Search

Saturday, March 30, 2013

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸውን በሄሊኮፕተር ያካሄዱት ጥንዶች

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸውን በሄሊኮፕተር ያካሄዱት ጥንዶች

ሙሽሮቹ "የጋብቻ ሥነ ሥርዓታችንን በሄሊኮፕተር ያካሄድነው ሞልቶን ተርፎን ሳይሆን የኢትዮጵያን የዕድገትና የለውጥ ሂደት ለኢትዮጵያውያንና ለመላው ዓለም ለማሳወቅ ነው" ብለዋል፡፡

"ኢትዮጵያ በዓለም ላይ የምትታወቀው በረሃብና በድርቅ ነው" የሚሉት ሙሽሮቹ " በአሁኑ ወቅት ግን ኢትዮጵያ ዓለምን በሚያስደምም ሁኔታ እያደገች መሆኗንና የተለየ ገጽታ እንዳላት ለማሳወቅ በተለየ ሁኔታ የጋብቻ ሥነ ሥርዓታችንን በሄሊኮፕተር ለማድረግ ችለናል፡፡" ነው የሚሉት ሙሽሮቹ ።

የጋብቻ ሥነ ሥነ ሥርዓታቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ በሄሊኮፕተር ያካሄዱት አቶ ሙሉቀን ፋንታዬ ወይም በቅጽል ስሙ / ሉክ/ እና ወይዘሪት ወይንሸት ሙሉነህ ውይም በቅጽል ስሟ /ወይኒ/ ናቸው፡፡

ሉክ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ ሙያዎች ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ወይኒ ደግሞ የአፄ ቴዎድሮስ አራተኛ የልጅ ልጅ ነች፡፡


በሊሞዚን መኪኖች በትልቅ ሆቴል ከሚካሄድ ቅልጥ ያለ የሠርግ ሥነ ሥርዓት ያነሰ ወጪ እንዳወጡ የሚናገሩት ሙሽሮቹ ፥ በጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸው ላይ እንዲታደም የጠሩት ሰው ቁጥር 150 ያህል ብቻ ነው፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ

Thursday, March 28, 2013

ሁለት እጅ አልባዋ አብራሪ ጄሲካ ሰኞ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ልምዷን ታካፍላለች


ሁለት እጅ አልባዋ አሜሪካዊትአውሮፕላን አብራሪ ጄሲካ ኮክስ ቻምቤሌይን የፊታችን ሰኞ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ንግግር ታደርጋለች።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ እንደገለጸው ፥ በተፈጥሮ ሁለት እጆቿን ያጣችው የ32 ዓመት ወጣት በዩኒቨርሲቲው ለ300 ተማሪዎች መጋቢት 23 ቀን 2005 ንግግር ታደርግላቸዋለች።
በቀስቃሽ ንግግሮቿ የምትታወቀው ጄሲካ  ወደ ኢትዮጵያ የምትመጣው ሃንዲካፕ ዓለም አቀፍ በተባለው ግብረ ሰናይ ድርጅትና በአሜሪካ ዓለም የልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤይድ) ትብብር ነው።
ጄሲካ በመላው ዓለም እንድትታወቅ ያደረጋት ፥ እጆች ሳይኖሯት አውሮፕላን ለማብረር በመቻሏና ለዚህም የአብራሪነት ፈቃድ ማግኘቷ ነው።
በአሪዞና ግዛት ተስከን የተወለደችው ጄሲካ ከጽንስ ጀምሮ እጆቿ የእግርንም ባህርይ ይዘው በመወለዷ  ፥ ለምታከናውናቸው ተግባራት ችግር እንደማይፈጥርባት መረጃዎች ያመለክታሉ ፤ በዚህም የምትፈልገውን ሁሉ በእግሮቿ ለማድረግ እምብዛም አትቸገርም።
ሃንዲካፕ ዓለም አቀፍ ፥ አካል ጉዳተኛ ሕጻናት ከትምህርት እንዳይገለሉ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም መግለጫው አመልክቷል።

