Search

Friday, June 21, 2013

MESSAGE FOR THE SINGLE LADIES AND GENTS

A Very Touching Story..,,

A poor boy was in love with a rich man daughter….One day the boy proposed to her and the girl said…”Hey! Listen, your monthly salary is my daily hand expenses..How can I be involved with you..?

How could you have thought of that? I can never love you, so forget about me and get engaged to someone else at your level”

But somehow the boy could not forget her so easily…..Some time 10 years later they stumbled into each other in a shopping mall.

The lady again said….,”Hey.. ! You! How are you? Now I’m married and do you know how much my husband’s salary is..? $15,700 per month! Can you beat that? And he is also very smart”

The guy’s eyes got wet with tears on hearing those words from the same lady….

A few seconds later, her husband came around but before the lady could say a word her husband seeing the guy, said……
“Sir you’re here and you’ve met my wife..” Then he said to his wife,”This is my boss, I’m also one of those working on his $100 million project!

And do you know a fact my dear? My boss loved a lady but he couldn’t win her heart….That’s why he has remained unmarried since.

How lucky would that lady have been, if she had married this my boss now? These days, who would love someone that much he said all these to his wife.

በምንያህል ተሾመ ጉዳይ ለህዝብ ይፋ ያልሆነው ምስጢር!!

በቀጣዩ ዓመት በብራዚል በሚደረገው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ምድብ ማጣሪያ በምድብ አራት የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ባለፈው እሁድ አምስተኛ የምድብ ጨዋታውን በአዲስ አበባ ደቡብ አፍሪካን በማሸነፍ ለመጨረሻው ዙር ውድድር ማለፉን ቢያረጋግጥም በተጨዋችነት ተገቢነት ጉዳይ በእጁ የገባውን ዕድል መልሶ ማጣቱን የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ አረጋግጠዋል። ‹‹ስህተት ፈፅመናል›› ሲሉም ተናግረዋል። የብሄራዊ ቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ከሜዳ ውጪ ከቦትስዋና ጋር በሜዳችን ላይ በተደረገ ጨዋታ ሁለት ቢጫ ካርድ በማየቱ ምክንያት ከቦትስዋና ጋር በተደረገ የመልስ ጨዋታ ማረፍ ሲገባው ተሰልፎ በመጫወቱ ብሄራዊ ቡድኑ በእጁ የገባውን ዕድል መልሶ ሊያጣ መቻሉን አቶ ሳህሉ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት አስረድተዋል። በፊፋ ህግ አንድ ተጨዋች ሁለት ቢጫ ካርድ ከተመለከተ አንድ ጨዋታ ማረፍ ይኖርበታል። ይህን ደግሞ የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተከታትሎ ማስፈፀም አለበት፡፡ ፊፋ በተለያዩ ምክንያቶች ሳይልክ ቢቀር እንኳን አላሳወክም ተብሎ ሊጠየቅ አይችልም።

