Search

Thursday, March 28, 2013

ሁለት እጅ አልባዋ አብራሪ ጄሲካ ሰኞ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ልምዷን ታካፍላለች


ሁለት እጅ አልባዋ አሜሪካዊትአውሮፕላን አብራሪ ጄሲካ ኮክስ ቻምቤሌይን የፊታችን ሰኞ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ንግግር ታደርጋለች።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ እንደገለጸው ፥ በተፈጥሮ ሁለት እጆቿን ያጣችው የ32 ዓመት ወጣት በዩኒቨርሲቲው ለ300 ተማሪዎች መጋቢት 23 ቀን 2005 ንግግር ታደርግላቸዋለች።
በቀስቃሽ ንግግሮቿ የምትታወቀው ጄሲካ  ወደ ኢትዮጵያ የምትመጣው ሃንዲካፕ ዓለም አቀፍ በተባለው ግብረ ሰናይ ድርጅትና በአሜሪካ ዓለም የልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤይድ) ትብብር ነው።
ጄሲካ በመላው ዓለም እንድትታወቅ ያደረጋት ፥ እጆች ሳይኖሯት አውሮፕላን ለማብረር በመቻሏና ለዚህም የአብራሪነት ፈቃድ ማግኘቷ ነው።
በአሪዞና ግዛት ተስከን የተወለደችው ጄሲካ ከጽንስ ጀምሮ እጆቿ የእግርንም ባህርይ ይዘው በመወለዷ  ፥ ለምታከናውናቸው ተግባራት ችግር እንደማይፈጥርባት መረጃዎች ያመለክታሉ ፤ በዚህም የምትፈልገውን ሁሉ በእግሮቿ ለማድረግ እምብዛም አትቸገርም።
ሃንዲካፕ ዓለም አቀፍ ፥ አካል ጉዳተኛ ሕጻናት ከትምህርት እንዳይገለሉ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም መግለጫው አመልክቷል።

No comments:

Post a Comment