Search

Friday, July 31, 2015

“ዘፈኑን እየተውኩ ወደ ዝማሬው ዓለም እየገባሁ ነው” – ድምፃዊት(ዘማሪት) ዘሪቱ ጌታሁን [ቃለ-ምልልስ]

ዘሪቱ ከበደ ዘፈን አቁማለች ወይንስ አላቆመችም የሚሉ አናጋጋሪ ጉዳዮች በርካታ ጊዜያት ሲነሱ ቆይተዋል፡፡ ይሄንን ጉዳይ በተመለከተ ከእርሷ አንደበት ይህ ነው የሚባል ቁርጥ ያለ ምላሽ ሳይሰጥበት በመቆየቱ በበርካቶች ዘንድ አከራካሪ ጉዳይ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ዘሪቱ በየወሩ በአማርኛ ቋንቋ ታትሞ ለገበያ በሚበቃው ሪቪል (REVEAL)መፅሄት ባደረገችው ቃለ ምልልስ ከዘፈኑ አለም በመውጣት መንፈሳዊ ጉዞ ላይ መሆኗን አስታውቃለች፡፡ መፅሄቱ ከቀረበላት ጥያቄዎች መካከል ዋና ዋናዎች አለፍ አለፍ ብይ በመቃኘት ላስነብባችሁ፡፡


☞ሪቪል፡ ከመንፈሳዊነት ጋር ተያይዞ መዝፈን አቁመሻል?
☞ዘሪቱ፡ መንፈሳዊነት ሁለገብና የሁለንተናችን ለውጥ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ደግሞ ከአለማዊነት ስንወጣ የማይነካ የህይወታችን ክፍል የለም፡፡ ሁሉም ነገር እኔ እንደምለውና ዓለም እንደምትሰብከው ሳይሆን እግዚአብሄር እንደሚለው የማድረግና የመሆን ሂደት ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ታዲያ እንደ ሁሉ ነገሬ የጥበብ ስራየም ሳይፈተሸ አያልፍም፡፡ ስለዚህ ሙዚቃም ይሁን ፊልም፤ ብቻ ምንም ነገር ልስራ የማደርገው ነገር እግዚአብሄር የሚፈልገውን መለዕክት ያደርሳል ወይ? ሰዎችን ይጠቅማል ወይ? ደሞስ እንደሱ ፍቃድና ልክ ሰዎችን ያሳዝናል? ያስደስታል ወይ ብዪ በመጠየቅና ይልቁንም ከሱ ከራሱ መለዕክትን በመቀበል ወደ መስራት መንፈሳዊነት እያደኩ ነው፡፡ መዝፈን ይሁን መዘመር አላውቅም፡፡ የማውቀው እግዚአብሄር እንደሚከብርበት ነው፡፡

☞ሪቪል፡ ብዙዎች ግን “ዘሪቱ ወይ ትዘምር ወይ ትዝፈን መቁረጥ አቅጧት እየወላወለች ነው” ይላሉ፡፡ በእርግጥ እየወላወልሽ ነው?

☞ዘሪቱ፡ እየሱስ ክርስቶስን ተከትያለሁ ብዪ በማምንባቸው ዓመታት ውስጥ በአካሄዴ ሁሉ እግዚአብሄርን ደስ አሰኝቻለሁ ብዪ አላስብም፡፡ ምንአልባትም በአንዳንድ የህይወቶቼ ክፍሎች እግዚአብሄርን አይፈሩም ተብለው ከሚታሰቡት ሰዎች እንኳን ብሼ አውቃለሁ፡፡ እንደእግዚአብሄር ምህረትና እንደ አባትነቱ ፍቅር ባይሆን ኖር ዛሬ ያለሁበት ቦታ አልገኝም ነበር፡፡ሰ አድርጌ የማላውቅ ግን መወላወል ነው፡፡ ፈርቼ አውቃለሁ፤ ግራ ገብቶኝም ያውቃል፤ ፈርሶ ሲሰራ እንደሰነበተ ሰው ደግሞ በሁሉም ነገር እርግጠኛ ሆኜ ሀሳቤን ሳለውጥ መጥቻለሁም ብዪ ለመናገርም አልደፍርም፡፡ ወላውዪ ግን አላውቅም፡፡

ዘሪቱ ሙዚቃ አቁማለች ብሎ ሚዲያ ጭምር ሲዘግብ ፤ እኔን ጠይቆና አነጋገግሮ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ከሆነች መቆሟ አይቀርም ብለው በራሳቸው በመደምደም ነው፡፡ እኔ ህይወቴን ስቀጥልና ከተነገሩት ዜናዎች በተቃራኒ የሙዚቃስራዎች ወደ አድማጭ ሲደርሱ የወላወልኩ የሚያስመስል መልክ ሊያሰጠኝ ችሏል፡፡
☞ሪቪል፡ ግን ዝናና ገንዘብን መስዋትነት ማድረግ የሚከብድ አይደለም?

☞ዘሪቱ፡ እኔ ለመተው የሚከብድ የገንዘብ ክምችት የለኝም፡፡ዝናንም በተመለከተ ዘማሪዎች ከዘፋኞች ባልተናነሰ ዝነኞች የሆኑበት ዘመን እንደሆነ ነው የማስበው፡፡ ከዝና ወደ ዝና ብሸጋገር አሁን ከምከፍለው ዋጋ የበለጠ እንደምከፍል አውቃለሁ፡፡

☞ሪቪል፡ ቤት መኪናና ሌሎች አያስፈልጉም ብለሽ ነው የምታምኚው?
☞ዘሪቱ፤ እኔ የማምነው ከሆነ ቦታ ተነስተህ የሆነ ቦታ ለመድረስ ትራንሰፖርት እንደሚያስፈልግ ነው፡፡ መኪናው ያንተ ከሆ ጥሩ፤ ካልሆነም መኖርህን ለማታውቅበት ለዛሬ ባለቤትነትህ ያለው ፋይዳ ውስን ነው፡፡ የቤትም አስፈላጊነት መጠለያነቱ፤ትርጉሙም አብረውህ በሚኖሩት ሰዎች እንጂ በባለቤተረነት ካርታው አይደለም፡፡ የባለቤተረነት ዋስትና ለእኔ ትርጉም የለሽ ነው፡፡እግዚአብሄር ወዶ ለሚጨምርልኝ ለእያንዳንዱ ቀን የሚያስፈልገኝን ሁሉ እንደሚያዘጋጅልኝ አምናለሁ፡፡
☞ሪቪል፤ እንደዚህ ያለ ህወት ግን ላገባችና በተለይም ልጆች እናት ለሆነች ሴት አይከብድም?

