Search

Monday, January 28, 2013

ኢቴቪ እና የአፍሪካ ዋንጫ

“በድብቅ አላስተላለፍኩም፤ በድርድር ላይ ነን” ኢቴቪ አለማየሁ አንበሴ በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ የሚገኘውን 29ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ በቀጥታ እያስተላለፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ስርጭቱን በድብቅ ሲያስተላልፍ እንደነበረ በይፋ ከተነገረ በኋላ የተለያዩ አስተያየቶችና ወቀሳዎች እየቀረቡበት ሲሆን ድርጅቱ በበኩሉ ጨዋታው እየተላለፈ ያለው በድብቅ አለመሆኑን እና እስከ አሁን ድረስ ድርድር እያደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በዕለቱ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በድብቅ እያስተላለፈ መሆኑን በሚመለከት በቴሌቪዥን ስክሪኑ ላይ የተጻፈው እና በኳስ ተንታኞች የቀረበው ተደጋጋሚ ወቀሳ ድርድር ላይ ያለው ድርጅት አቋም ነው ወይስ የጋዜጠኛው የሚለውን እያጠራ እንደሆነም ጠቁሟል፡፡ ኢቴቪ ውድድሩ ከመጀመሩ ቀደም ብሎ ከቴሌቪዥን ባለመብቱ ኩባንያ ጨዋታውን የማስተላለፍ መብት ለማግኘት ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ መጠየቁን አስታውቆ የተጠየቀው ክፍያ ተገቢ አይደለም በሚል ራሱን ጨምሮ በርካታ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች መቃወማቸውንና በድርድር ላይ መሆናቸውን አስታውቆ ነበር፡፡
በዚህ ሁኔታ ላይ እያለም ከመክፈቻ ሥነስርዓቱ ጀምሮ ሲያስተላልፍ ቆይቶ የኢትዮጵያና የዛምቢያ ጨዋታ በሚታይበት ወቅት የኢትዮጵያ ቡድን ጐል ማስቆጠሩን ተከትሎ ጨዋታው ይተላለፍበት የነበረው “አፌኔክስ” የተሰኘው የቴሌቪዥን ጣቢያ በስክሪኑ ላይ “ይህን ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ያለፍቃድ እያስተላለፈ ነው” የሚል የእንግሊዝኛ ጽሑፍ መልቀቁ ይታወቃል፡፡ ጽሑፉ ከተለቀቀ በኋላም በወቅቱ ጨዋታውን ሲዘግቡ የነበሩት ተንታኞች በተደጋጋሚ “ይህን ጨዋታ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ያለፍቃድ እያስተላለፈ ነው፡፡ ምናልባትም በሕግ ሊጠየቅ ይችላል” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ጣቢያው በሕግ መጠየቅ እና ቅጣትም እንዳለው እያወቀ ያለፍቃድ ማስተላለፉ ሳያንስ ፍቃድ በሌለውና ክፍያ ባልተፈፀመበት ፕሮግራም ላይ ስፖንሰር ሰብስቦ ማስተላለፍ ተገቢ አለመሆኑን አስተያየታቸውን ለአዲስ አድማስ የሰጡ የቴሌቪዥን ተከታታዮች ተናግረዋል፡፡ የቴሌቪዥን ፍቃድ ሳያወጡና ግብር ሳያስከፍሉ ተጠቃሚ መሆን በሕግ ያስቀጣል እያለ ራሱ ለሕግ ተገዢ አለመሆኑ አሳፋሪ ነው” የሚሉ መልዕክቶችም በማኅበራዊ ድረገፆች ላይ ሲተላለፉ ቆይተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት የመዝናኛና የስፖርት ዘርፍ የሥራ ሂደት መሪ አቶ ፍቅር ይልቃል ስለተፈጠረው ሁኔታ ለአዲስ አድማስ ሲያብራሩ፤ የጨዋታውን በቴሌቪዥን የማስተላለፍ መብት ከገዛው መቀመጫውን ቤኒን ካደረገው “LC2-Lancia” ድርጅት ጋር የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት እየተደራደረ ቀደም ሲል የተከናወኑትን አምስት የአፍሪካ ዋንጫዎች በደንበኝነት አብረው ሲሠሩ መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡

አቶ ፍቅር ቀደም ሲል የነበሩትን ድርድሮች በማሳያነት ሲጠቅሱም፣ ከድርጅቱ ጋር ሲሠሩ በነበረበት ወቅት መጀመሪያ አካባቢ ድርጅታቸው ይከፍል የነበረው 50ሺሕ ዩሮ (1ሚ.200 ሺ ብር) ሲሆን መጨረሻ ላይ ደግሞ የከፈለው 75ሺህ ዩሮ (1ሚ.800ሺ ብር) ነበር፡፡ በዚኛው ጨዋታ ግን ቀደም ሲል ከነበሩት ከ10 እጥፍ በላይ በመጨመር 750 ሺህ ዩሮ እና የአየር ሰዓት ክፍያ 250 ሺህ ዩሮን ጨምሮ በአጠቃላይ ወደ 1 ሚሊዮን ዩሮ (24ሚ.ብር) መጠየቁን አብራርተዋል፡፡ ዋጋው በዚህ መልኩ ሊጨምር የቻለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ በማለፉ ምክንያት ሊሆን ይችላል የሚል የግል አስተያየት እንዳላቸው የተናገሩት አቶ ፍቅር፤ ቀደም ካሉት ክፍያዎች በሚያስገርም ሁኔታ በመጨመሩ ምክንያት የድርድር ሂደቱ ሊራዘም እንደቻለ እና ጉዳዩ ዕልባት ሳያገኝ ጨዋታው መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ ድርጅታቸውም መልዕክቱ እስከተላለፈበት ጊዜ ድረስ እና አሁንም ጭምር (በትናንትናው ዕለት) በድርድር ላይ መሆናቸውን፣ ወደ መስማማቱም እየተጠጉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ጨዋታውም ከድርጅቱ ዕውቅና ውጪ በድብቅ ይተላለፍ የነበረ ባለመሆኑ ድርጅታቸው ላይ የሚደርስ የሕግ ተጠያቂነት እንደሌለ አስረድተዋል፡፡ ድርጅታቸው እስከዛሬ ይካሄዱ የነበሩ 10 የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎችን ሲያስተላልፍ ቆይቶ አሁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የተሰለፈበትን ጨዋታ ሳያስተላልፍ መቅረት የአድማጭ ተመልካቹን ፍላጎት አለማሟላት ነው ያሉት አቶ ፍቅር፤ እስከመጨረሻው ድረስ ተደራድረው ክፍያ በመፈፀም ኢቴቪ ጨዋታውን ማስተላለፉን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
 ምንጭ  : አዲስ አድማስ

Saturday, January 26, 2013

What’s in a Name in Ethiopia?

Kalkidan Hailemariam aka ‘Mitu’ and Linguistics Professor Zelealem Leyew


In Ethiopia, people have long used something called “house names.” They’re nicknames that family members give to one another. Traditionally, they have symbolic meanings. But the nature of those names is changing.
Kalkidan Hailemariam, a 19-year-old broadcast journalism student at the University of Addis Ababa, says her parents started calling her by her house name, Mitu, when she was about one year old.
“I didn’t know the meaning. Even my parents didn’t know what it means,” Kalkidan says.
“I really like [my house name]. When someone calls me Kalkidan, I don’t even turn my face,” she says.
Zelealem Leyew, a professor of linguistics at the University of Addis Ababa, says Mitu is a fairly typical house name for someone of Kalkidan’s age.
“We have these short and precise home names, like Tutu and Chuchu,” Zelealem says.
“And this, in linguistics, we call it reduplication – you just reduplicate or double a syllable,” he says.
Reduplication is common in many languages – from Chinese to Finnish to Maori. But Zelealem says it’s a new phenomenon in Ethiopia.
For centuries, Ethiopians have used long and colorful names, with symbolic meanings. They often bestow blessings or well wishes, or define the relationship between parent and child. Zelealem says that’s still the case in rural villages.
“If you go to the rural dwellers, they still enjoy giving names—these long names with meaning, with expressive power,” Zelealem says.
“They call them, Yene Geta, My Lord; Yene Gasha, My shield; Yene Shegga, My Beautiful or My Pretty,” he says.
Zelealem says no one knows exactly why these traditional house names are being replaced by shorter, cutesier names. But he suspects it has to do with Western influence. Ethiopia was relatively isolated from the West for centuries, but Europeans started coming here in large numbers in the 20th century.
“When they came to Ethiopia as missionaries, visitors, travelers, or scholars, they came with their languages,” Zelealem says.
“As a result of contact among speakers of different languages, we inherit names from other languages, and we donate, probably, names to other languages,” he says.
Zelealem says it’s a shame that so many Ethiopians are now using house names that don’t have meaning, and don’t have Ethiopian roots. But he acknowledges that there is a practical advantage to the shorter names – and that might explain their popularity in the cities.
“It is easier to call your baby girl Titi or Lili than Yelf Wagash or Yat’re Ida, which is relatively very long,” Zelealem says.
Eyosias Girma, a first-year student at the University of Addis Ababa, says all the kids in his family have short house names.
“My brother is Sweet,” he says.
“It’s because my mom used to eat a lot of sweet things when she was pregnant. My sister, she is Amen. Amen – let it happen.”
Eyosias says his own house name, Pio, doesn’t have a meaning. It was just something his sister started calling him. But the fact that it has no meaning doesn’t bother him. And he says it certainly doesn’t make him feel any less Ethiopian.

