Search

Wednesday, August 19, 2015

በማልቀስ የምናገኛቸው አስገራሚ የጤና በረከቶች

በማልቀስ የምናገኛቸው አስገራሚ የጤና በረከቶች

መቼስ በከፋንና ባዘንን ወቅት፣ የፍቅር ግንኙነታችን ሲቋረጥ፣ አሳዛኝ ፊሌሞች ስንመለከት፣ ከመጠን በላይ ስንደሰትና በሌሎችም ምክንያቶች  ስሜታችንን ፈንቅሎ የሚወጣው እንባችን አስገራሚ የጤና ጠቀሜታዎችስ እንደሚያስገኝልን ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን?
በአማካኝ በቀን 280 ግራም በዓመትም 30 ጋሎን እንባ ከአይናችን እንደሚፈስ ጥናቶች ያመለክታሉ።
በካሊፎርኒያ ሳኔ ጆሴ የስነልቦና ባለሙያ ሳይኮቴራፒስት የሆኑት ሻሮን ማርቲን እንደሚሉት ማልቀስ (ማንባት) እጅግ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት፤ ማልቀስ ጭንቀትን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንስ ማድረጉ ደግሞ ከሁሉ ጎልቶ የሚታይ ጠቀሜታው ነው ብለዋል።
ማልቀስ ከሚያስገኛቸው የጤና ጠቀሜታዎች ዋና ዋናዎቹን ስንቃኝ፦
1. ከሰውነታችን አላስፈላጊ ኬሚካሎችን ያስወግዳል፣
እንባ የአዕምሮ መታደስን ብቻ ሳይሆን የሚያመጣው ከሰውነታችን  ጎጂ  ኬሚካሎች በእንባ አማካኝነት እንዲወገዱ ባማድረግ ጭንቀትንም ሆነ መብሰልሰልን ያስወግድልናል።
ዶክተር ዊሊያም የተሰኙ የዘርፉ ተመራማሪ እንደሚናገሩት እንደ ላብ እና ሽንት ሁሉ እንባም አላስፈላጊና ጎጂ (toxic) ነገሮችን ከሰውነት ለማስወገድ ጠቃሚ ነው።
2.ባክቴሪያን ይገላል፣
እንባ በእናት ጡት ውስጥ የምናገኘውንና ሊሶዚም የተሰኘውን ባክቴሪያን በተፈጥሮ የመግደል አቅም ያለውን ንጥረ ነገር ይዟል።
ሊሶዚም እስከ 95 በመቶ ባክቴሪያን ከአምስት እስከ 10 ደቂቃ ባለ ጊዜ ውስጥ የመግደል ሀይል አለው።
እ.ኤ.አ በ2011 የተደረገ ጥናት እንዳመለከተው ሊሶዚም የአብዛኛዎቹን ባክቴሪያዎች  የላይኛው ግድግዳ ክፍል (cell walls) ከጥቅም ውጪ በማድረግ ባክቴሪያው እንዲሞትና እንዳይራባ ያደርጋል።
3. የእይታ ችሎታን ያሻሽላል፣
እንባ የእይን ኳስንና የአይን ቆብን በማለስለስ የእይታ ችሎታችን እንድሻሻል የሚያደርግ ሲሆን፥ አቧራን የመሳሰሉ ቆሻሻዎችን በማስወገድ ጭምር የተሻለ እይታ እንዲኖረን ያግዛል።
እንባ በተጨማሪም የአይን እንቅስቃሴ እንዲቀላጠፍ ይረዳል።
4. ጭንቀትን ያስወግዳል፣
ማልቀስ ከነበርንበት ስሜት በመውጣት እረፍት እንዲሰማንና ሸክሙ ቶሎ እንዲቀልልን በማድረግ ጭንቀትን እንድናስወግድ ያግዘናል።
የጭንቀት መንስኤ የሆኑ ሆርሞኖች ከሰውነታችን  የሚወገድበት መንገድ እንደመሆኑም  ያስጨነቀን ነገርን ለመርሳት እንደመሳሪያ ሆኖ ያገለግለናል።
ይህም ጭንቀትን ተከትለው የሚመጡትን እንደ ራስምታት፣ ከፍተኛ የደም ግፊት የመሳሰሉት እንዳይከሰቱብን ያደርጋል ማለት ነው።
5.ጥሩ ባህሪ (ሙድ) እንዲኖረን ፣
ማልቀስ ከየትኛውም ሰውሰራሽ ነገር በተሻለ ባህሪን (ሙድን) በማስተካከል ረገድ አቻ የለውም።
ባህሪያችንን በማስተካከል ረገድ ተመራጭ መሆኑን ነው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2008 በአሜሪካ ደቡብ ፍሎሪዳ የተደረገ ጥናት ያመለከተው።
እንባ ጭንቀትን ማስወገድ ብቻ ሳይሆን ተመልሰን በዚያው ሴሜት ውስጥ እንዳንገባ በማድረግ ረገድም ሚናው ላቅ ያለ ነው።