Wednesday, March 20, 2013

ሲሳይ ባንጫ በእሁዱ ጨዋታ አይሰለፍም

በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ጋር በነበራት 3ኛ የምድብ ጨዋታ ላይ የቀይ ካርድ የተመለከተው ሲሳይ ባንጫ ፥ በካፍ በመቀጣቱ ቡድኑ እሁድ ከቦትስዋና ጋር በሚኖረው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ አይሰለፍም።

በሌላ በኩል ቦትስዋና ማላዊን በሜዳዋ አስተናግዳ 1 ለ 0 በሆነ ውጤትያሸነፈች ሲሆን ፥ ቡድኑ ከኢትዮጵያ አቻው ጋር ላለበት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ነገ አዲስ አበባ ይገባል።
ኢትዮጵያዊው አጥቂ ሳላዲን ሰኢድም ከብሄራዊ  ቡድኑ በቀረበለት ጥሪ መሰረት  ዛሬ ቡድኑን የሚቀላቀል ይሆናል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከትናንት ወዲያ ጀምሮ ልምምድ መጀመሩ የሚታወስ ነው።

Monday, March 18, 2013

አማርኛ በቻይና ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሊሰጥ ነው

በቤጂንግ  የውጭ  ትምህርቶች ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ  ቋንቋን ማስተማር የሚያስችለውን ስምምነት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር ገብቷል ።
ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች ስምምነቱን ባለፈው ሳምንት  ተፈራርመዋል ።
በስምምነታቸው መሰረትም አማርኛ  ቋንቋ ከሚቀጥለው መስከረም ወር  ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው  መሰጠት ይጀመራል ።
የአዲስ  አበባ  ዩኒቨርሲቲም የቻይና  ቋንቋ  ስልጠና  ፕሮግራሙን  ወደ መጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ይሆናል ።
የትምህርት መርሃ ግብሩን ለመጀመርም ዛሬ  አዲስ አበባ  ላይ  የስምምነት ፊርማ ይፈፀማል ።

ቅዱስ ጊዮርጊስ የማሊውን ጆሊባ 2 ለ 0 አሸነፈ

ለአፍሪካ ሻምፕዮን  ሊግ ማጣሪያ ዛሬ አዲስ አበባ ስታዲየም ቅዱስ ጊዮርጊስና የማሊው ጆሊባ የተገናኙ ሲሆን ፥ ቅዱስ ጊዮርጊስ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል ።

ለቅዱስ ጊዮርጊስ ግቦቹን ያስቆጠሩት ከእረፍት በፊት ዮናታን ብርሃነና ከእረፍት በኋላ ፍፁም ገብረማርያም ናቸው ።
ቡድኖቹ ዛሬ ያካሄዱት ጨዋታ የመጀመሪያ ሲሆን ፥ የመልስ ጨዋታቸውን ከሁለት ሳምንት በኋላ በማሊ ያካሂዳሉ።
በሌላ ዜና ለአፍሪካ ኮን ፌዴሬሽን ዋንጫ ሱዳን ካርቱም ላይ ከአልሃሊ ሸንዲ ጋር የማጣሪያ ጨዋታ ያደረገው ደደቢት 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።
ሁለቱ ቡድኖች ከሁለት ሳምንት በኋላ አዲስ አበባ ላይ የመልስ ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ።

