Search

Saturday, March 30, 2013

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸውን በሄሊኮፕተር ያካሄዱት ጥንዶች

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸውን በሄሊኮፕተር ያካሄዱት ጥንዶች

ሙሽሮቹ "የጋብቻ ሥነ ሥርዓታችንን በሄሊኮፕተር ያካሄድነው ሞልቶን ተርፎን ሳይሆን የኢትዮጵያን የዕድገትና የለውጥ ሂደት ለኢትዮጵያውያንና ለመላው ዓለም ለማሳወቅ ነው" ብለዋል፡፡

"ኢትዮጵያ በዓለም ላይ የምትታወቀው በረሃብና በድርቅ ነው" የሚሉት ሙሽሮቹ " በአሁኑ ወቅት ግን ኢትዮጵያ ዓለምን በሚያስደምም ሁኔታ እያደገች መሆኗንና የተለየ ገጽታ እንዳላት ለማሳወቅ በተለየ ሁኔታ የጋብቻ ሥነ ሥርዓታችንን በሄሊኮፕተር ለማድረግ ችለናል፡፡" ነው የሚሉት ሙሽሮቹ ።

የጋብቻ ሥነ ሥነ ሥርዓታቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ በሄሊኮፕተር ያካሄዱት አቶ ሙሉቀን ፋንታዬ ወይም በቅጽል ስሙ / ሉክ/ እና ወይዘሪት ወይንሸት ሙሉነህ ውይም በቅጽል ስሟ /ወይኒ/ ናቸው፡፡

ሉክ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ ሙያዎች ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ወይኒ ደግሞ የአፄ ቴዎድሮስ አራተኛ የልጅ ልጅ ነች፡፡


በሊሞዚን መኪኖች በትልቅ ሆቴል ከሚካሄድ ቅልጥ ያለ የሠርግ ሥነ ሥርዓት ያነሰ ወጪ እንዳወጡ የሚናገሩት ሙሽሮቹ ፥ በጋብቻ ሥነ ሥርዓታቸው ላይ እንዲታደም የጠሩት ሰው ቁጥር 150 ያህል ብቻ ነው፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ

No comments:

Post a Comment