 from : FBC       

Friday, July 31, 2015

“ዘፈኑን እየተውኩ ወደ ዝማሬው ዓለም እየገባሁ ነው” – ድምፃዊት(ዘማሪት) ዘሪቱ ጌታሁን [ቃለ-ምልልስ]

ዘሪቱ ከበደ ዘፈን አቁማለች ወይንስ አላቆመችም የሚሉ አናጋጋሪ ጉዳዮች በርካታ ጊዜያት ሲነሱ ቆይተዋል፡፡ ይሄንን ጉዳይ በተመለከተ ከእርሷ አንደበት ይህ ነው የሚባል ቁርጥ ያለ ምላሽ ሳይሰጥበት በመቆየቱ በበርካቶች ዘንድ አከራካሪ ጉዳይ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ዘሪቱ በየወሩ በአማርኛ ቋንቋ ታትሞ ለገበያ በሚበቃው ሪቪል (REVEAL)መፅሄት ባደረገችው ቃለ ምልልስ ከዘፈኑ አለም በመውጣት መንፈሳዊ ጉዞ ላይ መሆኗን አስታውቃለች፡፡ መፅሄቱ ከቀረበላት ጥያቄዎች መካከል ዋና ዋናዎች አለፍ አለፍ ብይ በመቃኘት ላስነብባችሁ፡፡


☞ሪቪል፡ ከመንፈሳዊነት ጋር ተያይዞ መዝፈን አቁመሻል?
☞ዘሪቱ፡ መንፈሳዊነት ሁለገብና የሁለንተናችን ለውጥ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ደግሞ ከአለማዊነት ስንወጣ የማይነካ የህይወታችን ክፍል የለም፡፡ ሁሉም ነገር እኔ እንደምለውና ዓለም እንደምትሰብከው ሳይሆን እግዚአብሄር እንደሚለው የማድረግና የመሆን ሂደት ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ታዲያ እንደ ሁሉ ነገሬ የጥበብ ስራየም ሳይፈተሸ አያልፍም፡፡ ስለዚህ ሙዚቃም ይሁን ፊልም፤ ብቻ ምንም ነገር ልስራ የማደርገው ነገር እግዚአብሄር የሚፈልገውን መለዕክት ያደርሳል ወይ? ሰዎችን ይጠቅማል ወይ? ደሞስ እንደሱ ፍቃድና ልክ ሰዎችን ያሳዝናል? ያስደስታል ወይ ብዪ በመጠየቅና ይልቁንም ከሱ ከራሱ መለዕክትን በመቀበል ወደ መስራት መንፈሳዊነት እያደኩ ነው፡፡ መዝፈን ይሁን መዘመር አላውቅም፡፡ የማውቀው እግዚአብሄር እንደሚከብርበት ነው፡፡

☞ሪቪል፡ ብዙዎች ግን “ዘሪቱ ወይ ትዘምር ወይ ትዝፈን መቁረጥ አቅጧት እየወላወለች ነው” ይላሉ፡፡ በእርግጥ እየወላወልሽ ነው?

☞ዘሪቱ፡ እየሱስ ክርስቶስን ተከትያለሁ ብዪ በማምንባቸው ዓመታት ውስጥ በአካሄዴ ሁሉ እግዚአብሄርን ደስ አሰኝቻለሁ ብዪ አላስብም፡፡ ምንአልባትም በአንዳንድ የህይወቶቼ ክፍሎች እግዚአብሄርን አይፈሩም ተብለው ከሚታሰቡት ሰዎች እንኳን ብሼ አውቃለሁ፡፡ እንደእግዚአብሄር ምህረትና እንደ አባትነቱ ፍቅር ባይሆን ኖር ዛሬ ያለሁበት ቦታ አልገኝም ነበር፡፡ሰ አድርጌ የማላውቅ ግን መወላወል ነው፡፡ ፈርቼ አውቃለሁ፤ ግራ ገብቶኝም ያውቃል፤ ፈርሶ ሲሰራ እንደሰነበተ ሰው ደግሞ በሁሉም ነገር እርግጠኛ ሆኜ ሀሳቤን ሳለውጥ መጥቻለሁም ብዪ ለመናገርም አልደፍርም፡፡ ወላውዪ ግን አላውቅም፡፡