☞ዘሪቱ፤ እንደዚህ ያለ ህይወት ለማንም ቀላል አይደለም፡፡ በተለይም እንዳልከው፤ቤተሰብ ላለን ሰዎች ደግሞ የማይታሰብ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በስጋዊ አቅማችን ስንሞክረው ነው፡፡ ሰው የመሆንን ትርጉም ለመረዳት በፈቀድን መጠን ግን ራሱ እግዚአብሄር በእና ውስጥ ይችለዋል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን መከተል ማለት፤ ሰው በሀጢያት ከመውደቁ በፊት ወደ ነበረው ማንነት የመመለስ ጉዞ ማለት ነው፡፡ ያ ማንነት ደግሞ ከእግዚአብሄር የመሆንና ማንነቱን የማንፀባረቅ ህይወት ነው፡፡ በመሬታዊ ገደብ እሱን ማንፀባረቅ አይቻልም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አሰልጣኝነት ከመሬታዊ ገደብ ወደ እሱ ማንነት የሚያሻግረን መመሪያ ሁሉ ደሞ በቅዱስ ቃሉ ወስጥ አለ፡፡ ኢየሱስ ለምን አይነት ክብር እንደጠራን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ከንግዳችን፣ ከቤተሰባችንና ከራሳችን ጭምር በላይ እሱን እንድናስቀድም ነው፡፡ ይህ ሲሆን ብቻ ደቀመዛሙርቶቹ ልንሆን እንምንችል በግልፅ አስቀምጦልናል፡፡ ስለዚህ እሱን በመከተል ውስጥ ምንም አይነት አቋራጭ አልፈልግም፡፡
☞ሪቪል፤ ባለቤትሽ በዚህ ደስተኛ ነው?

