Search

Monday, September 16, 2013

በአንበሳ ግቢ አንበሳ ሰው ገደለ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 6 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በአንበሳ ግቢ የአንበሶች ማቆያ ማዕከል ውስጥ ዛሬ ከጠዋቱ 1:30 ላይ የሞት አደጋ ተከሰተ።

አደጋው የተከሰተው አቶ አበራ ሲሳይ የተባሉት የአንበሶቹ መጋቢ የአንበሶቹን ማደሪያ እያጸዱ ባሉበት ወቅት ከጥንቃቄ ጉድለት ባልተዘጋው በር የገባው ቀነኒሳ የተባለው አንበሳ ለህልፈተ ህይወት ዳርጓቸዋል።

የግለሰቡን ህይወት ለማትረፍ በወቅቱ በስራ ላይ የነበሩ የግቢው ሰራተኞች ጥረት ቢያደርጉም ሳይሳካ መቅረቱ ለማወቅ ተችሏል።

የሟች አስከሬን ከአንበሶቹ ማደሪያ ወጥቶ ወደ ምኒሊክ ሆስፒታል ተወስዷል።

ተመሳሳይ አደጋ ከዚህ በፊት በ19 89 ዓ.ም መከሰቱ የሚታወስ ነው።

Soucre : FanaBC

No comments:

Post a Comment