ሰራዊት በመድፈር ሙከራ ተከሷል መባሉ፣ “በሬ ወለደ” ነው አለ

በማስታወቂያና በፊልም ስራ የሚታወቀው አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ፤ በመድፈር ሙከራ አቤቱታ እንደቀረበበት መወራቱን በተመለከተ ተጠይቆ፤ “በሬ ወለደ ወሬ ነው” ሲል አስተባብሏል፡፡ የሠራዊት መልቲ ሚዲያ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ሠራዊት ፍቅሬ ላይ አንዲት የዩኒቨርስቲ ተማሪ ለፖሊስ አቤቱታ ማቅረቧን የሚናገሩ ምንጮች፣ ባለፈው ቅዳሜ “ለማስታወቂያ ስራ እፈልግሻለሁ” ብሎ ፒያሳ አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ ለመሳምና ለማሻሸት ሲሞክር አመለጥኩ” የሚል ነው ብለዋል፡፡
ምንጮቹ እንደሚሉት፤ የአቤቱታው ሂደት ተቋርጦ፣ ጉዳዩን በሽምግልና እንዲያልቅ መደረጉን ይናገራሉ፡፡ ከፖሊስ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ሳይሳካ የቀረ ሲሆን፤ ሠራዊት በበኩሉ “ወሬው የበሬ ወለደ አሉባልታ ነው፤ ምንም የማውቀው ነገር የለም” ብሏል፡፡ “ካሁን በፊት ከወገቤ በላይ ብዙ ተብያለሁ፤ አሁን ደግሞ ከወገቤ በታች መጡ” በማለት ቀልድ አዘል አስተያየቱን ሠጥቷል - ሠራዊት፡፡

Friday, March 15, 2013

Ethiopia’s Dibaba pulls out of London Marathon


Ethiopia’s Olympic 10,000 metres champion Tirunesh Dibaba has withdrawn from next month’s London Marathon with a shin injury, organisers said on Thursday.

Dibaba had been set for her debut over the 42.195-km distance but an old lower leg problem has flared up during training for the race.

“I have been in training for the London Marathon, but the increase in mileage has caused a flare up of my previous lower leg injury,” she said in a statement.

“As a result, I won’t be able to compete in this year’s London Marathon but I look forward to making my marathon debut there next year.”

Dibaba had been aiming to become the first Ethiopian woman to win the London race since her cousin Derartu Tulu in 2001.

Ethiopia’s challenge in the women’s race will now be spearheaded by Olympic champion Tiki Gelana who is running the London Marathon for the first time.

“Of course, it is disappointing to lose Tirunesh. She has been such a fantastic athlete on the track, and everyone was full of anticipation to see how well she performed in a marathon,” race director Hugh Brasher said.

Dibaba is a three-time Olympic champion, having also won the 5,000 and 10,000 at the 2008 Beijing Games.

source:http://gulftoday.ae

Thursday, March 14, 2013

በየሃ 2 ሺህ 800 ዓመት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ ህንጻ በቁፋሮ ተገኘ

በቅድመ አክሱም ታሪክ የየሃ ስልጣኔን በ100 ዓመት ወደ ፊት የሚያስቀድምና 2 ሺህ 800 ዓመት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ ህንጻ በቁፋሮ ተገኘ።
በየሃ አካባቢ ግራት ቤል ገብሪ በተሰኘ ስፍራ ነው ህንጻው በጀርመናውያንና በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የተገኘው።
ግኝቱ በኢትዮጵያና በየመን መካከል ቀድሞ በነበረ ግንኙነት የሚነገሩ መላምቶችን የሚቀይርና የኢትዮጵያን ታሪክ የሚያድስ ይሆናል ነው የተባለው።
ግኝቱ ቀደም ሲል ቋንቋ ላይ የተካሄዱ ምርምሮችንም የሚደግፍ ይሆናል ነው ያሉት።
የሃና አካባቢው ለቱሪዝም መስህብ እንዲሆንና የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲጠበቀም ታስቦ የሚገነባው ሙዚየም የዲዛይን ስራው ተጠናቋል።
በቁፋሮው አብረው የተገኙት የሸክላና የድንጋይ መሳሪያዎችን ጨምሮ ሌሎችም ተንቀሳቃሽ ቅርሶች በዚሁ ሙዚየም የሚቀመጡ ይሆናል።
ጥንታዊውና ታሪካዊው የየሃ ቤተመቅደስ 12 ሜትር ቁመት ሲኖረው በማዕዘን በተጠረቡና 7 ሜትር ርዘመት ባላቸው ድርብ ድንጋዮች ነው ያለምንም ማያያዣ ጭቃና ሲሚንቶ የተገነባው።
ለዘመናት የተፈራረቀበት ፀሃይና ዝናብ በአካባቢው ህይወት ያለው ነገር ካለመኖሩ ጋር ተደማምሮ የጉዳት መጠኑ እየጨመረና አካባቢውም በአረም እየተዋጠ ይገኛል።
የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ አቶ ከበደ አማረ እንደሚሉት የጥገናው በፍጥነት መካሄድ ህንጻው ሙሉ በሙሉ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ያስቸለዋል።

