግዚአብሔር፣ በመርማሪዎች እንደተነገራቸው ‹‹ሰው ታውቃለህ›› በሚል ብቻ መታሰራቸውን አስረድተዋል፡፡

የችሎቱን ታዳሚዎች ያሳዘነና ከንፈር ከማስመጠጥ አልፎ እንባ እስከ ማፍሰስ ያደረሳቸው የበምጫ ትራንዚት ባለቤት አቶ ዘለቀ ልየው ለፍርድ ቤቱ ያቀረቡት አቤቱታ ነው፡፡ አቶ ዘለቀ የጉምሩክ አስተላላፊ ትራንዚተር መሆናቸውን በጠበቃቸው በኩል ገልጸው፣ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ ስድስት ቀናት ቢሆናቸውም እስከ ግንቦት 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ቃላቸውን አለመስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 19 (4) መሠረት አንድ በቁጥጥር ሥር የዋለ ዜጋ ቃሉን እንዴት መስጠት እንዳለበት የተቀመጠው ድንጋጌም መጣሱን አመልክተዋል፡፡

ቢሯቸው መታሸጉንና በቢሯቸው ውስጥ ያለው ሰነድ ሳይለይ የሚያስፈልገውም ሆነ የማያስፈልገው ሰነድ አንድ ላይ በመታሸጉ፣ በእሳቸውም ላይ ሆነ በመንግሥት ላይ ጉዳት እንደሚያመጣ ተናግረዋል፡፡ ኤልሲ የተከፈተባቸው፣ ሥራ የተጀመረላቸውና ያልተጀመረላቸው ነጋዴዎች ብሔራዊ ባንክ ሄደው እንዳይጠይቁ መቸገራቸውን፣ ወደ አገር ውስጥ ያልገቡ ዕቃዎች ሰነዶች በሙሉ ስለተቆለፈባቸው ለወደብ የሚከፈለው በዶላር መሆኑንና ተጎጂው አገር ጭምር መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የታሸገባቸው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመሆኑ ድርጊቱ ሕገወጥ መሆኑን በመጠቆም እንዲከፈትላቸው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠበቃቸው ጠይቀዋል፡፡

ሕፃን ልጃቸው እሳቸው ሲያዙ ተመልክቶ እስካሁን በመሳቀቅ ላይ በመሆኑ እንዲያገኛቸው እንዲታዘዝላቸውም አመልክተዋል፡፡ ተጠርጣሪው እንዲናገሩ ጠይቀው ሲፈቀድላቸው እምባ እየተናነቃቸው፣ ‹‹እቤቴ አንድም ብር እንኳን ሳይተው መርማሪዎቹ ሁሉንም ገንዘብ ወስደውታል፡፡ የምጠይቀው ለልጄ ወተት መግዣ ብቻ አንድ ሺሕ ብር እንዲሰጡልኝ ነው፤›› ካሉ በኋላ መናገር አልቻሉም፡፡ የችሎቱ ታዳሚዎችም በተጠርጣሪው ንግግር የተወሰኑት ሲያለቅሱ የተወሰኑት ተክዘው ተስተውሏል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ከተናገሩ በኋላ ምላሽ እንዲሰጥ በፍርድ ቤቱ የታዘዘው መርማሪ ቡድኑ፣ አንዳንድ ጥያቄዎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች በመሆናቸው በቢሮ በኩል እንደሚፈቱ ተናግሯል፡፡ የዋስትና መብት ጥያቄን በሚመለከት ጉዳዩ ውስብስብ መሆኑን በመጥቀስ ቢለቀቁ ሰነድ፣ ምስክርና ሌሎች ማስረጃዎችን ሊያጠፉበት እንደሚችሉ በመግለጽ፣ ጥያቄያቸው ውድቅ እንዲደረግና የ14 ቀናት ጊዜ ምርመራ እንደፈቀድለት በድጋሚ ጠይቋል፡፡

ሌላው ፍርድ ቤቱ ችሎቱ ከመጀመሩ በፊት ለመርማሪ ቡድኑ ያነሳው ጥያቄ፣ ተጠርጣሪዎች ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበር ያዘዘውን ትዕዛዝ ኮሚሽኑ ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ቢታዘዝም፣ ለምን ሳይፈጽም እንደቀረ እንዲያብራራ ነበር፡፡ ኮሚሽኑ የተጠርጣሪዎችን ሕገ መንግሥታዊ መብት መከበር አለመከበር የመከታተል ግዴታ እንዳለበትም ፍርድ ቤቱ አስታውቋል፡፡

መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጠው ተጠርጣሪዎች በስድስት መዝገብ ተከፋፍለው የሚቀርቡ ናቸው፡፡ ሥራው ውስብስብ በመሆኑና ለብርበራ ተጠርጣሪው ጭምር የሚወጣበት ጊዜ በመኖሩ፣ ከሕግ አማካሪ ጋር የሚገናኙበትን ጊዜ ረቡዕና ዓርብ መደረጉን፣ የጊዜ ቀጠሮ ያላቸውንም በመለየት ከሕግ አማካሪዎቻቸው ጋር እያገናኘ መሆኑን ገልጿል፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መርማሪ ቡድኑ እንዳብራራው ጉዳዩ ውስብስብ መሆኑን ፍርድ ቤቱ መገንዘቡን ገልጾ፣ የተመርማሪዎች ዋስትና ጥያቄን ውድቅ ማድረጉን በማስረዳት ለመርማሪ ቡድኑ የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ በመፍቀድ ለግንቦት 26 ቀን 2005 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን ማለትም በቤተሰብ፣ በሕግ አማካሪና በሐኪም የመጎብኘትና የማግኘት መብታቸውን በሚመለከት የማዕከላዊ እስረኛ ኃላፊ ኮማንደር ብርሃኑ አበበ ቀርበው እንዲያስረዱ በታዘዘው መሠረት ኮማንደሩ ግንቦት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. አስረድተዋል፡፡

ኮማንደር ብርሃኑ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ሁሉም የሕግ አማካሪዎች ደንበኞቻቸውን አግኝተዋል፡፡ በችሎት የተገኙም የሕግ አማካሪዎች ከአቶ ከተማ ከበደ ጠበቃ በስተቀር ሁሉም መገኘታቸውን መስክረዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎችና የሕግ አማካሪዎች የተገናኙበት ቀን ሪፖርት እንዲደረግና አቶ ከተማ ከበደን በሚመለከትም ጥብቅ ትዕዛዝ በማስተላለፍ ለግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ሪፖርት እንዲያደርጉ በድጋሚ አዟል፡፡     


Ethiopian Reporter
 

Wednesday, May 22, 2013

ለ 40 ቀን 40 ለሊት እንጾማለን ብለው ሚስትን ለሞት ዳረጉ ልጆቹም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል

ያለምንም እህል እና ውሃ ጾምን ለ 40 ቀን 40 ለሊት እንጾማለን ብለው ጾማቸውን የጀመሩት የቤተሰብ አባላት ለከፍተኛ ጉዳት እና ለሞት መዳረጋቸውን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።
በጎተራ ኮንደሚኒየም ውስጥ ይኖሩ የነበሩት እነዚህ ሰዎች በሃገራችን እምነት አንጻር ጾም ጸሎትን እያደረግን አምላክን በጸሎት እናስባለን በማለት ጾማቸውን መጀመራቸው ተገልጾአል ።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ ያለው ባል እና ከጂማ ዩኒቨርሲቲ በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቀች ሲሆን ።

ባል በባህርዳር በክሊኒክ ይሰራ የነበር ሲሆን ሚስትም በዚሁ የሙያ ስራ ተሰማርታ ወደ  ባህርዳር ማቅናቷ እና የልጆቿን አባት በፍቅር ግንኙነት ጀምራ ወደ ትዳር አለም አብራው እንደዘለቀች እና ሁለት ልጆችን አፍርተው የ9 አመት እና የስድስት አመት ልጆችንም ማፍራታቸው  የሪፖርተራችን ያጠናቅራል ።

ከምግብ እና ከውሃ ተለይተው ለልጆቻቸው ብቻ በጣም ጥቂት ምግብን በመያዝ በቤታቸው ዘግተው ለቀናቶች ሰንብተዋል ።

ሂደቱ ለ25 ቀናት የተጓዘ ሲሆን ባለቤቷ እያበሰለ ለልጆቹ ከሚያቀርበው ምግብ ለራሱ በጥቂቱ የሚቀምስ ሲሆን ለባለቤቱ ሲሰጣት ግን ምንም አይነት ነገር መመገብ አለመቻሏን እና ምንም አያገባህም በማለት ምላሽ ታክል እንደነበር ዘገባው ያመለክታ.