ይህም ሆኖ ግን ፊፋ ከቦትስዋናው ጨዋታ 14 ቀን ቀደም ብሎ ምንያህል በቅጣት መሰለፍ እንደሌለበት ለፌዴሬሽኑ አስታውቋል። ባለፈው ረቡዕ ደግሞ መከራከሪያ ነጥብ ካላችሁ በማለት ጉዳዩን በድጋሚ ለማየት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ይሁን እንጂ ፌዴሬሽኑ የመከራከሪያ ነጥብ በማጣቱ ዝምታን መርጧል፡፡ በፊፋ ህግ ለጥያቄው በሁለት ቀን ውስጥ ምላሽ ካልተሰጠ ቅጣቱ ትክክል እንደሆነ ተቆጥሮ ለተጋጣሚው ቡድን ፎርፌ ይሰጣል። በዚህ ህግና ስርዓት መሰረትም ኢትዮጵያ ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ የመጨረሻውን የምድብ ጨዋታ ውጤት መጠበቅ ግድ ሆኖባታል፡፡ ኢትዮጵያ አሁንም ከምድቡ ለማለፍ የተሻለው ዕድል አላት። ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በመረጃ ልውውጥ ችግር ምክንያት ስህተት ሊፈፀም እንደቻለና ለዚህም የቡድን መሪው አቶ ብርሃኑ ከበደ፤አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻውና የአሰልጣኝ ቡድኑ፤ምንያህል ተሾመና አቶ አሸናፊ እጅጉ በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ ቢጫና ቀይ ካርድን ተከታትሎ የማስፈፀምና የማሳወቅ ሀላፊነት ግን የማን እንደሆነ በግልፅ አልተገለፀም። በዋናነት ትኩረት ተሰጥቶት ሲነገር የነበረው ከፊፋ የተላከው መረጃ መድረስ ላለበት አካል ደርሷል አልደረሰም ነው። በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሁሉም ሃላፊነቴን ተወጥቻለው ከማለት ውጪ ችግሩ የእኔ ነው የሚል ወገን ግን አልተገኘም። በዚህም ምክንያት ፌዴሬሽኑ ጉዳዩን ይበልጥ አጠናክሮ በመመርመር በቅርቡ የቅጣት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አስታውቋል። በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ምንያህል ሁለት ቢጫ ለማየቱ መረጋገጫ ሆኖ የቀረበው ከፊፋ የተላከው መረጃ ብቻ ነው። ከኢትዮጵያ ወገን የቀረበ ወይም የተያዘ ምንም መረጃ የለም። እንደ ፊፋ ሁሉ የብሄራዊ ቡድኑ የአሰልጣኝ ቡድን ለፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ወይም ቴክኒክ ክፍል ቢጫና ቀይን በተመለከተ መረጃ ሊሰጥ ቢገባም አልሰጠም። ዋና መረጃ ሊሆን ይገባ የነበረውም ይህ የአሰልጣኝ ቡድኑ የሚያቀርበው መረጃ ነው። ይህ መረጃ ተይዞ ቢሆን ኖሮ ይህ ሁሉ ችግርና ውዝግብ ባልተፈጠረ ነበር። የመረጃ ልውውጡ ባህልና ስርዓት እንዲሁም የጋራ ተጠያቂነቱ ስለሚኖር ምንያህልን በቦትስዋና ጨዋታ ለማሳረፍ የፊፋን ደብዳቤ ባልጠበቅን ነበር፡፡ ቀድሞውኑ መረጃው ስለሚኖር ሰጥተኸኛል አልሰጠኸኝም የሚል ክርክር ባልተነሳ ነበር። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች ሁሌም ቢጫ ለማየታቸው እንደማረጋገጫ እየተደረገ ሲያዝ የነበረው ከፊፋ የሚላከው ደብዳቤ ነው። ግን ስህተት ነው፡፡ ፊፋ ዕሮብ ዕለት ለፌዴሬሽኑ የመከራከሪያ ነጥብ ካላችሁ በማለት ደብዳቤ የላከው ሀገሮች የራሳቸውን ቢጫና ቀይ ካርድ የመያዝ ሃላፊነትና ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ ምናልባት የዕለቱ ዳኛ እና ኮሚሽነር ሪፖርት ሲያደርጉ ቁጥር ወይም ስም ተሳስተው ከሆነ በሚል ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት ለማጣራት ነው። እዚህ ጋር ነገሩን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ዘንድሮ በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ቡና ክለብ ላይ የተከሰተውን እናንሳ ፌዴሬሽኑ የ1ኛ ዙር መጠናቀቅን አስመልክቶ በተደረገ ግምገማ ወቅት እያንዳንዱ ክለብ የተመለከተውን ቢጫ ካርድ ለየክለቦቹ ሰጠ በዚህ ሰነድ ላይ የቡናው ሲሳይ ደምሴ የተመለከተው ሦስት ቢጫ ነው ይላል የቡድኑ አሰልጣኞች የያዙት ደግሞ አራት ቢጫ ይላል ክለቡ ፅህፈት ቤት ጋር ያለው ሰነድ ጋር ሲጣራ ደግሞ በርግጥም አራት ቢጫ ሆነ እናም በቀጣይ ጨዋታ ሲሳይ ደምሴ ቡና ከጊዮርጊስ ሲጫወት ሌላ ቢጫ በማየቱ እንዲያርፍ ተደረገ። ይህ ሲሆን ታዲያ ፌዴሬሽኑ ሲሳይ ማረፍ አለበት ብሎ ደብዳቤ አላከም። ነገር ግን በደንቡ መሰረት ቡና ራሱ ተከታትሎ ማሳረፍ ስለነበረበት እንዲያርፍ አድርጓታል፡፡ የምንያህል ጉዳይም መሆን የነበረበት እንዲህ ነው። ከፊፋ በላይ መረጃው ሊኖር የሚገባው ፌዴሬሽኑ ጋር በተለይም የአሰልጣኝ ቡድኑ ጋር ነው፡፡ ምንያህል በቦትስዋና ጨዋታ ተገቢ ተጨዋች እንዳልሆነ ለማወቅ የፊፋን ደብዳቤ መጠበቅ ባላስፈለገ ነበር። ይህ ሃላፊነት በዋናነት ደግሞ ሊሆን የሚገባው የዋና አሰልጣኙ ነው፡፡ በየትኛውም ክለብ ያለው አሰራር ይህ ነው፡፡ ዋናው አሰልጣኝ ይህን ሃላፊነት መዝግቦ እንዲይዝ የጨዋታ ቀን ለረዳት አሰልጣኙ ወይም ለቡድን መሪው ይሰጣል። ከጨዋታው በኋላም ያንን በመቀበል በራሱ ሰነድ ላይ ያሰፍራል ግልባጩንም ከሌሎች የጨዋታ ሪፖርቶች ጋር አያይዞ ለቴክኒክ ክፍሉ ወይም ለፅህፈት ቤቱ ያሳውቃል፡፡ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ውስጥ የነበረው አሰራር ግን ከእዚህ የተለየ ነው፡፡ ዋናው አሰልጣኝም ሆነ ረዳቱና የቡድን መሪው የጨዋታ ቀን ቢጫና ቀይን በተመለከተ ምንም አይነት መረጃ እንደማይዙና ይህ ብቻ አይደለም ስለ እያንዳንዱ ጨዋታና ተጨዋች በተመለከተ ለፌዴሬሽኑ ሪፖርት እንደማያቀርቡና በፌዴሬሽኑ በኩልም የመጠየቁ ባህል እንደሌለ ባደረግነው ማጣራት ለማረጋገጥ ችለናል፡፡

አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው የብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ከሆኑ ሁለት ዓመት የሞላቸው ቢሆንም ማን ምን ያህል ተጫወተ የሚሉና መሰል ጥያቄዎች ቢጠየቁ መረጃ በግለሰቦች እንጂ በፌዴሬሽኑ የለም፡፡ ለብሄራዊ ቡድኑ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ይወጣል ያ ሁሉ ብር የወጣበት ውድድርና መረጃ ግን በስርዓትና በተደራጀ መልኩ ተይዞ አይቀመጥም፡፡ የብሄራዊ ቡድኑ ሃላፊነት ሙሉ ለሙሉ ለአቶ ሰውነት ቢሰጥም በተመዘገበው ጥሩም ሆነ መጥፎ ውጤት ዙሪያ የፌዴሬሽኑ ሃላፊዎች ከአሰልጣኙ ጋር በየጊዜው ግምገማና ውይይት አያደርጉም፡፡ እንዲያውም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን የብሄራዊ ቡድኑን የአሰልጣኞች ቡድን እንቅስቃሴ በቅርብ የሚከታተለው ከፌዴሬሽኑ ይልቅ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ነው፡፡ የፌዴሬሽኑ ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ ሰኞ ዕለት ከቀኑ 10፡00ሠዓት እስከ ምሽት 2፡30 ሠዓት ድረስ በጉዳዩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ውይይትና ግምገማ አድርጓል፡፡ በዚህ ወቅትም የምንያህልን ቢጫ በተመለከተ ፊፋ ከላከው ውጪ በአሰልጣኝ ቡድኑ አባላት ወይም በፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት የተያዘ መረጃ እንዳለ ጠይቋል። ከማንም ምንም ሊቀርብ ግን አልቻለም፡፡ የፌዴሬሽኑ አመራሮች በቁጣ የአሰልጣኝ ቡድኑን አባላት እና ፅህፈት ቤቱን እንዴት የራሳችሁን መረጃ አትይዙም ሃላፊነቱስ የማን ነው ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ በዚሁ ወቅትም ይህ ሃላፊነት የአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው መሆኑ ተገልፆል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ከቅጥር ውላቸው ጋር ተያይዞ በተሰጣቸውና ሐምሌ 1/2004ዓ.ም ፈርመው በወሰዱት የስራ መዘርዝር ተራ ቁጥር 20 በኢንተርናሽናል ውድድር ወቅት ቢጫና ቀይ ካርድን በተመለከተ ተከታትሎ መዝግቦ የመያዝና የማስወሰን ሃላፊነት የእሳቸው መሆኑ ሰፍሯል። አሰልጣኝ ሰውነት ግን የስራ መዘርዝሩን እንዳላዩትና ሃላፊነቱም የእሳቸው ሊሆን እንደማይገባ ይዘው እንደማያውቁና ወደፊትም እንደማይዙ ተናግረዋል የፌዴሬሽኑ ሃላፊዎችም በአሰልጣኙ ንግግር ክፉኛ በመቆጣት አምርረው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የእኛን ተጨዋቾች ብቻ ሳይሆን የተጋጣሚ ተጨዋቾችን ቅጣት ሳይቀር ተከታትለህ ልትይዝ ይገባል በማለት ሁሉም አቋም ሲይዙ አቶ ሰውነት ጉዳዩን እንዳለሳለሱት ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በጉዳዩ ዙሪያ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንቶችና ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው አስተያየት እንዲሰጡን ተንቀሳቃሽ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ብንደውልም ምላሽ ልናገኝ አልቻልንም። ሰኞ ዕለት በተደረገው ውይይትና ግምገማ ቢጫና ቀይ ካርድን መዝግቦ የመያዙ ሃላፊነት ለማን እንደተሰጠና መሠረታዊ ችግሩ ምን እንደሆነ ቢታወቅም ይህ ግን በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ይፋ አልተደረገም፡፡ በማንም በኩል ይፋ እንዳይደረግና በምስጢር እንዲያዝም ትዕዛዝ እንደተሠጠ ከታማኝ ምንጮቻችን ለማወቅ ችለናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በተፈጠረው ስህተት ዙሪያ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ትናንት የፌዴሬሽኑን ከፍተኛ ሃላፊዎች ጠርቶ አነጋግሯል፡፡ የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አብዲሳ ያደታ ትናንት ረፋድ ላይ የፌዴሬሽኑን ሃላፊዎች በፅህፈት ቤታቸው ረዥም ሰዓት በመውሰድ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያና መረጃ እንዲሰጡዋቸው ጠይቀዋል። ይሁን እንጂ ምን ውሳኔ እንዳሳለፉ ጥረት ብናደርግም ለማወቅ አልቻልንም።