Friday, January 25, 2013

ኤፍቢአይ የመረጃ ዋና ቋቶችን በሚዘጋበት ጊዜ በሺዎች የሚቆጠሩ ደንበኞች ላይ የኢንተርኔት አገልገሎት መቋረጥ እንደሚደርስ ተገለጸ

ፍ ቢ አይ አንዳንድ የመረጃ መረብ ላይ ስርቆት የሚፈጽሙ ግለሰቦች  የሚጠቀሙበትን ዋና የመረጃ ቋቶች በሚዘጋበት ጊዜ በአብዛኛው በአሜሪካና በእንግሊዝ የሚገኙት ከ300 መቶ ሺ በላይ  የሚደርሱ ደንበኞች ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ሊደርስ  እንደሚችል  ገለፀ።

እ.ኤ.አ በህዳር  2011 ላይ  ኤፍ ቢ አይ ባካሄደው ዘመቻ  ቫይረስን  በመጠቀም ከ4 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ደንበኞች ላይ ጥቃት ለማደረስ የተዘጋጁ የመረጃ ቋቶችን  መለየቱን  ያስታወቀ ሲሆን፤ ደንበኞች የተለያዩ ድረ-ገጾችን በሚከፍቱበት ወቅት  ማስታወቂያዎችን እንዲመለከቱ በማድረግ ክፍያ ካልፈጸሙ ጥቃት እንደሚያደርሱባቸው  ይገልጻሉ፡፡

ማስታወቂያ በመልቀቅ በሚፈጽሙት የድረ-ገፅ ጠለፋና ደንበኞችን በማስገደድ በሚፈጽሙት ወንጀል ተግባር ከ14 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚያገኙ ሲሆን፤ በተጨማሪም በመረጃ ቋታቸው ቁልፍ የሆኑ የድህረ-ገጽ አውታሮችን በቁጥጥራቸው ሥር ያውላሉ።

እያንዳንዱ ድረ-ገጽ የራሱ የሆነ የአድራሻ ስም እንዳለው የሚታወቅ ሲሆን፤ ይህ አድራሻ ወደ ቁጥርነት በመቀየር ከዋና የመረጃ ቋት ጋር ግንኙነት በማድረግ ኮምፒውተሮች ድረ-ገጽን ለመጠቀም እንዲችሉ ያደርጋል፡፡

በዚህ መሃል የተደራጁት ወንጀለኞች ዋና የመረጃ ቋቱ ላይ ጥቃት በመፈጸም ኮምፒውተሮች የአድራሻ ስሞችን አስገብተው ወደ  ቁጥርነት የሚቀይሩበትን  ሂደት  እንዲስተጓጎል  ያደርጋሉ ፡፡

በቅርብ ጊዜ ውስጥ ኤፍቢአይ ወንጀለኞቹ ላይ ክትትል ለማድረግ ከካሊፎርኒያው  አይ ኤስ ሲ ኩባንያ ጋር እየሰራ ከመሆኑ በተጨማሪ ከሌሎች የደህንነት ተቋማት ጋር በመተባበር የደንበኞች ኮምፒወተሮች ላይ በመረጃ ቋት  አማካኝነት ጥቃት  መድረሱን በማረጋገጥና ተጠቂዎችን የማንቃት ሥራዎች እየተካሄዱ ይገኛሉ፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ተጠቃሚዎች ጥቃት እንደደረሰባቸው ለማወቅ የሚያስችል  ማጣሪያ በኢንተርኔት  በመለቀቁ  ከአራት ሚሊዮን  በላይ ደንበኞች ላይ  ይደርስ የነበረው ጉዳት  ወደ  300 ሺ መቀነሱን  በዋና የመረጃ ቋት  በሚደርሰው ጥቃቶች  ላይ  የሚሰሩት ድርጅቶች ያወጡት መረጃዎች ያሳያል።

በአብዛኛው በጥቃቱ ኢላማ የሆኑት ኮምፒወተሮች የሚገኙት በአሜሪካ ቢሆንም ሌሎች  እንደ ጣሊያን፣ ህንድ፣ እንግሊዝና ጀርመን የመሳሰሉ ሃገራት ውስጥ የሚገኙ ቀላል የማይባሉ የደንበኞች ኮምፒውተሮች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን መረጃዎች የሚጠቁሙ ቢሆንም በአይ.ኤስ.ሲ ኩባንያ ማረጋገጫ ማግኘት እንደሚያስፈልግም  ተጠቁሟል።

