Search

Friday, March 8, 2013

በአዲስ አበባ ለ10 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እሁድ እጣ ያወጣል

በአዲስ አበባ ለ10 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የፊታችን እሁድ እጣ ይወጣል።
እጣ የሚወጣባቸው ቤቶች ጀሞና ሰሚትን ጨምሮ በተለያዩ ሳይቶች የተገነቡ ናቸው።
የፊታችን እሁድ በመዘጋጃ ቤት የሚኖረውን የእጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት አስመልክቶ የከተማዋ ቤቶች ልማትና ኮንስትራክሸን ቢሮ ዛሬ ማምሻውን መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
ባለፈው አመት ተጀምረው እየተጠናቀቁ ካሉት ቤቶችም ከወር በኋላ በዕጣ የሚታደሉ እንዳሉ ከቢሮው የተገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አስተዳደሩ በተለያዩ ዙሮች የጀመራቸው 95 ሺህ ቤቶች በግንባታ ላይ ይገኛሉ።
እየተገነቡ ካሉትና ወደፊትም ከሚገነቡት ቤቶች ለህዝብ ግልጋሎት እየሰጡ ያሉ ፥ የመንግስት ሰራተኞች ውስን ድርሻ በቅድሚያ የሚያገኙበት አሰራር እንደሚዘረጋ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ መናገራቸው አይዘነጋም።

No comments:

Post a Comment