ሆኖም ግን 40ኛ ቀኑ ከመድረሱ አራት ቀን በፊት የእናት የአፍጠረን መለወጥ ያየችው ህጻን ከወላጅ እናቷ ተለይታ  ከታናሽ እህቷ ጋር በሶፋ ላይ መተኛት መጀመሯን እና ከዚያም በመስኮት እራበን ድረሱልን እያለች መጮኋን እና የጎረቤት ልጅ መጥታ በበር ቀዳዳ በተሰጣት ቁልፍ ከፍታ በመግባት ፣ሁለቱ ህጻናቶች ቆዳቸው ተጣብቆ በምግብ ጉዳት ምክንያት ከስተው የተገኙ ሲሆን ባል እራሳቸውን በመሳት በሆስፒታል በህክምና ክትትል ላይ ናቸው ሚስትዬዋ ግን በህይወት ሊተርፉ አለመቻላቸውን ዘገባው አክሎ ጠቁሞአል.

 

Tuesday, May 21, 2013

በጣና ሃይቅ በደረሰ የጀልባ መገልበጥ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይዎት አለፈ

ትናንት ከቁንዝላ ወደ ደልጊ 102 ሰዎችን አሳፋሮ ሲጓዝ የነበረ ጀልባ በመግለበጡ እስካሁን አምስት ሰዎች መሞታቸውን የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ደልጊ መዳረሻ ስፍራ በግምት 150 ሜትር ርቀት ላይ  ፥ ተሳፋሪዎችን ለማውረድ ሲቃረብ  ጀልባው የመገልበጥ አደጋ እንደደረሰበትም ነው የዓይን እማኞች የተናገሩት።
የመምሪያው ሀላፊ ኮማንደር ዘመነ አመሸ ለባልደረባችን ኤልያስ ተክለወልድ እንደነገሩት ፥ የአደጋው መንስኤ እስካሁን በእርግጠኝነት ባይታወቅም  ፤ ተሳፋሪዎቹ ለመውረድ እየተዘጋጁ ሰለነበር በአንድ ስፍራ መከማቸታቸው የሚዛን መዛባት አስክትሎ ለአደጋው ምክንያት ሊሆን ይችላል ተብሏል።
ፋሲለደስ በመባል የምትጠራውን ጀልባ ሲያሽከረክር  የነበረው ካፒቴን በህይወት የተረፈ ሲሆን ፥ ለፖሊስ በሰጠው ቃልም ይህኑኑ አረጋግጧል ነው ያሉት።
በአሁኑ ወቅት ምናልባትም በህይወት የተረፈ ካለ እና ተጨማሪ አስከሬኖችን የማፈላለጉ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ይህ አይነቱ አስከፊ አደጋ ሲያጋጥም የመጀመሪያው ነው ያሉት ኮማንደር ዘመነ ፥ በቀጣይ ትክክለኛውን መረጃ በማጣራት ምክንያቱን ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን ብለዋል።
 (ኤፍ ቢ ሲ)