በአሁኑ ወቅት  የጥቃቱ ምንጭ ናቸው  ተብለው  የተለዩት ዋና የመረጃ ቋቶች  እ.ኤ.አ  ከሐምሌ 9 በኋላ እንዲዘጉ ስለሚደረጉ አንዳንድ የመረጃ ቋቶቻቸው አማካኝነት  የጥቃቱ ኢላማ የሆኑ ደንበኞች ድንገተኛ የሆነ የኢንተርኔት መቋረጥ እንደሚገኝማቸው ተገምቷል።

የኤፍ.ሰ ኪውር ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት ሲያን ሱሊቫን በጉዳዩ ላይ  አስተያየታቸውን ሲሰጡ ይህ ችግር ግልፅ እስኪሆን ድረስ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችልና  አንዳንድ የመረጃ ቋቶች በደንብ ተለይተው እስኪያዙ ድረስ ደንበኞች ድረ-ገጾቻቸውን  መጠቀም እንደሚያስቸገራቸውና ግማሹ የመረጃ ምንጭ ሰርቶ ሌላኛው በማይሰራበት ጊዜ ግር ማሰኘቱ እንደማይቀር ጠቁመዋል፡፡

Friday, January 18, 2013

Some facts about Ethiopian weavers






- Weaving is considered a male skill and weavers are almost exclusively male. Spinning is traditionally done by the women. It’s been hard for Ethiopians to move past these cultural norms.
- Weavers build their looms by hand, and the looms are made to be mobile. So the weaver can carry the loom to find work — nomadic style.
- When they set up a loom, a traditional weaver will dig a hole beneath the set-up for his feet, and the weaver will literally spend all day toiling in the dirt.
- Weavers are considered very low in social stature. If there was a caste system, they would be almost rock-bottom. The only vocations that are lower are blacksmiths and tanners.
- A weaver typically makes about 300-400 Birr per month. (100 Birr is about $5.50) This is not a livable wage.
But Ethiopian cotton is excellent. And the textiles Ethiopians produce are stunning.

አባባ ተስፋዬ(Ababa Tesfaye interview)

Ababa Tesfaye interview

ከአባባ ኮሚኩ እስከ አባባ ተስፋዬ
ባውዛ፡- አባባ ተስፋዬ በመጀመሪያ ለቃለ መጠየቃችን ፈቃደኛ በመሆንዎ በባዉዛ
ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በጣም እያመስገንኩ ወደ ጭዉዉት ልግባና

