Search

Monday, March 18, 2013

አማርኛ በቻይና ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሊሰጥ ነው

በቤጂንግ  የውጭ  ትምህርቶች ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ  ቋንቋን ማስተማር የሚያስችለውን ስምምነት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር ገብቷል ።
ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች ስምምነቱን ባለፈው ሳምንት  ተፈራርመዋል ።
በስምምነታቸው መሰረትም አማርኛ  ቋንቋ ከሚቀጥለው መስከረም ወር  ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው  መሰጠት ይጀመራል ።
የአዲስ  አበባ  ዩኒቨርሲቲም የቻይና  ቋንቋ  ስልጠና  ፕሮግራሙን  ወደ መጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ይሆናል ።
የትምህርት መርሃ ግብሩን ለመጀመርም ዛሬ  አዲስ አበባ  ላይ  የስምምነት ፊርማ ይፈፀማል ።

No comments:

Post a Comment