Wednesday, June 19, 2013

Betty may Get kicked out of Big Brother Africa

Elikem Kumordzi, one of Ghana’s representatives in the ongoing Big Brother Africa The Chase reality show could be exiting the show come Sunday.

The Ghanaian has found his head on the chopping block after Monday’s nominations session, having received four nominations.

Elikem seemed to be on the lips of some of the Rubies housemates including his onetime crush, Tanzanian, Feza, who said Elikem is not being true to himself and the other housemates.

South African representative Angelo told Big Brother Elikem could not be trusted because he has also been trying to get people to vote for certain people and that did not go down well him.

Botswana’s Oneal also said his reason for nominating the Ghanaian was that he is guilty of being associated with Zimbabwean, Pokello, and that neither one of them can be trusted.

After nominations in the Rubies house Monday, Elikem and Malawian Natasha had four each while Elikem’s new love Pokello had five.

Lovebirds, Sierra Leonean Bolt and Ethiopian Betty are also up for possible eviction in the Diamond house. Bolt had four nominations while Betty had three. Kenyan, Annabel and Tanzanian, Nando had three nominations each.

Ghana's other representative, Selorm (Selly) Ghalley was however lucky as she received only one nomination. Pokello nominated her due to their never-ending feud.

As stipulated in the show’s rules, the Head of House in the two houses has the power to save or replace nominated housemates after the nominations session.

Bassey, Head of House in the Rubies after pondering over the nominated housemates opted to save Pokello and replaced her with Oneal.

Annabel, Head of House in the Diamond House settled on saving herself from possible eviction. She put up Motamma in her place.

This means that at least two of seven nominated housemates - Bolt, Natasha, Oneal, Betty, Elikem and Motamma – will be packing their bags home come Sunday.























Tuesday, June 18, 2013

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፊፋን ክስ አመነ




አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሰኔ 1 ቀን 2005 ዓ.ም ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡
ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ  አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ከፊፋ ደብዳቤ ደርሶት እንደነበርም ገልጿል፡፡
የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህ መሰረት የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ ፣ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ፣ ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ እና የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች ጥፋተኛ ተብለዋል።
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በጥፋተኞቹ ላይ በቅርቡ ተገቢውን ቅጣት በመውሰድ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የቡድኑ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ፥ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በጨዋታውም አሸንፈን ወደ አለም ዋንጫ እንደምንሳተፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል አሰልጣኙ፡፡
በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ እና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣትም ያስጥላል፡፡

Monday, June 17, 2013

Public Opionion on Betty and Bolt-DW.DE | 14.06.2013

ዶ/ር ቴዎድሮስ ከግብፁ አቻቸው ጋር ባደረጉት ውይይት ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ቀሩ

ዲስ አበባ፣ ሰኔ 10 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከግብፁ አቻቸው ሞሃመድ ካመል አሚር ጋር ተወያዩ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በማለዳው የውይይት ክፍለ ጊዜያቸው ከስምምነት መድረስ ሳይችሉ ተለያይተዋል።

ከሰዓት በኋላም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ  እንደሚወያዩም ይጠበቃል።

ሌሎች የተፋሰሱ ሃገራት የማይቀበሉትንና ግብፅ በቅኝ ግዛት ዘመን በ1929 እና1959 በተደረጉ ውሎች መሰረት የዓባይን ውሃ በበላይነት የልጠቀም ጥያቄን ታሰማለች።