☞ዘሪቱ፤ በጣም ደስተኛ ነው እንጂ፡፡ የምተገዛ ሚስት አድረጎለታል፡፡ ከዚህ ህይወት ጋር በተዋወኩባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በእኔ ላይ ባስከተለው የማንነት መናጋት ተከትለው በመጡ ጥፋቶች ብዙ ዋጋ ከፍሏል፡፡ ሚስትህ ፈርሳ እስክተሰራ መታገስ ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ከመጀመሪያዋ የተሻለች ሚስት እንዳለችው እሱ ምስክር ነው፡፡
ጌታ ይባርክሽ ዘሪቱ!!
@የእውነት ቃል
source: zehabesha.com
☞ሪቪል፡ ከመንፈሳዊነት ጋር ተያይዞ መዝፈን አቁመሻል?
☞ዘሪቱ፡ መንፈሳዊነት ሁለገብና የሁለንተናችን ለውጥ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ደግሞ ከአለማዊነት ስንወጣ የማይነካ የህይወታችን ክፍል የለም፡፡ ሁሉም ነገር እኔ እንደምለውና ዓለም እንደምትሰብከው ሳይሆን እግዚአብሄር እንደሚለው የማድረግና የመሆን ሂደት ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ታዲያ እንደ ሁሉ ነገሬ የጥበብ ስራየም ሳይፈተሸ አያልፍም፡፡ ስለዚህ ሙዚቃም ይሁን ፊልም፤ ብቻ ምንም ነገር ልስራ የማደርገው ነገር እግዚአብሄር የሚፈልገውን መለዕክት ያደርሳል ወይ? ሰዎችን ይጠቅማል ወይ? ደሞስ እንደሱ ፍቃድና ልክ ሰዎችን ያሳዝናል? ያስደስታል ወይ ብዪ በመጠየቅና ይልቁንም ከሱ ከራሱ መለዕክትን በመቀበል ወደ መስራት መንፈሳዊነት እያደኩ ነው፡፡ መዝፈን ይሁን መዘመር አላውቅም፡፡ የማውቀው እግዚአብሄር እንደሚከብርበት ነው፡፡
☞ሪቪል፡ ብዙዎች ግን “ዘሪቱ ወይ ትዘምር ወይ ትዝፈን መቁረጥ አቅጧት እየወላወለች ነው” ይላሉ፡፡ በእርግጥ እየወላወልሽ ነው?
☞ዘሪቱ፡ እየሱስ ክርስቶስን ተከትያለሁ ብዪ በማምንባቸው ዓመታት ውስጥ በአካሄዴ ሁሉ እግዚአብሄርን ደስ አሰኝቻለሁ ብዪ አላስብም፡፡ ምንአልባትም በአንዳንድ የህይወቶቼ ክፍሎች እግዚአብሄርን አይፈሩም ተብለው ከሚታሰቡት ሰዎች እንኳን ብሼ አውቃለሁ፡፡ እንደእግዚአብሄር ምህረትና እንደ አባትነቱ ፍቅር ባይሆን ኖር ዛሬ ያለሁበት ቦታ አልገኝም ነበር፡፡ሰ አድርጌ የማላውቅ ግን መወላወል ነው፡፡ ፈርቼ አውቃለሁ፤ ግራ ገብቶኝም ያውቃል፤ ፈርሶ ሲሰራ እንደሰነበተ ሰው ደግሞ በሁሉም ነገር እርግጠኛ ሆኜ ሀሳቤን ሳለውጥ መጥቻለሁም ብዪ ለመናገርም አልደፍርም፡፡ ወላውዪ ግን አላውቅም፡፡
ዘሪቱ ሙዚቃ አቁማለች ብሎ ሚዲያ ጭምር ሲዘግብ ፤ እኔን ጠይቆና አነጋገግሮ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ከሆነች መቆሟ አይቀርም ብለው በራሳቸው በመደምደም ነው፡፡ እኔ ህይወቴን ስቀጥልና ከተነገሩት ዜናዎች በተቃራኒ የሙዚቃስራዎች ወደ አድማጭ ሲደርሱ የወላወልኩ የሚያስመስል መልክ ሊያሰጠኝ ችሏል፡፡
☞ሪቪል፡ ግን ዝናና ገንዘብን መስዋትነት ማድረግ የሚከብድ አይደለም?
☞ዘሪቱ፡ እኔ ለመተው የሚከብድ የገንዘብ ክምችት የለኝም፡፡ዝናንም በተመለከተ ዘማሪዎች ከዘፋኞች ባልተናነሰ ዝነኞች የሆኑበት ዘመን እንደሆነ ነው የማስበው፡፡ ከዝና ወደ ዝና ብሸጋገር አሁን ከምከፍለው ዋጋ የበለጠ እንደምከፍል አውቃለሁ፡፡
☞ሪቪል፡ ቤት መኪናና ሌሎች አያስፈልጉም ብለሽ ነው የምታምኚው?
☞ዘሪቱ፤ እኔ የማምነው ከሆነ ቦታ ተነስተህ የሆነ ቦታ ለመድረስ ትራንሰፖርት እንደሚያስፈልግ ነው፡፡ መኪናው ያንተ ከሆ ጥሩ፤ ካልሆነም መኖርህን ለማታውቅበት ለዛሬ ባለቤትነትህ ያለው ፋይዳ ውስን ነው፡፡ የቤትም አስፈላጊነት መጠለያነቱ፤ትርጉሙም አብረውህ በሚኖሩት ሰዎች እንጂ በባለቤተረነት ካርታው አይደለም፡፡ የባለቤተረነት ዋስትና ለእኔ ትርጉም የለሽ ነው፡፡እግዚአብሄር ወዶ ለሚጨምርልኝ ለእያንዳንዱ ቀን የሚያስፈልገኝን ሁሉ እንደሚያዘጋጅልኝ አምናለሁ፡፡
☞ሪቪል፤ እንደዚህ ያለ ህወት ግን ላገባችና በተለይም ልጆች እናት ለሆነች ሴት አይከብድም?
☞ዘሪቱ፤ እንደዚህ ያለ ህይወት ለማንም ቀላል አይደለም፡፡ በተለይም እንዳልከው፤ቤተሰብ ላለን ሰዎች ደግሞ የማይታሰብ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በስጋዊ አቅማችን ስንሞክረው ነው፡፡ ሰው የመሆንን ትርጉም ለመረዳት በፈቀድን መጠን ግን ራሱ እግዚአብሄር በእና ውስጥ ይችለዋል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን መከተል ማለት፤ ሰው በሀጢያት ከመውደቁ በፊት ወደ ነበረው ማንነት የመመለስ ጉዞ ማለት ነው፡፡ ያ ማንነት ደግሞ ከእግዚአብሄር የመሆንና ማንነቱን የማንፀባረቅ ህይወት ነው፡፡ በመሬታዊ ገደብ እሱን ማንፀባረቅ አይቻልም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አሰልጣኝነት ከመሬታዊ ገደብ ወደ እሱ ማንነት የሚያሻግረን መመሪያ ሁሉ ደሞ በቅዱስ ቃሉ ወስጥ አለ፡፡ ኢየሱስ ለምን አይነት ክብር እንደጠራን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ከንግዳችን፣ ከቤተሰባችንና ከራሳችን ጭምር በላይ እሱን እንድናስቀድም ነው፡፡ ይህ ሲሆን ብቻ ደቀመዛሙርቶቹ ልንሆን እንምንችል በግልፅ አስቀምጦልናል፡፡ ስለዚህ እሱን በመከተል ውስጥ ምንም አይነት አቋራጭ አልፈልግም፡፡
☞ሪቪል፤ ባለቤትሽ በዚህ ደስተኛ ነው?
☞ዘሪቱ፤ በጣም ደስተኛ ነው እንጂ፡፡ የምተገዛ ሚስት አድረጎለታል፡፡ ከዚህ ህይወት ጋር በተዋወኩባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በእኔ ላይ ባስከተለው የማንነት መናጋት ተከትለው በመጡ ጥፋቶች ብዙ ዋጋ ከፍሏል፡፡ ሚስትህ ፈርሳ እስክተሰራ መታገስ ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ከመጀመሪያዋ የተሻለች ሚስት እንዳለችው እሱ ምስክር ነው፡፡
ጌታ ይባርክሽ ዘሪቱ!!
@የእውነት ቃል
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45476#sthash.bBT1znLx.dpuf

“ዘፈኑን እየተውኩ ወደ ዝማሬው ዓለም እየገባሁ ነው” – ድምፃዊት(ዘማሪት) ዘሪቱ ጌታሁን [ቃለ-ምልልስ]

  • 707
     
    EmailShare
ዘሪቱ ከበደ ዘፈን አቁማለች ወይንስ አላቆመችም የሚሉ አናጋጋሪ ጉዳዮች በርካታ ጊዜያት ሲነሱ ቆይተዋል፡፡ ይሄንን ጉዳይ በተመለከተ ከእርሷ አንደበት ይህ ነው የሚባል ቁርጥ ያለ ምላሽ ሳይሰጥበት በመቆየቱ በበርካቶች ዘንድ አከራካሪ ጉዳይ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ዘሪቱ በየወሩ በአማርኛ ቋንቋ ታትሞ ለገበያ በሚበቃው ሪቪል (REVEAL)መፅሄት ባደረገችው ቃለ ምልልስ ከዘፈኑ አለም በመውጣት መንፈሳዊ ጉዞ ላይ መሆኗን አስታውቃለች፡፡ መፅሄቱ ከቀረበላት ጥያቄዎች መካከል ዋና ዋናዎች አለፍ አለፍ ብይ በመቃኘት ላስነብባችሁ፡፡
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45476#sthash.bBT1znLx.dpuf

Monday, July 13, 2015

Health: የሴትን ልጅ ልብ ለመማረክ እና ቀጣይነት ያለው ግንኙነት ለመመስረት የሚረዱ 6 ነጥቦች


ሴቶች በፍቅር ውስጥ አጥብቀው የሚፈልጉት ምንድነው?