Oromo Cultural Cloth

Some Oromo men wear woya (toga-like robes), and some women wear wandabiti (skirts). Others wear leather garments or animal skin robes, and some women wear qollo and sadetta (women's cloth made of cotton).
Modern garments from around the world are also worn. In cash-producing areas and cities, Oromos wear modern Western-style clothes. Oromos have clothes designated for special days. They call the clothes that they wear on holidays or other important days kitii and the clothes that they wear on working days lago.

Tuesday, March 12, 2013

የሆሊውድ የፊልም ባለሙያዎች በማንዴላ ላይ ለሚሰሩት ፊልም አዲስ አበባ ገቡ


 የደቡብ አፍሪካና የሆሊውድ የፊልም ባለሙያዎች በቀድሞው የደቡብ አፍሪካ መሪና የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ የስጦታ ሽጉጥ ዙሪያ የፊልም ቀረጻ ለማድረግ አዲስ አበባ ገብተዋል።
ማንዴላ በቀዳማዋ ሃይለስላሴ ዘመነ መንግስት በቀድሞው የኮልፌ ማሰልጠኛ ተቋም ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠናን ለ8 ሳምንታት ተከታትለዋል።
በወቅቱ ማንዴላ የኢትዮጵያ ቆይታቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው ደቡብ አፍሪካ ሲመለሱ ፥ ከቀዳማዊ ሃይለስላሴ በስጦታ መልክ የተበረከተላቸውን የስጦታ ሽጉጥ ይዘው ነበር።
ማንዴላ በአፓርታይድ ስርአት አራማጆች በሮቢን ደሴት በታሰሩበት ወቅት በስጦታ የተበረከተላቸውን ሽጉጥ ከመሬት በታች ቆፍረው ቀብረውት ነበር።
ይሁን እንጅ ማንዴላ ከ27 አመታት የእስር ቆይታ በኋላ ከእስር ቤት ሲወጡ በስጦታ ያገኙትን ያንን ታሪካዊ ሽጉጥ በአካባቢው በተካሄዱ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት ሊያገኙት አልቻሉም።
የሆሊውድ የፊልም ባለሙያዎችም ይህህነ ታሪክ በመንተራስ የፊልም ቀረጻ ለማድረግ በማሰብ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን ፊልሙ ለመላው አለም በቅርቡ ለዕይታ ይበቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በፊልሙ ስራ ውስጥ የተወሰኑ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች የሚሳተፉ ሲሆን ፥ የፊልሙን የኢትዮጵያ ቀረጻ ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅትም በአብዛኛው ተጠናቋል።
የፊልም ስራውን አጠቃላይ ሁኔታ በተመለከተም ዛሬ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቲያትር ቤት በዝግጅቱ አስተባባሪዎች መግለጫ ይሰጣል።

