Search

Wednesday, March 20, 2013

ሲሳይ ባንጫ በእሁዱ ጨዋታ አይሰለፍም

በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ጋር በነበራት 3ኛ የምድብ ጨዋታ ላይ የቀይ ካርድ የተመለከተው ሲሳይ ባንጫ ፥ በካፍ በመቀጣቱ ቡድኑ እሁድ ከቦትስዋና ጋር በሚኖረው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ አይሰለፍም።

በሌላ በኩል ቦትስዋና ማላዊን በሜዳዋ አስተናግዳ 1 ለ 0 በሆነ ውጤትያሸነፈች ሲሆን ፥ ቡድኑ ከኢትዮጵያ አቻው ጋር ላለበት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ነገ አዲስ አበባ ይገባል።
ኢትዮጵያዊው አጥቂ ሳላዲን ሰኢድም ከብሄራዊ  ቡድኑ በቀረበለት ጥሪ መሰረት  ዛሬ ቡድኑን የሚቀላቀል ይሆናል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከትናንት ወዲያ ጀምሮ ልምምድ መጀመሩ የሚታወስ ነው።

No comments:

Post a Comment