በጥንዶች መካከል ለሚኖር የተሳካ የፍቅር ግንኙነት የፍላጎት መጣጣም እጅግ አስፈላጊ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ በዚህ ረገድ የሰው ልጆች በአጠቃላይ፣ ተመሳሳይ የሚመስል መሰረታዊ ፍላጎቶች ቢኖራቸውም ወንዶችና ሴቶች በየግል ከፍተኛ ቦታ የሚሰጧቸው የተለያዩ የስሜት ፍላጎቶች ይኖሯቸዋል፡፡
በግንኙነት መስክ ውስጥ ከምንጠቀምባቸው ክህሎቶች ሁሉ የመጀመሪያውና ጠቃሚ ነገር፣ የተጓዳኛችንን ጥልቅ ፍላጎት እና ተግባራት አስቀድሞ መረዳት ሲሆን፣ ይህ ማስተዋል አብሮን ያለውን ሰው ጠንቅቀን እንድንረዳ ስለሚያግዘን ችግሮች ከመሰከታቸው በፊት እንድንታደጋቸው ብሎም ከተፈጠሩ በኋላ በንቃት እና በጥበብ መለስ እንድንል ይረዳናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሰዎችን መሻት ሳይነግሩን የማወቅ ክህሎትን መማርና መለማመድ፣ አታካችና አድካሚ ቢመስልም ውጤቱ ግን እጅግ አመርቂ እንደሚሆን አያጠያይቅም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ በጥንዶች መካከል ተቀራርቦ ፍላጎቶችን ማውራት፣ ስሜትን መጋራትና ምክንያትን መግለጽ፣ የተሻለ ቅርርቦሽን በመፍጠር በትዳር ላይ መተማመንን ስለሚጨምር መልካም የሚባል ውጤትን ሊያስገኝልን ይችላል፡፡

ብዙውን ጊዜ ሰዎች ጥምረት የሚገቡት በዘርፉ በቂ የሚባል ዝግጅት ሳይኖራቸው እንደሆነ በተደጋጋሚ በዚህ አምድ ላይ የተነሳ ጉዳይ ነው፡፡ ይህም ትዳርን ውስብስብ እና አታካች እያደረገ መጥቷል፡፡ ከስልጣኔ ጋር ተያይዞ የመጣውም የሰው ልጅ ፍላጎት መጨመርና በትንሽ ነገር ያለመርካት አባዜ፣ በትዳር ውስጥ ተስፋ መቁረጥ የራሱን የሆነ ሚና ይጫወታል፡፡
በአንድ ወቅት ኖራ ሃይደን የተባለች የማህበራዊ ህይወት ተመራማሪ በመጽሐፏ እንዳለችው፣ አብዛኛው ወንዶች ስለ ሴቶች ያላቸው አተያይ እጅግ አስደንጋጭ ነበር፡፡ በወንዶች ዓይን ሴቶች ማለት፣ በዚህች ምድር ላይ ካሉ ነገሮች ሁሉ በላቀ ደረጃ እጅግ ውስብስብና፣ ፍላጎታቸው የማይታወቅ በቀላሉ የማይረኩ ፍጡሮች እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡
በዚሁ ጥናት ላይ የሴትን ልጅ ፍላጎት ከመረዳትና፣ ሴትን ልጅ ደስተኛ ከማድረግ ይልቅ (ኑዩክለር ፊዚክስ ማጥናት እንደሚቀል ገልጧል)
ይህ በእውነቱ ከእውነታው ጋር እጅግ የሚጣረስና ለሴቶች እጅግ አስደንጋጭ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ እሳቤ የሚመነጨው ሁላችንም በራሳችን ግለኛ ዓለም ውስጥ ተከልለን የራሳችንን ተፈጥሮና ፍላጎት ብቻ ስለምናዳምጥና የሌሎችን ማንነት ለማወቅና ተጣጥሞ ለመኖር ምንም አይነት ጥረት ስለማናደርግ ይመስለኛል፡፡
በተለያየ ጊዜ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች፣ ስለወንዶችና ሴቶች ረቂቅ ባህሪያትና ፍላጎት ለማወቅ በርካታ ጥናቶችን አካሂደዋል፡፡ ከእነዚህ ጥናቶች የተውጣጣውን መደምደሚያ መሰረት በማድረግ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ሴቶች የሚስማሙበትንና፣ ሴቶች ከትዳር አጋራቸው ወይም ፍቅረኛቸው አጥብቀው የሚሹትን 6 ነጥቦችን ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡

የሴትን ልጅ ልብ ለመማረክ እና ቀጣይነት ያለው ግንኙነት ለመመስረት የሚረዱ 6 ነጥቦች
(Caring) እንክብካቤ
1. በጥናቱ ውስጥ ከተካተቱ አብዛኛዎቹ ሴቶች በፍቅር ለሚንከባከብ ወንድ በቀላሉ እንደሚሸነፉ ገልፀዋል፡፡ ይህም የሚሆነው ሴቶች በተፈጥሮ ካላቸው የእንስትነት ባህሪ የተነሳ ከወንዶች ስሜት እና ፍቅርን ብቻ ሳይሀን፣ ከለላን፣ አለኝታነትን እና እክብካቤን አጥብቀው እንደሚሹ ተናግረዋል፡፡ ይሄም ምኞት እና ደህንነት እንዲሰማው ስለሚያደርግ ህይወትን ለቀቅ አድርገው በመመልከት የበለጠ ደስተኛ ያደርጋቸዋል፡፡