የት አካባቢ ነበር የተወለዱት?
አባባ ተስፋዬ- የተወለድኩት ከዱ የሚባል ሀገር ነው ባሌ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡
ባውዛ፡- ወደ አዲስ አበባ እንዴት መጡ?
አባባ ተስፋዬ፡- አባቴ ነው ሊያስተምሩኝ ያመጡኝ በኋላም ቀበና አካባቢ በአንድ የፈረንሳይ /ህርት ቤት ውስጥ ገባሁ አሁን ኮከበጽባህ ይባላል፡፡ አባቴ አቶ መንበረ ወርቅ ለሚባሉ ሰው አደራ ሰጥተውኝ ሄዱ በኋላ ጣሊያን ወደ
ሀገራችን ገባ፡፡
ባውዛ፡- አባትዎም በወቅቱ ለትምህርት ንቃት ነበራቸው ማለት ነው?
አባባ ተስፋዬ፡- እኔም የሚገርመኝ ይሄ ነው አባቴ በዚያን ጊዜ ምን አሰበው ወደ አዲስ አበባ እንዳመጡኝ በእውነት ይገርመኛል፡፡ በዚያን ጊዜ ለትምህርት ምን ያህል ጥሩ አመለካከት እንዳላቸው አስካሁን ይገርመኛል፡፡
ባውዛ፡- ስንት ዓመት ይሆኖት ነበር ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ?
አባባ ተስፋዬ፡- 12 ዓመት ቢሆነኝ ነው፡፡ ነገር ግን ገና 7 ዓመቴ ፊደል ጨርሼ ዳዊት መድገም ጀምሬ ነበር ጎበዝ ነበርኩ ቀልድም እይዝ ነበር፡፡
ባውዛ፡- በዚህ የሆናል አባትዎ ወደ አዲስ አበባ ያመጡዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- ይሆናል፡፡
ባውዛ፡- ከዚያ በኋላ ጣሊያን ገባ እርስዎስ ትምህርትዎን ቀጠሉ?
አባባ ተስፋዬ፡- የለም----የለም--- የጣሊያን ባሪያ ሆንኩ አለቀ፡፡ ታሪኩ ብዙ ስለሆነ ጽፈህ አትጨርሰውም፡፡ ለጣሊያን ባሪያ ብሆንም በኋላ ጣሊያኑን ፈንክቼ ወደ ሐረር
አመለጥኩ ሳቅ-----
ባውዛ፡- ታዲያ ወደ ቴአትሩ ዓለም እንዴት ተቀላቀሉ?
አባባ ተስፋዬ፡- ጣሊያኑን ፈንክቼ በባቡር ወደ ሀረር ከሄዱኩም በኋላ ጣሊያኖች ያሰሩት ራስ ሆቴል ገብቼ ስራ ጀመርኩ በኋላም ልዑል መኮንን ሆቴሉን ስለገዙት የሆቴሉ ኃላፊ ሆንኩ፡፡ እዛ ሆቴል እየሰራሁ ሳለሁ እንግሊዞች (ሱድ አፍሪካውያን) ወደ ሀገራቸው ሲሸኙ የሀገራቸውን ማርሽ አሰሙ፡፡ በኋላ የእኛ ሀገር ሕዝብ መዝሙር የሚያሰማ ባለመኖሩ ቆጨኝና በቃሌ የሀገራችንን ሕዝብ መዝሙር ዘመርኩ በዚህ ጊዜ
ጃንሆይ ‹‹ማነው?›› ብለው ጠየቁ የእነ ግራዝማች ጥግነህ፣ የእነቀኝ አዝማች ቤተሰብ
መሆኔ ተነገራቸውና ወደ አዲስ አበባ እንድመጣ አስደረጉ በነገራችን ላይ አባቴና የአባቴ
ቤተሰቦች ያለቁት ኦጋዴንና ባሌ ውስጥ ነው፡፡