በወንድወሰን አንዱዓለም

Friday, March 8, 2013

በአዲስ አበባ ለ10 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እሁድ እጣ ያወጣል

በአዲስ አበባ ለ10 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የፊታችን እሁድ እጣ ይወጣል።
እጣ የሚወጣባቸው ቤቶች ጀሞና ሰሚትን ጨምሮ በተለያዩ ሳይቶች የተገነቡ ናቸው።
የፊታችን እሁድ በመዘጋጃ ቤት የሚኖረውን የእጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት አስመልክቶ የከተማዋ ቤቶች ልማትና ኮንስትራክሸን ቢሮ ዛሬ ማምሻውን መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
ባለፈው አመት ተጀምረው እየተጠናቀቁ ካሉት ቤቶችም ከወር በኋላ በዕጣ የሚታደሉ እንዳሉ ከቢሮው የተገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አስተዳደሩ በተለያዩ ዙሮች የጀመራቸው 95 ሺህ ቤቶች በግንባታ ላይ ይገኛሉ።
እየተገነቡ ካሉትና ወደፊትም ከሚገነቡት ቤቶች ለህዝብ ግልጋሎት እየሰጡ ያሉ ፥ የመንግስት ሰራተኞች ውስን ድርሻ በቅድሚያ የሚያገኙበት አሰራር እንደሚዘረጋ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ መናገራቸው አይዘነጋም።

አበበ ቢቂላ እና ጋቢው

አበበ በሮም ኦሎምፒክ በማሸነፉና የኢትዮጵያ ስም በማስጠራቱ ትልቅ ኩራት ሆነ ለቶኪዮ ኦሎምፒክ ዝግጅት ተጀምረ፡፡ አበበ በተለያየ ጊዜ ሩጫ ሲያካሄድ እያቋረጠ ይወጣ ጀመር፡፡ ችግር ሲገጥመው ለይድነቃቸው ያማክራል፣ የቡድኑ ሐኪም ዶክተር ፍሬደሪክና ይድነቃቸው በአበበ ጉዳይ ተወያዩና አስመረመሩት ትርፍ አንጀት አለበት፣ እንዲህ ሆኖ መሮጥ አይችልም አሉ፣ ኦፕራሲዮን መሆን አለበት፣ ሁለቱም ወሰኑ ለአበበም ነገሩት፣ ‹‹ እናንተ እንዳላችሁ›› አለ፡፡ ሆስፒታል አስተኙት ኦፕራሲዮን ተደረገ፡፤ጉዳዩ ሌላ ቦታ ተሰማ ጭቅጭቅ ተፈጠረ፡፡ ‹ይድነቃቸውና ፍሬደሪክ አበበን አስቀደዱት›› ተባለ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ኢትዮጵያ ወርቅ እንዳታመጣ በማሰብ ነው ተብሎ ተወገዙ፣ አበበ ግን ‹‹ከማንም በላይ እነሱ ለእኔና ለውጤቱ አስበው ነው›› አለ፡፡
 አበበ ገና ኦፖራሲዮኑ ሙሉ በሙሉ ሳይደርቅ ወደ ቶኪዮ ሄደ አበበ በሽተኛ ነውና ጋቢ ለብሶ መሄድ ነበረበት የጃፓን ሐኪሞቸም ህመሙንና ስፌቱን አዩ እንዲህ ሆነህ መንቀሳቀስ አትችለም አሉት፣ አበበ ግን ልዩ ፍጡር ነበር ሮም በባዶ እግሩ ሮጧላ፡፡ ቶኪዮ ላይ ደግሞ ከበሽታው ሙሉ ለሙሉ ሳያገግም ማራቶንን ሮጠ የጃፓን ጋዜጦች አበበ በሽተኛ መሆኑን ነው የሚያውቁት በመሮጡ ተገረሙ፣ በማሸነፉም ተደነቁ እውነትም ልዩ ፍጡር ነው አሉ፡፡ ለብሶት የሄደው ጋቢ አሁንም ድረስ እዚያው ጃፓን ይገኛል፣ ሰዎች ጋቢውን ይጎበኙታል ገንዘብ ከፍለው ይለብሱና ፎቶ ይነሳሉ አበበ ሮጦ እንዳሸነፈ ወደ ይድነቃቸው ሄደና ‹‹ ወሬኞችን ጭጭ አደረግናቸው›› አለ፡፡ ሮም ላይ ሲያሸንፍ ደግሞ ወደ ይድነቃቸው ጠጋ ብሎ ‹‹ አንጀቶን አላራስኩትም ?›› አላቸው ያን ጊዜ ምንም ለማያመጡ ለምን ሄዱ ተብሎ ከቤተ መንግሥት ወቀሳ ነበር፣ አበበም የመጀመሪያውን ወርቅ በማምጣቱ ይድነቃቸው ተደሰቱ አበበ የሮጠው መስከረም 1 ቀን ነው ይድነቃቸው የተወለዱት ደግሞ መስከረም 1 ቀን ነው፡፡ ይድነቃቸው ሻምፓኝ ይዘው መጡ፡፡ ‹‹ ለኔም ለአንተም›› አሉት መስከረም 1 ለሁለቱም ልዩ ቀን ነበር፡፡
 