2. ትኩረት
ይሄንን ፍላጎት በሁለት ከፍለን ልናየው እንችላለን፡፡
2.1 መደመጥ
Joeu Barton የተባለ የስርዓተ ፆታ ተመራማሪ በጥናቱ ላይ እንዳሰፈረው፣ ሴቶች በቀን ውስጥ በአማካኝ 20,000 ቃላቶችን ሲጠቀሙ፣ በተቃራኒው ወንዶች ደግሞ 7,000 ቃላትን በመጠቀም ሀሳባቸውን ያስረዳሉ፡፡ ይህም በግልፅ እንደሚያስረዳን አንደኛ ሴቶች ለቋንቋ እና ለንግግር ፈጣን የሆነ አዕምሮ እንዳላቸው ሲሆን፣ ሌላው እና ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ፣ ሴቶች በንግግር ራሳቸውን በመግለፅ የበለጠ ነፃነት እንደሚሰማቸው ሲሆን ችግር በገጠማቸውና በጨነቃቸውም ጊዜ በማውራት ብቻ ያለ ምንም ተጨማሪ ምክርና መፍትሄ የተሻለ እፎይታና እረፍት እንደሚሰማቸው ሲሆን፣ በዚህም ጊዜ ንግግራቸውን በትኩረት ለሚያዳምጣቸው ወንድ የተለየ ፍቅርና አክብሮት ይኖራቸዋል፡፡
2.2 አንዲሰት ሴት አብሯት ካለ ወንድ ከፍቅርና እንክብካቤ ባሻገር አትኩሮ ትሻለች
በርካታ የህይወት ተሞክሮዎች እንደሚያመለክቱት፣ ሰዎች በተሰበሰቡበት ግብዣ ላይ አንድ ወንድ ፍቅረኛውን ወይም የትዳር አጋሩን ከሰዎች ጋር በሚኖረው ጨዋታ እጇን በማሻሸት ወይም በመሳም፣ አብሮነቱን ቢያረጋግጥላት በቀላሉ ልቧን በፍቅር በማቅለጥ የጥሩ ስሜት ባለቤት እንድትሆን እንደሚረዳ ይታመናል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ወንዶች በግንኙነት ውስጥ የሚመለከቱት፣ ትልቁን ምስል ብቻ በመሆኑ አብሮነት በራሱ በቂ ነው ብለው ሊያስቡ ይችላሉ፡፡ ሴቶች ደግሞ ባላቸው የተለያየ አፈጣጠር ዝርዝር ነገሮች ላይ ትኩረት ስለሚያደርጉ እያንዳንዱን እንቅስቃሴና ፍሰት ይከታተላሉ፡፡ በመሆኑም ወንዶች ፍቅረኛቸው ወይም የትዳር አጋራቸውን ከመነፈጠሯም ረስተው ለረጅም ሰዓት ከሶስተኛ ወገን ጋር ጨዋታ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በሴቶች አዕምሮ ውስጥ የመተውና አትኩሮት የማጣት ስሜትን ሊያጭር ስለሚችል ወንዶች ትኩረት ሊያደርጉበት ይገባል፡፡ ይሄንን በጣም ቀላል ግን ከፍተኛ ተፅዕኖ ሊፈጥር የሚችል እውነታ በመረዳት፣ በሄዳችሁበት ሁሉ ለሴቶቻችሁ አብሮነት ትኩረትና ዕውቅናን በመስጠት፣ ስሜታቸውን ከመጉዳት ብትታደጉ በምላሹ ፍቅር እና አድናቆትን ትቀበላላችሁ፡፡
እዚህ ጋ ልብ ልንለው የሚገባው እውነታ፣ ይህ ዓለም መስጠትንና መቀበልን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ የሰውን ስሜት ጎድቶ መልካም የስሜት ምላሽ መጠበቅ የዋህነት ስለሆነ፣ የምንፈልገውን ለማግኘት የሚፈለገውን መስጠት ግድ ይለናል፡፡

3. (Security) ጥበቃ
ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው፣ የወንድ ልጅ ከለላ እና መጋ መሆን፣ አሁንም ድረስ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ያለው እውነታ ነው፡፡ በዚህ በሰለጠነው እና የሴቶች እኩልነት በተረጋገጠበት 21ኛው ክፍለ ዘመን እንኳን፣ ሴት ልጅ በግሏ ገቢ በማስገኘት ሀብት ማካበት ብትጀምርም፣ የወንድ ልጅ ግብአት አቅራቢ እና ጠባቂ መሆን የሴትን ልጅ ስሜት ለማረጋጋት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህም በዘለለ ወንድ ልጅ ለሴት ከተለያየ አደጋ ጠባቂ ሆኖ መገኘቱ፣ እምነቷን የበለጠ ስለሚያጠነክረው ፍቅሯ እየጎለበተ ይሄዳል፡፡