ባውዛ፡- አባትዎ አሳሽ (አስገባሪ) ነበሩ ይባላል?
አባባ ተስፋዬ፡-አዎ አሳሽ ናቸው፡፡ በዚያን ጊዜ አሳሽ ማለት አልገብርም ያለውን
ቦታ ለራስ መኮንን ያስገብሩ ነበር፡፡ (የአፄ ኃይለሥላሴ) አባት እና ወደ ሐረርና ጨርጮ
አካባቢዎች ብዙ ዘመቻ አድርገዋል፡፡ ይሄን ብቻ ባወራህ 1 ሰዓትም አይበቃህም፡፡
ባውዛ፡- እንግዲህ የኢትዩጰያን ሕዝብ መዝሙር ዘመሩና አዲስ አበባ እንዲመጡ
ተደረገ ከዛስ ምን ሆነ?
አባባ ተስፋዬ፡- ተማሪ እያለሁ ጀምሬ የኢትዩጵያን ሕዝብ መዝሙር አውቅ ነበር
ጣሊያንም ከገባ በኋላ አሮጌ ፒያኖ አግቼ ተለማምጄአለሁ፡፡ በሆቴሉም ውስጥ ሙዚቃ
እሞክር ነበር፡፡ ከዛ 1937 . እንደ ኢትዩጵያ አቆጣጠር በሀገራችን ኪነጥበብን
ለማቋቋም አዋጅ ተነገረ፡፡ በኋላም ማዘጋጃ ቤት ተቋቁሞ ስለነበረ እዚያ ገባሁ፡፡ አስራ አንድ ወር ያለ ደመወዝ ሰራሁ፡፡ ደመወዝ
ያልጠየኩበት ምክንያት በንጉሱ ትዕዛዝ
መምጣቴን በማሰብ ነበር፡፡ መብልና
መጠለያ ግን ተመቻችቶልኝ ነበር፡፡
የሙዚቃ ትምህርቴን ከተማርኩ በኋላ
በዚያው ቴአትር ቤት አክተር ሆንኩ፡፡
ባውዛ፡- የሴት ገጸ ባህሪ ወክለው ይጫወቱ
ነበር፡፡ በዛን ጊዜ ደግሞ 18 ዓመት
ጎረምሳ ነበሩና እንዴት አድርገው ነው
የሴት ድምጽ ማውጣት የቻሉት?
አባባ ተስፋዬ፡- ቀላል ነው እንደሴት
መሆን አሁንም የሴት ድምጽ ማውጣት
እችላለሁ፡፡ ልበልልህ----ሳቅ-----የሴት
ድምጽ ብቻ ሳይሆን መንጎራደዱንም
እችልበታለሁ ላሳይህ----ሳቅ-----
ባውዛ፡- ከዛስ በቴአትሩ እንዴት ቀጠሉ?
አዲስ ተስፋዬ፡- ከዛማ 1944 . ወደ
ኮሪያ ሄድኩ ኮሪያም ሄጄ ‹‹ጠላቤቷን››
የተሰኘውን ቴአትር የሴት ገጸ ባህሪ
ተላብሼ በደንብ ሰራሁ፡፡ ቀሚስ ለብሼ
ብታየኝ ምኔም ወንድ አይመስልም ነበር
‹‹
ምናልሸኝ----!›› ያልኩ እንደሆን ሴትም
አስንቀ ነበር፡፡ በኋላም ብሔራዊ ቴአትር
1948 . ተከፈተ ድሮ መጀመሪያ
ማዘጋጃ ቤት የነበርን አክተሮች በሙሉ
ወደዚያ ተዛወርን የጃንሆይ ኢዩቤልዩ
በዓል ነበር፡፡ በደመቀ ስነ-ስርዓት ነበር
የተከፈተው ከዚያ በኋላ አክተር ሆኜ ስሰራ
ቆየሁ፡፡
ባውዛ፡- ከዛ በኋላ ወደ ኢትዩጵያ
ቴሌቭዥን እንዴት ገቡ?
አበባ ተስፋዬ፡- 1957 . በማዘጋጃ
ቤት ውስጥ የኢትዩጵያ ቴሌቭዥን
ሲመሰረት ነው የገባሁት በወቅቱ
የእንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤት ትመጣለች
ተብሎ ነው።
ባውዛ፡- የቴሌቭዥን ዝግጅቱ
የተጧጧፈው ሙዚቃም ስናጠና ነበር፡፡
በኋላም 1957 ህዳር 1 ቀን የኢትዩጵያ
ቴሌቪዥን የልጆች ኘሮግራም ተጀመረ፡፡
ኘሮግራሙ የተጀመረው ደግሞ በእኔ
ጠያቂነት ነበር፡፡ በወቅቱ የቴሌቭዥን
ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የነበሩት ብላታ
ግርማቸው ተክለሀዋሪያት ነበሩ፡፡ በወቅቱ
ቴክኒሻኖቹ ፈረንጆች ነበሩ፡፡ ብላታ
ግርማቸው የሕፃናት ኘሮግራም አሰፈላጊ
መሆኑን ስነግራቸው ይሄም አለ እንዴ
‹‹
ብለው ፈረንጁን አማከሩት ፈረንጁም
‹‹
ሰው አላችሁ›› ብሎ ጠየቀ በኋላ እኔ
ተመርጬ ስቱዲዮ ገባሁ፡፡
ባውዛ፡- የልጆች ኘሮግራም እንደጀመሩ
ሲያቀርቡ የነበሩት የኘሮግራም ይዘት ምን
ነበር?
አባባ ተስፋዬ፡- ተረት ነበር
የማቀርበው፡፡