Monday, May 20, 2013

ቅዳሜ ኢትዮጵያ ከ ሱዳን ጋር ለምታደርገው ጨዋታ የተጫዋቾች ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ
ግንቦት 12 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ አፍሪካ ህብረት የተመሰረተበትን 50 ኛ አመት  ክብረ በአል ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያ ከሱዳን በምታደርገው ጨዋታ ላይ የሚካፈሉ ተጫዋቾችን ስም ዝርዝር የኢትዮጵያ  ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ይፋ አደረጉ ፡፡
በዚህም መሰረት የተመረጡት ተጫዋቾች ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ደጉ ደበበ ፣አበባው ቡጣቆ፣ቢያድግልኝ ኤልያስ፣አሉላ ግርማ፣ሽመልስ በቀለ ፣አዳነ ግርማ ፣ያሬድ ዝናቡ፣ዮናታን ብርሀነና ተስፋዬ አለባቸው ናቸው ፡፡
ከ ደደቢት ሲሳይ ባንጫ ፣ ስዩም ተስፋዬ ፣ብርሃኑ ቦጋለ፣አይናለም ሃይሉ፣አክሊሉ አየነው ፣አዲስ ህንጻ፣በሃይሉ አሰፋ ፣ጌታነህ ከበደ ፣ምን ያህል ተሾመ ፣ዘነበ ከበደ(አዩካ) ና ዳዊት ፍቃዱ ሲሆኑ ፥
ከ ኢትዮጵያ ቡና ጀማል ጣሰው፣አስቻለው ግርማ ፣ፖክ ጅምስ እና ኤፍሬም አሻሞ፥
ከ መብራት ሃይል አስራት መገርሳ እና መስፍን ወንድሙ፥
ከ መከላከያ ጥላሁን ወልዴ ፥
ከ ኢትዮጵያ መድህን ሳለሃዲን ባርጌቾ፥
ከ ሀዋሳ ከነማ ወንድሜነህ ዘሪሁን፥
ከ ሰበታ ከነማ ደረጀ አለሙ እና ከ ሲዳማ ቡና ደግሞ ሞገስ ታደሰ  ሆነዋል ፡፡
ተጫዋቾቹ ከነገው ግንቦት 13 ማለዳ ጀምሮ በ ፌዴሬሽኑ ጽህፈት ቤት ተገኝተው ሪፖርት እንዲያደርጉም  አሰልጣኙ ጥሪያቸውን አስተላለፈዋል፡፡

የግሉን ዘርፍ በሙስና ወንጀል ተጠያቂ የሚያደርግ አዋጅ ሊወጣ ነው

አዲስ አበባ ፣ግንቦት 10 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን የግሉን  ዘርፍ  በሙስና ወንጀል ተጠያቂ የሚያደርግ አዋጅ  ለመደንገግ በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ ከህብረተሰቡ እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ መክሯል።
አዋጁ ህዝባዊ ድርጅቶች ናቸው ተብለው በሚታሰቡ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች  በግል ኩባንያዎች  እና በአክሲዮን ማህበራት ውስጥ የሚፈፀሙ የሙስና የወንጀል ድርጊቶችን  ተጠያቂ የሚያደርግ አንቀፅ ተካቶበታል ።
ይህም የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ወይንም የአክሲዮን ማህበርን ወይንም የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን በሚያደራጅ ሰው ወይም ኮሚቴ በድርጅቱ ውስጥ በማስፈፀም ሂደት የህዝብ ሃብት እንዳይባክን ለመከላከልም የሚያስችል  ነው ተብሏል። 
በእነዚህ የህዝብ ድርጅቶች ውስጥ የተቀጠሩ ቋሚና ጊዜያዊ ተራ ሰራተኞችም ቢሆኑ በሙስና ወንጀል ውስጥ ከተገኙ ህጉ ተፈፃሚ ይሆንባቸዋል ።
በሚስጢር ሊጠበቁ የሚገቡ የካዝና የመጋዘን ወይም ውድ እቃ የሚቀመጥባቸው የመሳሰሉ ሳጥኖችን ቁልፎች ሆን ብሎ ወይንም በቸልተኝነት ለሌላ ሰው  አሳልፎ በመስጠት ድርጅቶች እንዲመዘበሩ ያደረጉ ሰራተኞችን ለመቅጣትም  በአዋጁ ጠንካራ ድንጋጌዎች እንዲካተቱበት ተደርጓል።
የአዋጁ መውጣትም በእነዚህ የህዝብ ድርጅቶች ላይ የሚታዩ ብልሹ አሰራሮችን በማስተካከል ህጋዊ መስመርን ተከትለው እንዲተዳደሩ ያግዛልም ተብሎ ታስቧል።
በ ታደሰ ብዙዓለም ።
       