4. Blind Loyalty (ፍፁም የሆነ ተአማኒነት)
በአብዛኛው አንዲት ሴት የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ስትሆን ወይም በወንድ ስትፈቀር ራሷን የተለየች ፍጡር አድርጋ እንድታይ ትሆናለች፡፡ ይህም ምን አልባት ከሴቶች ተፈጥሮ በተጨማሪ ወንዶች በፍቅር መብረቅ በተመቱ ጊዜ ያፈቀሯትን ሴት የግላቸው ለማድረግ የሚጠቀሙበት ገደብ የለሽ ሙገሳና ማሞካሸት፣ ሴቶች ለራሳቸው ያላቸውን አመለካከት በማዛባት፣ ውጫዊ መስህብን እንደ ብቸኛ የማንነታቸው መለኪያ አድርገው እንዲወስዱት ሳያስገድዳቸው አልቀረም፡፡
በመሆኑም በግንኙነት ውስጥ አንዲት ሴት የራሷን የመስህብ ደረጃ ጠንቅቃ ብታውቅም ባፈቀራት ወንድ እይታ ስትፈረጅ ‹‹ሁሉን ያስናቀች ቆንጆና ፀባየ ሰናይ መሆኗን እንዲነገራት ትፈልጋለች›› በማንኛውም አጋጣሚ የእሷ ወንድ የሌላዋን ቆንጆ አለባበስ ወይም አቋም ቢያደንቅ እሷን የወሰደባት ያህል ስለሚሰማት መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሰውን ቆንጆ በመቃረም፣ የትዳር አጋራችንን ስሜት ከምንጎዳ፣ ያገባናትን ሴት በትዳር አብረን እንድንኖር ውሳኔ ላይ ያደረሰንን መልካም ሰብዕና፣ ውበት፣ ወይም ተግባር በማስታወስ ከልብ የመነጨ አድናቆታችንን እና ሙገሳችንን መቸርን ብንለማመድ፣ ለትዳራችን ዕድሜ ማራዘሚያነት እንደሚጠቅም ጥናቶች እና ተሞክሮዎች ያመለክታሉ፡፡

5. Understanding (መረዳት)
በርካታ ሴቶች ከተጓዳኛቸው አጥብቀው የሚፈልጉት ተጨማሪው ነገር፣ የትዳር አጋራቸው የእነሱን ሚና እና በቤት ውስጥ ያላቸውን አስተዋፅ እንዲረዳ እና ዕውቅና እንዲሰጥ ነው፡፡ አንዳንድ ወንዶች ሴት ልጅ በቤት ውስጥ የምታከናውናቸውን ረቂቅና እጅግ ወሳኝ ተግባራት ባለማወቅ ዕውቅናን ሲነፍጉ ይስተዋላሉ፡፡ የሴት ልጅ ተፈጥሮ ማለትም በሴትነት የምታልፋቸውን ከባባድ ደረጃዎች፣ እርግዝና፣ ወሊድ፣ ማጥባት እና ልጅን መንከባከብ በምድራችን ካለ ነገር ሁሉ እጅግ ውድ፣ ፈታኝ እና ዋጋ ሊተመንለት የማይችል መሆኑን በመረዳት፣ ሴት ሆነው ያንን መክፈል እንኳን ባይችሉ፣ ክብደቱን በመረዳት እና ርህራሄ በማሳየት ሊያዝኑላቸው፣ ሊንከባከቧቸው እና ሊደግፏቸው ይገባል፡፡ ይሄም በሴት ልጅ ልቦና ውስጥ እስከ መጨረሻው ለመቀመጥ ጥርጊያ መንገድ ይሆናል፡፡

6. Sex (ወሲብ)
በተጣማሪዎች መካከል ፍቅር ሰምሮ ኑሮ እንዲደረጅ፣ በሐሳብ እና ፍላጎት መጣጣም ተቀዳሚው መሆኑ የማያጠያይቅ ሀቅ ነው፡፡ መከባበሩ፣ መፈቃቀሩና የሐሳብ መጣጣሙ እንደተጠበቀ ሆኖ በወሲብ አለመጣጣም ባለትዳሮች ከትዳራቸው ውጪ ሌላ ሰው መጎብኘታቸው የተለመደ ተግባር እየሆነ መጥቷል፡፡
ብዙውን ጊዜ ተጣማሪዎች፣ የሐሳብ አለመጣጣምን አቻችለውና ተቻችለው ኑሮን ሲገፉ ይስተዋላል፡፡ በአሁኑ ዘመን እየተስተዋለ የመጣው እውነታ እንደሚያመለክተን ግን በወሲብ አለመጣጣምን ማስታመም ስለሚያቅታቸው ወይም ከሌላ ጋ ሲማግጡ ወይም ከነጭራሹ ትዳርን ሲያፈርሱ ይታያሉ፡፡
በአብዛኛው በርካታ ወሲብ ነክ ፅሑፎችና ጥናቶች አንድን ወንድ እንዴት ለወሲብ ማነሳሳት እንዳለብን እና እንዴት እርካታ ላይ እንዲደርስ መርዳት እንዳለብን የሚገልፁ ናቸው፡፡ ይህም የሚያሳየው የሴት ልጅ ስሜት ይሄ ነው የሚባል አትኩሮት ከማህበረሰቡ ጭምር እንዳልተቸገረው ነው፡፡
Nora Hayden (How to satisfy a women every time) በተሰኘው መጽሐፏ ላይ እንደገለፀችው 80% የሚሆኑት ሴቶች፣ እውነተኛ እርካታ ላይ እንደሚደርሱ ሆኖም የትዳር አጋራቸውን ለማስደሰት ሲሉ ብቻ እርካታ ላይ እንደደረሱ እንደሚያስመስሉ ይናገራሉ፡፡ ይህም የሚሆነው ወንዶች በወሲብ ጊዜ የሴትን ልጅ ፍላጎት እና የስሜት ምስጢር መረዳት ስለሚያቅታቸው እነሱ በሚረኩበት መንገድ ይረካሉ ብለው በማሰብ ዘልማዳዊ የሆነውን ግንኙነት ያደርጋሉ፡፡ ሆኖም ፈጣሪ ወሲብን በትዳር መካከል እንድትደሰትበትና ትውልድን እንድናስቀጥልበት የሰጠን ታላቅ ፀጋ በመሆኑ፣ የሴትም ልጅ ስሜት መጠበቅ እና በባሏ መደሰት እንዳለባት በመረዳት በግልፅ በመወያየትም ሆነ በዘርፉ የተፃፉ ጽሑፎችን በማንበብ፣ ደስታውን የጋራ የማድረግ የወንዶች ተቀዳሚ ኃላፊነት ነው፡፡
በመጨረሻ ማንሳት የምፈልገው ነጥብ፣ ብዙዎች በትዳር ላይ በግንኙነት ዙሪያ በመርህ ደረጃ የሚነሱ ጠቃሚ ምክሮችን ማንበብ ፋይዳ ቢ መሆኑን ሲናገሩ ይታያል፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያትነት የሚያነሱት መከራከሪያ የፀሐፊዎቹ ወይም አነበብን የሚሉ ሰዎችን ግለ ህይወት በናሙናነት በማንሳት፣ በትዳር ህይወታቸው ስኬታማ አለመሆናቸውን ነው፡፡ እዚህ ጋ መረዳት ያለብን ቁም ነገር፣ ችግሩ ያለው ከዕውቀቱ ወይም ከንባቡ ሳይሆን ያወቅነውን እና የሰማነውን በልቦናችን አኑረን መተግበር ስለሚሳነን መሆኑን ነው፡፡ በመሆኑም ተፈጥሮ የለገሰችን ሰብዕና፣ በህይወት ተሞክሮ እና ዕውቀት በማዳበር፣ ያካበትነውን ዕውቀት በመተግበር እና ለውጥ በማምጣት ትዳራችን በግምት ሳይሆን፣ በጥበብ የምንመራትን ልቦና ይስጠን፡፡