ዘሪቱ ሙዚቃ አቁማለች ብሎ ሚዲያ ጭምር ሲዘግብ ፤ እኔን ጠይቆና አነጋገግሮ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ከሆነች መቆሟ አይቀርም ብለው በራሳቸው በመደምደም ነው፡፡ እኔ ህይወቴን ስቀጥልና ከተነገሩት ዜናዎች በተቃራኒ የሙዚቃስራዎች ወደ አድማጭ ሲደርሱ የወላወልኩ የሚያስመስል መልክ ሊያሰጠኝ ችሏል፡፡
☞ሪቪል፡ ግን ዝናና ገንዘብን መስዋትነት ማድረግ የሚከብድ አይደለም?

☞ዘሪቱ፡ እኔ ለመተው የሚከብድ የገንዘብ ክምችት የለኝም፡፡ዝናንም በተመለከተ ዘማሪዎች ከዘፋኞች ባልተናነሰ ዝነኞች የሆኑበት ዘመን እንደሆነ ነው የማስበው፡፡ ከዝና ወደ ዝና ብሸጋገር አሁን ከምከፍለው ዋጋ የበለጠ እንደምከፍል አውቃለሁ፡፡

☞ሪቪል፡ ቤት መኪናና ሌሎች አያስፈልጉም ብለሽ ነው የምታምኚው?
☞ዘሪቱ፤ እኔ የማምነው ከሆነ ቦታ ተነስተህ የሆነ ቦታ ለመድረስ ትራንሰፖርት እንደሚያስፈልግ ነው፡፡ መኪናው ያንተ ከሆ ጥሩ፤ ካልሆነም መኖርህን ለማታውቅበት ለዛሬ ባለቤትነትህ ያለው ፋይዳ ውስን ነው፡፡ የቤትም አስፈላጊነት መጠለያነቱ፤ትርጉሙም አብረውህ በሚኖሩት ሰዎች እንጂ በባለቤተረነት ካርታው አይደለም፡፡ የባለቤተረነት ዋስትና ለእኔ ትርጉም የለሽ ነው፡፡እግዚአብሄር ወዶ ለሚጨምርልኝ ለእያንዳንዱ ቀን የሚያስፈልገኝን ሁሉ እንደሚያዘጋጅልኝ አምናለሁ፡፡
☞ሪቪል፤ እንደዚህ ያለ ህወት ግን ላገባችና በተለይም ልጆች እናት ለሆነች ሴት አይከብድም?

☞ዘሪቱ፤ እንደዚህ ያለ ህይወት ለማንም ቀላል አይደለም፡፡ በተለይም እንዳልከው፤ቤተሰብ ላለን ሰዎች ደግሞ የማይታሰብ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በስጋዊ አቅማችን ስንሞክረው ነው፡፡ ሰው የመሆንን ትርጉም ለመረዳት በፈቀድን መጠን ግን ራሱ እግዚአብሄር በእና ውስጥ ይችለዋል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን መከተል ማለት፤ ሰው በሀጢያት ከመውደቁ በፊት ወደ ነበረው ማንነት የመመለስ ጉዞ ማለት ነው፡፡ ያ ማንነት ደግሞ ከእግዚአብሄር የመሆንና ማንነቱን የማንፀባረቅ ህይወት ነው፡፡ በመሬታዊ ገደብ እሱን ማንፀባረቅ አይቻልም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አሰልጣኝነት ከመሬታዊ ገደብ ወደ እሱ ማንነት የሚያሻግረን መመሪያ ሁሉ ደሞ በቅዱስ ቃሉ ወስጥ አለ፡፡ ኢየሱስ ለምን አይነት ክብር እንደጠራን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ከንግዳችን፣ ከቤተሰባችንና ከራሳችን ጭምር በላይ እሱን እንድናስቀድም ነው፡፡ ይህ ሲሆን ብቻ ደቀመዛሙርቶቹ ልንሆን እንምንችል በግልፅ አስቀምጦልናል፡፡ ስለዚህ እሱን በመከተል ውስጥ ምንም አይነት አቋራጭ አልፈልግም፡፡
☞ሪቪል፤ ባለቤትሽ በዚህ ደስተኛ ነው?