ባውዛ፡- ተረቱን ከየት ነበር የሚያገኙት?
አባባ ተስፋዬ፡- ድሮ በልጅነቴ አባቴና
አያቴ ብዙ ተረት ይነግሩኝ ነበር፡፡ እኔ
ደግሞ የማስታወስ ችሎታዬ ከድሮ ጀምሮ
ትልቅ ነበር፡፡
ባውዛ፡- መቼ መቼ ነበር ኘሮራሙን
የሚያቀርቡት?
አባባ ተስፋዬ፡- ቅዳሜ፣ እሁድና ሰኞ
ነበር፡፡
ባውዛ፡- 1957 የተወለደ ሕፃን ዛሬ
ትልቅ ሰው ነውና በዛን ጊዜ የነበሩ ልጆች
ለኘሮግራሙ ያላቸው አስተያየት ምን
ይመስል ነበር?
አባባ ተስፋዬ፡- ዛሬ ወደ ውጭ አሜሪካ
የጋበዙኝ ሁሉ በዛን ጊዜ ሕፃን ነበሩ፡፡ከዛ
ጊዜ በኋላ የተወለዱ ብዙ ናቸው በዛሬ ጊዜ
በጣም እየረዱኝ ያሉት እነሱ ናቸው፡፡
ገንዘብ ይሰጡኛል ስልክ እየደወሉም
ያጽናኑኛል ወደ ኢትዩጵያ በሄዱ ቁጥር
ተረቶቼን ይገዛሉ በብዙ ነገር ያስቡኛል፡፡ የእኔን ተረቶችና ምክር እንደውለታ
ቆጥረው ያስቡኛል፡፡ ወላጆቻቸውም
እንዲሁ ያከብሩኛል፡፡ ልጆቻችንን
ከአልባሌ ስፍራ እንዲርቁ በማድረግዎት
እናመሰግንዎታለን ይሉኛል፡፡
ባውዛ፡- ለምን ያህል ጊዜ ነው በኢትዩጰያ
ቴሌቪዥን የልጆች ኘሮግራም የቀረቡት?
አባባ ተስፋዬ 42 ዓመት ያህል
ነው እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ የአክተርንት
ስራዬንም ደርቤ ነበር የምሰራው እና ለዚህ
ሁሉ ዓመት ልጆችን በተረት ስመክርና
ሳዝናና ቆይቼአለሁ፡፡
ባውዛ፡- መቼም በወጣትነትዎ ነው
ይሄንን ስራ የጀመሩትና ሲጀምሩም ‹‹አባባ
ተስፋዬ›› ነበር የሚባሉት ወይስ ሌላ ስም
ነበርዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- በፊት ጭምብል (ማክስ)
አድርጌም እሰራ ነበር መጠሪያዬም ‹‹አባባ
ኮሚኩ ነበር›› የሚባለው በኋላ በራሴ ስም
እንዲሆን ተደረገ፡፡
ባውዛ፡- ህፃናትን ለማዝናናት ሳይንሳዊ
ትምህርት ቀስመዋል እንዴ?
አባባ ተስፋዬ፡- በፍጹም በተፈጥሮዬ
ነው ፊቴን የምቀያይረው ደግሞም መርሳት
የሌለብህ አክተርም ጭምር ነኝ፡፡ ልጅም
ለመምከር እንደዚያ ፊትን መቀያየርም
ያስፈልጋል፡፡ የምናገረው በስሜት
በእንቅስቃስና ድራማቲክ በሆነ ነገር
ካልደገፍኩት ልጆች ይሰለቻሉ፡፡ ስለዚህ
ፊቴን በመቀያየር ተረቴን አቀርባለሁ
እንጂ ማንም አላስተማረኝም እግዚአብሔር
ነው የሰጠኝ የአባቴ ምክር የአያቴ ተረት
ነው ለዚህ ያበቃኝ ተማሪም እያለሁ
መሸለል መፎከር እወድ ስለነበር የቁጣ
የደስታና የሐዘን የፊት ቅርጽ ማሳየት
እችላለሁ፡፡
ባውዛ፡- 42 ዓመታት ያህል ከሰሩበት
የኢትዩጵያ ቴሌቭን የልጆች ክፍለ ጊዜ
ኘሮግራም ለምን ለቀቁ?
አባባ ተስፋዬ፡- መቼም ከልጅ የዋለ
ልጅ ነው ይባል የለ አንዲት ልጅ ተረት
ስተርት ያንን ምክንያት አደረጉና ‹‹ከዛሬ
ጀምሮ ኮንትራታችን አልቋል አሉኝ›› እሺ
ብዬ ወጣሁ፡፡
ባውዛ፡- በቃ በዚህ ምክንያት ስራዎትን
ለቀቁ ማለት ነው?
አባባ ተስፋዬ፡- እኔ የማውቀው
ይህንን ነው፡፡ የቀረውን ደግሞ ‹‹ለምን
ኮንትራቱን አቋረጣችሁበት›› ብለህ
እነሱን ጠይቃቸው እኔ በበኩሌ ምንም
የማውቀው ነገር የለም በወቅቱ ልጅቷ
ተረት ስትናገር ጠይቄአታለሁ ‹‹አንድ
ጋና እና አንድ ፈረንጅ ነበሩ ስትል አንድ
ጋና ነው ያለችው የዩኒሴፍ ተረት ነበር፡፡
እነርሱ ምን እንደተሰማቸው አላውቅም
ብቻ ይሄ ተረት እንደተላለፈ የስንብት