ሴት ልጅ ምን መስማት አትሻም!
ሴቶች ስለ ሌላ ሴት ወይም ስለ ቀድሞ ጓደኛህ ስታደንቅ መስማት አትፈልግም፡፡ ከሌላ ሴት ጋር እንድታወዳድራትም እንዲሁ፡፡ ስለ ሰውነት ቅርጽና ውበቷ አድናቆት እንጂ ነቀፌታ ቅር ያሰኛታል፡፡ በድንገት ተሳስተህ የሌላ ሴት ስም ማንሳትም አይኖርብህም፡፡ በሌላ መንገድ ያስጠረጥርሃልና፡፡ ከአሁን ቀደም በነበረህ የሴት ልጅ ትውውቅ ውስጥ አላግባ ያደረካቸውን ነገሮች ማውራትህ ከባድ ግምት ውስጥ ይጥልሃልና በተቻለ መጠን ከኋላ ፈቅር ታሪክህ ውስጥ ጥሩ ጥሩውን እንጂ የሚያስተችህን ለመርሳት ወይም ላለማንሳት ጥረት አድርግ፡፡ በሌላዋ ላይ ይህን ያደረገ በእኔም ላይ ማድረጉ አይቀርም የሚል እምነት ይኖራታልና፡፡ ሴቶች ስለ አንተ ማወቅ የሚፈልጉትን ሲጠይቁህ እውነቱን መናገሩን ብቻ ነው የሚያዋጣው፡፡ ብዙ ጊዜ ሴቶች ለማወቅ በሚመስል መልኩ ይጠይቃሉ እንጂ የሚጠይቁትን ነገር ቀድሞውኑ ያውቁታልና አትዋሽ!
በተቻለ መጠን ከአሁን ቀደም ከነበረህ የፍቅር ትስስር እንዴት እንደተለያየህ ምክንያትህን አሳማኝነት ያለውና ከአንተ በኩል ከፍተኛ ጥረት ማድረግህ ላይ ያነጣጠረ ይሁን እንጂ ኃላፊነትህን ስላለመወጣትህ የሚያንፀባርቁ ምክንያቶችን ወይም ደግሞ ቀድሞውኑ ለመለያየት የማያበቁ ምክንያቶችህን ሴቶች መስማት አይፈልጉም!! ቢሰሙም ትዝብት ውስጥ ይጥሉሃልና ጠንቀቅ በል!!