Thursday, June 13, 2013

Man injured when police tried to shoot Hayna

ኮንዶሚኒየም ፎቅ ላይ የወጣውን ጅብ ለማስወጣት በተከፈተ ተኩስ አንድ ወጣት ቆሰለ

በመስከረም አያሌው
በሐያት ኮንዶሚኒየም ሶስተኛ ፎቅ ላይ ወጥቶ አልወርድም ያለውን ጅብ ለማስወጣት በተተኮሰ ጥይት አንድ ወጣት ቆስሎ ሆስፒታል ገባ።
በህንጻው ላይ የሚኖሩ የአይን እማኞች እንደገለፁት፤ ከትናንት በስቲያ ከምሽቱ አራት ሰዓት ገደማ ወደ ህንጻው በማምራት ሶስተኛ ፎቅ አንድ መኖሪያ ቤት በር ላይ የተኛውን ጅብ ትላንት ለማስወጣት አምስት ጥይቶች ተተኩሰው ጅቡ የተገደለ ሲሆን፤ በአካባቢው የነበረ አንድ ወጣት በነጠረ ጥይት ሆዱ ላይ ተመትቶ ሆስፒታል ገብቷል። ፎቁ ላይ የወጣው ጅብ እስከ ትናንት ከረፋዱ አራት ሰዓት ገደማ ድረስ እዚያው ፎቁ ላይ መቆየቱን የተናገሩት ነዋሪዎቹ ጅቡን እንዳዩት በማስፈራራት ለማስወጣት ቢሞክሩም አልቻሉም። ነዋሪዎቹ ለፖሊስ ስልክ ደውለው ያሳወቁ ሲሆን፤ ፖሊስም “ለአካባቢ ጥበቃ በስልክ ጉዳዩን አሳውቀናል” በማለቱ ጅቡ እዚያው ሊያድር ችሏል።
ጅቡ በህንጻው ላይ እስካለበት ጊዜ ድረስ ፎቁ ላይ የነበሩ ነዋሪዎች ከቤታቸው ሳይወጡ መቆየታቸውን የገለፁ ሲሆን፤ ትናንት ጠዋት ላይም አንዳንድ ወላጆች በዱላ እና በአንዳንድ ነገሮች ጅቡን እየተከላከሉ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላካቸውን ገልፀዋል። ጅቡ በህንፃው ላይ ሌሊቱን ሙሉ በማሳለፉ ከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ ሆነው ማደራቸውን የገለፁት የህንጻው ነዋሪዎች፤ ጅቡ ከቦታው እስከተነሳበት ሰዓት ድረስም እንደልባቸው በህንጻው ላይ ለመንቀሳቀስ መቸገራቸውን ገልጸዋል። በህንጻው ላይ እንዲህ አይነቱ ነገር ሲፈጠር ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን የገለፁት ነዋሪዎቹ፣ በሁኔታው በጣም መደናገጣቸውን ገልጸዋል።
ጅቡ በህንጻው ላይ ሌሊቱን ሙሉ ካሳለፈ በኋላ እስከ ትናንት ረፋድ አራት ሰዓት ድረስ እዚያው የቆየ ሲሆን፤ አራት ሰዓት ተኩል አካባቢ በፖሊስ አማካይነት በአምስት ጥይቶች ተገድሎ ከህንጻው ላይ ሊወርድ ችሏል።n
(ምንጭ፡-ሰንደቅ ጋዜጣ 8ኛ ዓመት ቁጥር 405 ሰኔ 5/2005)

Thursday, June 6, 2013

ነባር የ20/80 ቤት ተመዝጋቢዎች ዝርዝር ይፋ ሆነ

የጋራ መኖሪያ ቤቶች ምዝገባ በወረዳና በተመረጡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ይካሄዳል

የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፈላጊዎች በወረዳና በተመረጡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ምዝገባ እንደሚያካሄዱ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዛሬ ግንቦት 28/2005 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ በአዲስ አበባ በተለያዩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መርሃ ግብር የሚመዘገቡ የከተማዋ ነዋሪዎች በወረዳና በተመረጡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መሆኑን ገልጿል፡፡
ነባር ተመዘጋቢዎች ዳግም እንዲመዘገቡ የተፈለገው መረጃውን ለማጥራትና የቤት ፍላጎታቸውን መቀየር ለሚፈልጉ ለማመቻቸት ነው ብለዋል በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የመኖሪያ ቤቶች ልማትና የመንግስት ህንጻዎች ኮንስትራክሽን ዘርፍ ሀላፊ አቶ አማረ አስግዶም፡፡
የመንግስት ሰራተኞች 20 በመቶ ቅድሚያ የማግኘት እድል ተሰጥቷቸዋል፡፡ ለመመዝገብ ሲሄዱም የቀበሌ መታወቂያ ከሌላቸው የታደሰ የሰራተኛ መታወቂያ መያዝ እንዳለባቸው አቶ አማረ ተናግረዋል፡፡
በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በውክልና በ40/60ና በቤቶች ስራ ማህበራት መርሃ ግብር ብቻ መመዝገብ ይችላሉ፡፡
ከሰኔ 3 እስከ ነሐሴ 17/2005 ዓ.ም በ10/90፣ 20/80 አዲስና ነባር፣ በቤቶች ስራ ማህበራትና በ40/60 ቤት ፈላጊዎች ምዝገባ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ቅጾች በአዲስአበባ ቤቶች ልማት ኤጀንሲ መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን መንግስቱ ተናግረዋል፡፡
በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ኤጀንሲው ከሚያቀርባቸው የመመዝገቢያ ቅጾች ውጭ ቅጾች እየተሸጡ በመሆኑ ቤት ፈላጊዎች በምዝገባ ወቅት በመመዝገቢያ ወረዳዎች በሚሰጣቸው ቅጾች ብቻ መጠቀም እንዳለባቸው አቶ መስፍን አሳስበዋል፡፡
ቤት ፈላጊዎች ለምዝገባ ከመምጣታቸው በፊት የቁጠባ ሂሳብ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መክፈት የግድ መሆኑንና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚታየውን መጓተት ለማስተካከልም እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ምዝገባው በከተማዋ በ116 ወረዳዎችና ከ177 በላይ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በዚህ የበጀት አመት 95 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ ሲሆን 24 ሺህ ቤቶች ተጠናቀዋል፡፡

ከሰኔ 3/2005 ዓ/ም ጀምሮ በሚካሄደው ምዝገባ ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን በላይ ቤትፈላጊዎች ይመዘገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ፡፡
ሪፖርተር ፡-አዝመራው ሞሴ

Wednesday, June 5, 2013

ለቤት ምዝገባ የሚያስፈልገውን የባንክ ሂሳብ ለመክፈት የሚስተዋለውን ሰልፍ ለማቅለል መፍትሄ ማዘጋጀቱን ባንኩ ገለፀ


ኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በ10/90 እና በ20/80 የመኖሪያ ቤት መርሃ ግብር መሰረት  ለመመዝገብ የሚያስፈልገውን ዝግ የባንክ ሂሳብ ለመክፈት በየቅርንጫፎቹ እየተስተዋለ ያለውን ሰልፍ ለማቅለል መፍትሄ እያዘጋጀሁ ነው አለ፡፡
ባንኩ  እንዳለው የሚስተዋለውን ረዥም ሰልፍ ለማስቀረት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከሁለት ሰአት እስከ ምሽቱ 11 ሰአት  የሚካሄደውን ምዝገባ በምሽትም ማድረግና እሁድን ተጨማሪ የስራ ቀን ማድረግም ከመፍትሄዎቹ መካካል ናቸው፡፡
ያም ሆኖ ህብረተሰቡ እስከ ሰኔ 21 ድረስ ዝግ ሂሳቡን መክፈትና ጎን ለጎንም ምዝገባውን በማካሄድ ሰልፉን ማቅለል ይችላልም ተብሏል፡፡
ባንኩ በትናንትናው እለት የቁጠባ ደብተር መስጠት የጀመረ ሲሆን ፥ በእለቱም ከ14 ሺህ የሚበልጡ ሰዎች የቁጠባ ሂሳብ ከፍተዋል፡፡ ይህ ቁጥር እስከዛሬ ረፋድም 40 ሺህ መድረሱን የባንኩ ባለስልጣናት ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ቁጥር ውስጥም 2 ሺህ የሚሆኑት ብቻ ለ10/90 ሲመዘገቡ ቀሪዎች ደግሞ 20/80ን ምርጫቸው አድርገዋል ተብሏል፡፡
ሰኞ ለሚጀመረው የቤቶች ምዝገባ ከ4 ሺህ በላይ መዝጋቢ ሰራተኞች የተዘጋጁ ሲሆን ፥ በመብራት መቋረጥ ምክንያት ምዝገባው እንዳይቋረጥም በየምዝገባ ጣቢያዎቹ ጀነሬተሮች ተዘጋጅተዋል፡፡
የ 10/90 የቤት ፕሮግራም ከዚህ በፊት ያልነበረ በመሆኑ ፥ በዚህ የቤት መርሃ ግብር የሚመዘገቡ ነዋሪዎች በሚቀጥለው አመት በሚጠናቀቁት  24 ሺህ ቤቶች ቅድሚያ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
በነዚህ የቤት መርሃ ግብሮች የሚመዘገቡ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም በሚገኙበት አገር የገንዝብ ኖት እንዲቆጥቡም በአዲስ አበባ ቤቶች ኤጀንሲ በኩል መልእክት ተላልፏል፡፡