ደብዳቤ ሰጡኝ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ ኮንትራትዎ
አብቅቷል›› አሉኝ እሺ ብዬ እጅ ነስቼ
ወጣሁ፡፡
ባውዛ፡- እርስዎ ግን በስራው መቀጠል
ይፈልጉ ነበር?
አባባ ተስፋዬ፡- እንዴ እኔ የተፈጠርኩት
ለልጆች ነው በመጣሁ ጊዜ ሀገሩ በጋዜጣ
በስልክ ተጨናንቆ ነበር ምንም እንኳ
የስንብት ደብዳቤውን ሲሰጡኝ እጅ ነስቼ
ብቀበልም ህፃናቱ ለእኔ ካላቸው ፍቅርና
አክብሮት አንፃር ግን ሀዘን ይሰማኛል፡፡
ባውዛ፡- አሜሪካንን እንዴት ያይዋታል?
አባባ ተስፋዬ፡- አሜሪካ ሀያል ናት፡፡
የዓለም ንጉሥ ናት ሁሉ ነገር እጃ ላይ
ነው፡፡ እኔ ግን ሀያል ሀገር የምለው
ሀገሬን ነው፡፡ ኢትዩጵያን እወዳታለሁ፡፡
‹‹
ወፍ የሚጮኸው እንዳገሩ ነው›› ይባል
የለ ከዚህ ውጭ በልጅነታቸው እኔ
የመከርኳቸው በዚሁ በአሜሪካ ይገኛሉ፡፡
እነዚህ ሰዎች ዛሬ ታላላቅ ሰዎች ሆነዋል፡፡
ስለዚህ እኔም ከኢትዩጵያ መጥቼ
ከእነርሱ ጋር በመገናኘቴ ደስታዬ ወደር
የለውም፡፡ ወደ አሜሪካ ስመጣም ባዶ
እጄን አልመጣሁም፡፡ ከአራት መቶ በላይ
መጽሐፍት ይዤ ነው የመጣሁት፡፡ በሲዲ
የተዘጋጀ ተረት ይዤአለሁ፡፡ እና ጥሩ ጊዜ
እንደማሳልፍ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ባውዛ፡- ኢትዩጵያውያን ህፃናትን
እየመከሩ ያሳደጉት አባባ ተስፋዬ እርሶ
ግን ልጆች አልዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- አዎ አሉኝ፡፡ ሶስት
ልጆች ወልጄ ነበር፡፡ ሁለቱ ሞቱብኝ
አንዱ ግን አድጎ ልጅ ወልዶአል፡፡
እግዚአብሔር ይመሰገን ልጅ ከስሬ
አይጠፋም፡፡ አሁን አሥራ አንድ ቤተሰብ
አብረን እንኖራለን በዚህም ደስ ይለኛል፡፡
ባውዛ፡- በመጨሻ ምን የሚሉት ምን
የሚያስተላልፉት መልክት አልዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- ወደዚህ ወደ አሜሪካ
በዚህ እድሜዬ በመምጣቴ ደስተኛ ነኝ
እኔን ለመርዳት ብዙ ሰዎች ሲጥሩ
አያለሁ፡፡ ለእነሱም የላቀና የከበረ ምስጋና
እንዳለኝ በዚህ አጋጣሚ ንገርልኝ፡፡
አብዛኛውን ጊዜዬን ህፃናትን እየመከርኩ
በማሳለፌ ከምንም ባልተናነሰ ደስተኛ
ነኝ፡፡ የሚወዱኝ ልጆች ብዙ ናቸው፡፡
ወላጆቻቸው ቢሆንም ለእኔ ትልቅ
አክብሮት አላቸው፡፡ ባለፈው ታምሜ
ከሞት ላዳኑኝ ምስጋና ይድረሳቸው፡፡
በዚህ በአሜካ ተወልደው ያደጉ ህፃናትም
ሀገራቸውን እንዲያውቁ እንዲወዱ እና
ስለሀገራቸው የሚቆረቆሩ እንዲሆኑ
እንደምፈልግ ንገረልኝ፡፡ ሁሉምንም
እወዳቸዋለሁ፡፡ በተለይ በዚህ በአሜሪካ
የሚኖሩ ወላጆች ለልጆቻው የኢትዩጵያን
ተረት እንዲያስተምሩ በዚህ አጋጣሚ
እጠይቃለሁ፡፡ የአገራቸውን አኢትዮጵያን
ቋንቋ፣ባህልና ታሪክ እንዲያውቁ ማስተማር
ይኖርባቸዋል። ለዚሕም ወላጆቻቸው
ትልቅ አላፊነት አለባቸው፡፡
ባውዛ፡- ለኢትዩጵያ ቴሌቭዥን የልጆች
ክፍለ ጊዜን እንደሚሰናበቱ ሁሉ እኛንም
አሰናብቱን?
አባባ ተስፋዬ፡- አዎ አስታወስከኝ፡፡
‹‹
ደህና ሁኑ ልጆች----የዛሬ አበባዎች የነገ
ፍሬዎች----ደህና ሁኑ ልጆች----ደህና ሁኑ››
ባውዛ፡- አመሰግናለሁ አባባ ተስፋዬ
መልካም የአሜሪካ ቆይታ ይሁንልዎ፡፡
አባባ ተስፋዬ- እግዚአብሔር ይስጥልኝ
አመሰግናለሁ፡፡