source: www.zehabesha.com

Wednesday, July 8, 2015

የግል ባንኮች ትርፍ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል

የግል ባንኮች ትርፍ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል

የግል ባንኮች ትርፍ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል
-ንግድ ባንክ ከታክስ በፊት 12 ቢሊዮን ብር ማትረፉ ተሰምቷል
በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ 16 የግል ባንኮች በ2007 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ እንደሚያገኙ ሲጠበቅ፣ አንዳንድ ባንኮችም የትርፍ ምጣኔያቸውን ከእጥፍ በላይ ማሳደጋቸው ታወቀ፡፡ 
የ2007 ዓ.ም. የባንኮቹ የመጀመሪያ ደረጃ ጥቅል መረጃ እንደሚያሳየው ሁሉም ባንኮች በአትራፊነታቸው ዘልቀዋል፡፡ ከአምናው የበለጠ ትርፍ ማግኘትም ችለዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ሁሉም ባንኮች ከታክስ በፊት አትርፈውት የነበረው ግርድፍ ትርፍ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ መሆኑ ይታወሳል፡፡
ሁሉም የግል ባንኮች በ2007 በበጀት የሒሳብ ሪፖርት ተቀናናሽ ሒሳብ ቢኖርባቸውም፣ ጥቅል ትርፋቸው ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ይሆናል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት ከፍተኛ ትርፍ በማግኘት ዘንድሮም ከግል ባንኮች ከፍተኛውን ትርፍ ያስመዘገበው ዳሸን ባንክ ሲሆን፣ ከታክስ በፊት ከ950 ሚሊዮን ብር በላይ ማትረፉ ተጠቁሟል፡፡ በ2006 ዓ.ም. ባንኩ ከታክስ በፊት 928 ሚሊዮን ብር ማትረፉ አይዘነጋም፡፡
አዋሽ ባንክም ወደ 890 ሚሊዮን ብር ገደማ ማትረፉ እየተነገረ ነው፡፡ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ከግል ባንኮች በትርፍ መጠኑ ወደ ሦስተኛ ደረጃ ላይ የመጣው የኦሮሚያ የኅብረት ሥራ ባንክ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በማትረፍ ደረጃውን ይዞ መቀጠሉ ታውቋል፡፡
በበጀት ዓመቱ በትርፍ ምጣኔው ከፍተኛ ዕድገት ካሳዩ ባንኮች መካከል እናት ባንክ አንዱ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ ከ72 ሚሊዮን ብር በላይ ማትረፍ ችሏል፡፡ ይህ ትርፍ ባለፈው በጀት ዓመት ካገኘው ትርፍ ጋር በንፅፅር ሲቀመጥ ከእጥፍ በላይ ማደጉን ያሳያል፡፡ ባንኩ በ2006 በጀት ዓመት አስመዝግቦት የነበረው ትርፍ 31 ሚሊዮን ብር እንደነበር ይታወሳል፡፡
እንደ እናት ባንክ ሁሉ ከአምናው የትርፍ ምጣኔ ጋር ሲነፃፀር ከ50 በመቶ በላይ ብልጫ ያለው ትርፍ ያስመዘገበው አንበሳ ባንክ ነው፡፡ እንደ ምንጮች ገለጻ የአንበሳ ባንክ በ2007 ዓ.ም. ያልተጣራ ትርፍ 275 ሚሊዮን ብር ደርሷል፡፡ ይህ ትርፍ አምና አስመዝግቦት ከነበረው 127 ሚሊዮን ብር ጋር ሲነፃፀር ከ145 ሚሊዮን ብር በላይ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ 
አንበሳ ባንክ በትርፍ ዕድገቱ ብቻ ሳይሆን 580 ሚሊዮን ብር የነበረውን የተቀማጭ ገንዘብ አቅሙን ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር በማድረስ ከፍተኛ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉ ይጠቀሳል፡፡
ብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ በ2006 ዓ.ም. 131 ሚሊዮን ብር የነበረውን ትርፍ ወደ 140 ሚሊዮን ብር ማድረስ ችሏል፡፡ ንብ ባንክ ከ430 ሚሊዮን ብር በላይ እንዳተረፈ ሲነገር፣ አምና 350 ሚሊዮን ብር ያተረፈው አቢሲኒያ ባንክ ደግሞ ከ365 ሚሊዮን ብር በላይ ማትረፉ ተጠቁሟል፡፡ ደቡብ ግሎባል ባንክም ከአምናው በተሻለ ከታክስ በፊት 31 ሚሊዮን ብር ማትረፍ ችሏል፡፡ ይህ ትርፍ ከሁሉም ባንኮች ያነሰ ነው፡፡ ባንኩ አምና ያገኘው ትርፍ 19 ሚሊዮን ብር ነበር፡፡
ሌሎቹም ባንኮች የትርፍ ምጣኔያቸው ዕድገት የተለያየ ቢሆንም፣ የትርፍ ዕድገት በማሳየታቸው በአጠቃላይ የግል ባንኮችን የትርፍ መጠን አምና ከነበረበት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ያሳድገዋል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡ 
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2007 በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር ከታክስ በፊት ማትረፉ ተሰምቷል፡፡ ንግድ ባንክ ባለፈው ዓመት 9.7 ቢሊዮን ብር ከታክስ በፊት ማትረፉ ይታወሳል፡፡ የዘንድሮው ግን ትልቅ ትርፍ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ 

Wednesday, July 1, 2015

ባዶ እግር መሄድ ለጤና የሚያስገኘው ጠቀሜታ

ከብዙ ዘመናት በፊት ጫማ የሚባለው የእግር ልባስ ከመሰራቱ በፊት ሰዎች እግራቸውን ባዶ ነበር የሚሄዱት።
በአሁኑ ጊዜም ቢሆን በገጠራማ አካባቢ ያሉ ሰዎች ያለ ጫማ በባዶ እግር ሲጓዙ ይስተዋላል።
ታዲያ በባዶ እግር መጓዝ ለጤናቸን በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተመራማሪዎች ያስታወቁ ሲሆን፥ ከነዚህም ውስጥ እግራችን የተስተካከለ እና ጤናማ የመንካት ስሜት እንዲሁም ከተፈጥሮ ጋር ቀጥታ ግንኙነት እንዲኖረው ያደርጋል።
በቀን ውስጥ ቢያንስ ለ5 ደቂቃ ያክል በባዶ እግር በመሄድ ወይም በመንቀሳቀስም ሰውነታችንን ተገቢውን ሀይል እንዲያገኝ እንደሚረዳንም ተመራማሪዎች ተናግረዋል።
በተጨማሪም በባዶ እግር መንቀሳቀስ ጥሩ ስሜት እንዲሰማን እንደሚያደርግም ተመራማሪዎቹ አስታውቀዋል።
በባዶ እግራችን በምንራመድበት ጊዜም የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖረን የሚያደርግ ሲሆን፥ በዚህ ጊዜም ከደም ዝውውሩ ጋር ሰውነታቸን በቂ ሀይል በማግኘት የሰውነታችን ክፍሎች እንዲነቃቁ ያደርጋል።
በቀን ውስጥ ቢያንስ ለ5 ደቂቃ ያከል በባዶ እግራችን መጓዝ ለልብ ህመህ እንዳንጋለጥ የሚረዳን መሆኑ የተነገረ ሲሆን፥ በተጨማሪም የምግብ መፈጨትን ለማስተካከል፣ የጭንቀት ስሜትን ለማሰወገድ እና የሰውነታችንን አቅም ማጣት ለመከላከል ይረዳናል።
በባዶ እግር ለመሄድ ጊዜ የማናገኝ ከሆነ ወይም የማንቸል ከሆነ ደግሞ እግራችንን እና እጃችንን ጠዋት እና ማታ በደንብ መታሸት /ማሳጅ/ መደረግ ይመከራል።
በዚህ መንገድ በመጠቀምም እግራችንን ባዶ በመሄድ የምናገኘውን የጤና ጠቀሜታዎች ማግኘት ይቻላል።
ተተርጉሞ የተጫነው፦ በሙለታ መንገሻ
Tran : FBC