Monday, June 3, 2013

በአዲሱ የቤት ፈላጊዎች ምዝገባ ህገወጦችን ለጠቆመ 15 በመቶ ወሮታ ይከፈለዋል

የምዝገባ መረጃዎቹ በጠ/ሚኒስትሩ ቢሮ የመረጃ ማጠራቀምያ ቋት ይገባሉ
የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ባወጣው አራት አይነት የመኖሪያ ቤቶች ምዝገባ፤ ህገወጥ መረጃዎችን ያቀረቡና በህገወጥ መንገድ የተመዘገቡ ወገኖች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ ያስታወቀ ሲሆን፣ ህገወጦችን ለሚጠቁሙ ዜጐች 15 በመቶ ወሮታ የሚከፈልበት አሠራር ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መሥፍን መንግስቱ ከትናንት በስቲያ ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጡት ማብራሪያ፤ ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ችግር በሚታይባት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተጀመረው ፕሮግራም ይህ አብዛኛውን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ እንደሚታሰብ ገልፀዋል፡፡
የከተማዋ ነዋሪዎች በእኩልና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ የቤት ችግራቸውን እንዲያቃልሉ ታስቦ በከፍተኛ ጥንቃቄ የቤት ፈላጊዎች ምዝገባው እንደሚካሄድ ጠቁመው፤ በህገወጥ መንገድ ለመመዝገብ በሚሞክሩና ከወጣው መስፈርት ውጪ ተመዝግበው በሚገኙ ዜጐች ላይ የማያዳግም ጥብቅ እርምጃም እንደሚወሰድ ተናግረዋል፡፡ እነዚህን ህገወጦች ለሚመለከተው አካል ለሚጠቁሙ ወገኖችም የ15% ወሮታ ለመክፈል የሚያስችል አሠራር ለማውጣት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አቶ መስፍን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ ምዝገባው በከፍተኛ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች የሚከናወን መሆኑን የተናገሩት ሃላፊው፤ መረጃዎቹ በኔትወርክ እንዲያያዙና በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ በሚገኝ የመረጃ ማጠራቀሚያ ቋት ውስጥ እንዲገቡ ለማድረግ የሚያስችል አሠራር መደራጀቱንም ገልፀዋል፡፡
መስተዳድሩ የመኖሪያ ቤት ፈላጊዎች የመመዝገቢያ ቀናትን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ ቤት ፈላጊዎች በተሰጠው የጊዜ ገደብ ብቻ ቀርበው እንዲመዘገቡ አሳስቧል፡፡ በወጣው ፕሮግራም የ10/90 እና 20/80 ወይም የኮንዶሚኒየም ቤቶች ተመዝጋቢዎች ከሰኔ 3 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 21 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ምዝገባቸውን የሚያካሂዱ ሲሆን፣ በ1997 ዓ.ም ተካሂዶ በነበረው የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምዝገባ ተመዝግበው እስከ አሁን ድረስ እጣው ያልወጣላቸው ዜጐች በዚህ ምዝገባ እንደ አዲስ ሊመዘገቡ እንደሚገባም ተገልጿል፡፡ የቀድሞ የኮንዶሚኒየም ምዝገባ በአዲሱ ምዝገባ ተሻሽሎ የሚከናወን ሲሆን ከዚህ በኋላ የ1997 ዓ.ም ምዝገባ ዋጋ እንደማይኖረው ተጠቁሟል፡፡
ቤት ፈላጊዎች ከተመዘገቡ በኋላ በድጋሚ በሚካሄደው የማጣሪያ ምዝገባ የጣት አሻራ እንዲሰጡ እንደሚደረግና ለዚህም የሚያገለግሉ የመሣሪያዎች ግዢ እየተከናወነ እንደሆነ ዋ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ተመዝጋቢዎች እንደየሚመዘገቡበት የቤት ልማት ዓይነት መቆጠብ የሚገባቸውን የገንዘብ መጠን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ በመቆጠብ የባንክ ደብተር መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ነባር የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች፣ በአዲሱ ምዝገባ ለባለ ሶስት መኝታ ቤት 685 ብር፣ ለባለ ሁለት መኝታ ቤት 561 ብር፣ ለባለ አንድ መኝታ ቤት 274 ብር እንዲሁም ለስቱዲዮ 151 ብር በቅድሚያ ሊቆጥቡ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ ለአዲሱ የ20/80 ወይም የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምዝገባ ለባለ ሶስት መኝታ ቤት 489 ብር፣ ለባለ ሁለት 401 ብር እንዲሁም ለባለ አንድ 196 ብር መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡ በቀድሞ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምዝገባ ተመዝግበው እጣ ያልወጣላቸውና በዚህ ምዝገባ እንደ አዲስ የሚመዘገቡ ነባር ተመዝጋቢዎች ከአዲሶቹ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንደሚስተናገዱም ተገልጿል፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች የተዘጋጀው የ10/90 የስቱዲዮ ቤቶች ደግሞ 187 ብር በቅድሚያ መቆጠብ የሚገባ ሲሆን፣ የእነዚህ ቤቶች ግንባታ በአብዛኛው እየተጠናቀቀ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ የ40/60 ቤቶች ምዝገባ ተጠቃሚ የሚሆኑት የተሻለ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች አካላት እንደሆኑ የተናገሩት አቶ መስፍን፤ ሙሉ ክፍያ ለሚከፍሉ ተመዝጋቢዎች ቅደሚያ እንደሚሰጥም ጠቁመዋል፡፡ የእነዚህን ቤቶች ምዝገባ በተመለከተ በባንክ በኩል መመሪያዎች ወጥተው ተፈፃሚ እንደሚደረጉም ሃላፊው ገልፀዋል፡፡ የማህበራት ምዝገባም በቡድን እየተደራጁ በሚመጡ ወገኖች ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመው፤ በምዝገባ ወቅት የቤቱ ዋጋ 50% እና መሬት ተዘጋጅቶ የግንባታ ፈቃድ ከመሰጠቱ በፊት 50% በዝግ ሂሳብ የሚቀመጥ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡ ለ40/60 ቤቶች ምዝገባው ከነሐሴ 6 እስከ ነሐሴ 17 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ የሚከናወን ሲሆን ማህበራት ደግሞ ከሐምሌ 15 ቀን እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ምዝገባቸውን እንደሚያከናውኑ ተጠቁሟል፡፡ በአዲሱ የቤት ፈላጊዎች ምዝገባ በቀን ከ100ሺ በላይ ሰዎች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አቶ መስፍን ተናግረዋል፡፡ የመንግስት ሠራተኞችን በተመለከተ በልዩ የምዝገባ አሠራር በየመ/ቤቶቻቸው በኩል እንዲከናወን መወሰኑም ተገልጿል፡፡