Source:librogk.com

Monday, March 4, 2013

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንቱን መረጠ

አቶ ብርሃነ ኪዳነ ማርያም በድጋሚ ለሚቀጥሉት አራት አመታት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴን እንዲመሩ በድጋሚ በፕሬዝዳንትነት ተመረጡ።
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ በቢሾፍቱ ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ ፥ አቶ ብርሃነን በሙሉ ድምጽ መርጧል።
አቶ ብርሃነ ባለፉት 4 አመታት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፥ ብቁ የሰው ሃይልና የጠነከረ አደረጃጀት እንዲሁም ጠንካራ ገንዘብ አቅም እንዲኖረው ማስቻላቸው ይነገራል።
ኮሚቴው የራሱ ዘመናዊ ቀልጣፋ አደረጃጀት እንዲኖረው አዲስ አበባ ኡራኤል አካባቢ ዘመናዊ ህንጻ ገዝቷል።
በየዘርፉም አስፈላጊ ሙያተኞችን በማሰባሰብ አቅሙን ለመገንባት መሰረት እንደጣሉ የሚነገርላቸው አቶ ብርሃነ የፖለቲካል ሳይንስ እና የህግ ምሁር ናቸው።
ሃገራቸውንም በተለያዩ ከፍተኛ ቦታዎች አገልግለዋል።
ለቅርጫት ኳስ ከፍተኛ ፍቅር ያላቸው ሲሆን የተጠቆሙትም ከቅርጫት ካስ ፌዴሬሽን ነው።
ጠቅላላ ጉባኤው በውሎው ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን ተመልክቷል ፤ ከእነዚህ መሃል የ2012 እቅድ አፈጻጸም ፥ የኦዲት ሪፖርት መርምሮ በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን አዳዲስ አራት ስራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላትንም መርጧል።
ለአባላቱም የስነ ምግባር ደንብ መመሪያ አጽድቋል።
ኮሚቴው በመጨረሻም የቢሾፍቱ ኦሎምፒክ መንደርን መርቋል።

Israel’s Health Ministry Investigating Illegal Contraceptives to Ethiopian Women


Israel’s health ministry is investigating claims that Ethiopian women are being injected with a controversial contraceptive without their knowledge or consent.
Thousands of Ethiopian women are said to be receiving shots of Depo-Provera every three months in Israeli clinics. The contraceptive stops menstruation and has been linked to fertility problems and osteoporosis.
Yaakov Litzman, Israel’s deputy minister of health, who has previously denied the practice, will lead the inquiry, a spokesperson announced.
The phenomenon was uncovered when social workers noticed the birth rate among Ethiopian immigrants halving in a decade. An Israeli documentary investigating the scandal was aired in December and prompted a popular outcry.

Sunday, March 3, 2013

ለታዋቂው አሠልጣኝ ዶክተር ወልደ መስቀል ኮስትሬ ህክምና የሚያስፈልገው 60 ሺህ ዶላር ሊሞላ 295 ሺህ ብር ብቻ ቀረው!

 
ለታዋቂው አሠልጣኝ ዶክተር ወልደ መስቀል ኮስትሬ ህክምና የሚያስፈልገው 60 ሺህ ዶላር ሊሞላ 295 ሺህ ብር ብቻ ቀረው!