ሶሪያውያን እናቶች በሴት ልጆቻቸው ላይ ጨክነዋል

በሶሪያ መላ የታጣለትን የእርስበርስ ጦርነት በመሸሽ ወደ ዮርዳኖስ የተሰደዱ እናቶች፣ ህይወት ፈተና ሆኖባቸው ሴት ልጆቻቸውን “ለጊዜያዊ ትዳር” እየሸጡ ነው፡፡ ስደተኛ ወላጆች በሴት ልጆቻቸው ላይ መጨከን እንደጀመሩ የዘገበው ሲኤስ፣ ኑሮን ለመግፋት የሚያስችላቸው ብቸኛ አማራጭ ሆኖ ያገኙት ሴት ልጆቻቸውን በሺዎች በሚቆጠሩ ዶላሮች ለጋብቻ መሸጥ ነው፡፡ ከዮርዳኖስም ሆነ በሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ጋብቻ ፈላጊ ወንዶች ለሴቷ ቤተሰቦች ገንዘብ የሚሰጡበት ባህል አለ፡፡ ይሄም ሆኖ ግን የሰሞኑ የዮርዳኖስ ስደተኛ ካምፖች “የጋብቻ ገበያ”፣ እርግጥም ወንዶች ሴቶችን ለዘላቂ ትዳር የሚገዙበት አይደለም፡፡ አብዛኛዎቹ “ትዳሮች” ከሳምንታት የዘለቀ ዕድሜ እንደማይኖራቸው የገለፀው ዘገባው፤ ይልቁንም “የወሲብ ገበያ” ሊባል የሚችል መሆኑን አስረድቷል፡፡
ይህንን የሴት ልጆች ሽያጭ ከሚያቀላጥፉትና ራሳቸውን “የጋብቻ ደላላ” ብለው ከሚጠሩት መካከል ሶሪያዊቷ ስደተኛ ኡም ማጄጅ አንዷ ናት፡፡ ኡም ማጄድ ከሰሞኑ እየጦፈ በመጣው የስደተኛ ልጃገረዶች ሽያጭ ገበያ ፋታ አጥታለች፡፡ የሞባይል ስልኳ በገዢዎች ጥሪ ተጨናንቋል፡፡ ኡም ማጄድ ከወላጆች ጋር በመነጋገር ለሽያጭ ከምታቀርባቸው ሴቶች ጠቀም ያለ ኮሚሽን ታገኛለች፡፡ ክብረ ንጽህናዋ ያልተገረሰሰ ልጃገረድ በሰሞኑ ገበያ እስከ 5ሺህ ዶላር ታወጣለች፡፡ አያ የተባለችዋ የ17 አመቷ ሶሪያዊት ስደተኛ አያ፤ ከቤተሰቦቿ ጋር በስደት ወደ ዮርዳኖስ ከመጣች አንድ አመት ያህል ሆኗታል፡፡
ይሄም ሆኖ ግን የስደት ኑሮ ለእሷም ሆነ ለቤተሰቧ አሳር ሲሆንባቸው፣ ብቸኛውን አማራጭ ለመውሰድ ተገደዱ፡፡ አያ ለ70 አመት ሳኡዲ አረቢያዊ “ትዳር ፈላጊ” ሽማግሌ በ3ሺህ 500 ዶላር ተሸጠች፡፡ ትዳር ፈላጊው ሽማግሌ ግን ከሙሽሪት አያ ጋር የመሰረተውን ትዳር ለማፍረስ የፈጀበት የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ “ከእሱ ጋር ያሳለፍኩት አንድ አመት ልክ እንደ አስፈሪ ቅዠት ነበር፡፡ ግማሹን ወር በመራር ለቅሶ ነው ያሳለፍኩት፡፡ ከቤተሰቦቼ ጋር እንድገናኝና እንዳወራ አይፈቅድልኝም ነበር፡፡ ምርጫ አልነበረኝምና በሰቀቀን ነበር የምኖረው” ብላለች - አያ ስለ ሽያጩ ትዳሯ ስትናገር፡፡
እንዲህ ለጋ ልጃገረዶችን ለገበያ አቅርባ የምታሻሽጠው ኡም ማጄድ እየሰራችው ስላለችው ነገር ሃፍረትም ሆነ ፀፀት አይሰማትም፡፡ “መኖር የምችልበት ብቸኛው መንገድ ይህ “ስራ” ነው፡፡ ሶሪያውያን ስደተኞች በዮርዳኖስ ሌላ ስራ መስራትና ገቢ ማግኘት አንችልም፡፡ ስለዚህ ምን ማድረግ እንችላለን?...እንስረቅ?...እንግደል?” ትላለች ማጄድ፡፡ የሚገርመው ግን “አንቺስ የ13 አመት ልጃገረድ ልጅሽን ለመሸጥ ትፈቅጃለሽ?” ለሚለው የጋዜጠኞች ጥያቄ የሰጠችው መልስ ነው፡፡ “በፍፁም አላደርገውም!... ልጆቼን ከምሸጥ አይኖቼን አውጥቼ ብሸጣቸው እመርጣለሁ!” ነው ያለችው ማጄድ፡፡