Saturday, June 1, 2013

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ ወደቆ ያገኘውን 3.4 ሚሊዮን ብር ለባለቤቱ አስረከበ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአንድ መንገደኛ የጠፋ 184 ሺህ ዶላር ወይም ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ  ለባለቤቱ አስረከበ፡፡
በኢትዮጵያ አየር መንገድ የጽዳት ስራ የሚሰራው ብርሃኑ ጀምበሩ የተባለው የ21 አመት ወጣት ሥራውን ሲያከናውን የተጠቀለለ እቃ ያገኛል ፥ብርሃኑ ጥቅሉ  ገንዘብ መሆኑን ቢያቅም ለበላይ ኃላፊዎች ማስረከቡን ይናገራል፡፡
የገንዘቡ ባለቤት በኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ንግድ የተሰማሩና ዜግነታቸው ጋምቢያዊ የሆነው መንገደኛ ወደ ሆንግ ኮንግ ጉዞ ሲያደርጉ ባለፈው ማክሰኞ ምሽት ነበር በተሳፈሩበት አውሮፕላን ላይ ገንዘባቸውን ረስተው የወረዱት፡፡
ለክፍያ ያዘጋጁት ገንዘብ  ከአንጎላ ዋና ከተማ ሉዋንዳ ተሳፍረው ሆንግኮንግ እስኪደርሱ ድረስም መጥፋቱን  አላወቁም ነበር፡፡ግለሰቡ ገንዘባቸው መጥፋቱን ባወቁ ቅፅበት ግን፥ ለአየር መንገዱ አግባብ ባለው መስመር ገንዘባቸው መጥፋቱን ያሳውቃሉ፡፡
በዚህም በትናንትናው እለት ካሉበት ቦታ መጥተው ገንዘባቸውን ለመረከብ በቅተዋል፡፡በኢትዮጵያ አየር መንገድ ታሪክም ይህን የሚያክል ከፍተኛ ገንዘብ ለባለቤቱ ሲመለስ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው ተብሏል፡፡