የረዥም ርቀት ዋና አሠልጣኝ ሆነው በርካታ ታዋቂና ታላላቅ አትሌቶች በማፍራት የሚታወቁት ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ እግራቸው ላይ የተገጠመው ብረት ምርዘት (ኢንፌክሽን) ፈጥሮባቸው የአልጋ ቁራኛ ከሆኑ ሰነባብቷል፡፡

ለአልጋ ቁራኛ የዳረጋቸው ይኼው የዶክተር ወልደ መስቀል ሕመም፣ በአገር ውስጥ ሕክምና መዳን እንደማይችልና ወደ ውጭ አገር ሔደው ሕክምና እንዲያደርጉ የቅዱስ ያሬድ ሆስፒታል የሕክምና ቦርድ መወሰኑን በተለያዩ ጊዜ በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ መገለጹ ይታወሳል፡፡

የሕክምናውን ወጪ በተመለከተ ልጃቸው አቶ ያዕቆብ ወልደ መስቀል እንደገለጸው ከሆነ፣ የሚያስፈልገው 60 ሺሕ ዶላር ነው፡፡ ይህንኑ ለማሟላትም አትሌቶችን ጨምሮ የተለያዩ መንግሥታዋና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ የዶክተር ወልደ መስቀልን ሕይወት መታደግ ይችሉ ዘንድ ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተቋቁሞ እንቅስቃሴ መጀመሩንና ምላሽም እየተገኘ መሆኑን አስረድቷል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ አለባቸው ንጉሤ ፌዴሬሽኑ ለዶክተር ወልደ መስቀል ኮስትሬ ሁትለ መቶ ሺሕ ብር (200,000) የሰጠ ሲሆን ኢትዮጲካሊንክ የተባለው የሬዲዮ ፕሮግራም ትናንት ምሽት ላይ ባደረገው የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ መሰናዶ አንድ መቶ አምስት ሺህ ብር (105,000) ማሰባሰብ ችሏል። አሁን የቀረው ሁለት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ (295,000) ብር ብቻ ነው። ይህን ታላቅ አሰልጣኝ ለማዳን ሁሉም ወገን ላደረገው ርብርብ ከፍተኛ ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል። ቀሪው ገንዘብም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሟልቶ ዶክተሩ ወደ ህክምናቸው የሚሄዱበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን ተስፋ አለን።

snake prank: Very Funny


ሀና ግርማ እና አዲስ የሙዚቃ ስራዎቿ

ሀና ግርማን ብዙዎች በኢትዮጵያ አይይል ውድድር ላይ ተመልክታችኋታል። በተለይ በልዩ የኦፔራ መዚቃ ተሰጥዎዋ ተደናቂነት ያተረፈችው አዳጊ ወጣት ሰሞኑን ሁለት ነጠላ ዘፈኖች አውጥታለች።
ሃና ሙዚቃውን እንዴት ተጫወተችው? የዚህን ሙዚቃ ዜማና ሙዚቃ ያቀናበረው እንዲሁም ሃናን የሚያሰለጥናት ቴድሮስ መኮንን( ቴዲ ማክ) መልስ ሰጥቶናል። እንዲሁም ሃና የኦፔራ ዘፈን እንድትዘፍን ያበረታታኝ ወንድሜ ነው ትላለች። ወንድሟ ታደሰ ግርማ ይባላል። በሙዚቃም ብቻ ሳይሆን በትምህርቷም እንድትበረታታ ይረዳታል።
ልጆች በልጅነት እድሜያቸው ታዋቂ ሲሆኑ አብዛኛውን ጊዜ የልጅነት ጊዜያቸውን በቅጡ አጣጥመው እንዳያድጉ የሚያደርገው የራሱ ሚና አለውና ከዚህስ አንፃር በቤተሰብ በኩል ምን አይነት ድጋፍ ሃና ታገኛለች? ሃና ብዙ አድናቂዎች አፍርታለች። ለነሱም መልዕክት አስተላልፋለች።
ስለሙዚቃ ስራዎቿ እና በህይወቷ ላይ ስለገጠማት ለውጥ ዛሬ በወጣቶች መድረክ የምንዳስሰው ይሆናል።

ልደት አበበ
አርያም ተክሌ