☞ዘሪቱ፤ በጣም ደስተኛ ነው እንጂ፡፡ የምተገዛ ሚስት አድረጎለታል፡፡ ከዚህ ህይወት ጋር በተዋወኩባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በእኔ ላይ ባስከተለው የማንነት መናጋት ተከትለው በመጡ ጥፋቶች ብዙ ዋጋ ከፍሏል፡፡ ሚስትህ ፈርሳ እስክተሰራ መታገስ ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ከመጀመሪያዋ የተሻለች ሚስት እንዳለችው እሱ ምስክር ነው፡፡
ጌታ ይባርክሽ ዘሪቱ!!
@የእውነት ቃል
source: zehabesha.com
☞ሪቪል፡ ከመንፈሳዊነት ጋር ተያይዞ መዝፈን አቁመሻል?
☞ዘሪቱ፡ መንፈሳዊነት ሁለገብና የሁለንተናችን ለውጥ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ደግሞ ከአለማዊነት ስንወጣ የማይነካ የህይወታችን ክፍል የለም፡፡ ሁሉም ነገር እኔ እንደምለውና ዓለም እንደምትሰብከው ሳይሆን እግዚአብሄር እንደሚለው የማድረግና የመሆን ሂደት ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ታዲያ እንደ ሁሉ ነገሬ የጥበብ ስራየም ሳይፈተሸ አያልፍም፡፡ ስለዚህ ሙዚቃም ይሁን ፊልም፤ ብቻ ምንም ነገር ልስራ የማደርገው ነገር እግዚአብሄር የሚፈልገውን መለዕክት ያደርሳል ወይ? ሰዎችን ይጠቅማል ወይ? ደሞስ እንደሱ ፍቃድና ልክ ሰዎችን ያሳዝናል? ያስደስታል ወይ ብዪ በመጠየቅና ይልቁንም ከሱ ከራሱ መለዕክትን በመቀበል ወደ መስራት መንፈሳዊነት እያደኩ ነው፡፡ መዝፈን ይሁን መዘመር አላውቅም፡፡ የማውቀው እግዚአብሄር እንደሚከብርበት ነው፡፡
☞ሪቪል፡ ብዙዎች ግን “ዘሪቱ ወይ ትዘምር ወይ ትዝፈን መቁረጥ አቅጧት እየወላወለች ነው” ይላሉ፡፡ በእርግጥ እየወላወልሽ ነው?
☞ዘሪቱ፡ እየሱስ ክርስቶስን ተከትያለሁ ብዪ በማምንባቸው ዓመታት ውስጥ በአካሄዴ ሁሉ እግዚአብሄርን ደስ አሰኝቻለሁ ብዪ አላስብም፡፡ ምንአልባትም በአንዳንድ የህይወቶቼ ክፍሎች እግዚአብሄርን አይፈሩም ተብለው ከሚታሰቡት ሰዎች እንኳን ብሼ አውቃለሁ፡፡ እንደእግዚአብሄር ምህረትና እንደ አባትነቱ ፍቅር ባይሆን ኖር ዛሬ ያለሁበት ቦታ አልገኝም ነበር፡፡ሰ አድርጌ የማላውቅ ግን መወላወል ነው፡፡ ፈርቼ አውቃለሁ፤ ግራ ገብቶኝም ያውቃል፤ ፈርሶ ሲሰራ እንደሰነበተ ሰው ደግሞ በሁሉም ነገር እርግጠኛ ሆኜ ሀሳቤን ሳለውጥ መጥቻለሁም ብዪ ለመናገርም አልደፍርም፡፡ ወላውዪ ግን አላውቅም፡፡
ዘሪቱ ሙዚቃ አቁማለች ብሎ ሚዲያ ጭምር ሲዘግብ ፤ እኔን ጠይቆና አነጋገግሮ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ከሆነች መቆሟ አይቀርም ብለው በራሳቸው በመደምደም ነው፡፡ እኔ ህይወቴን ስቀጥልና ከተነገሩት ዜናዎች በተቃራኒ የሙዚቃስራዎች ወደ አድማጭ ሲደርሱ የወላወልኩ የሚያስመስል መልክ ሊያሰጠኝ ችሏል፡፡
☞ሪቪል፡ ግን ዝናና ገንዘብን መስዋትነት ማድረግ የሚከብድ አይደለም?
☞ዘሪቱ፡ እኔ ለመተው የሚከብድ የገንዘብ ክምችት የለኝም፡፡ዝናንም በተመለከተ ዘማሪዎች ከዘፋኞች ባልተናነሰ ዝነኞች የሆኑበት ዘመን እንደሆነ ነው የማስበው፡፡ ከዝና ወደ ዝና ብሸጋገር አሁን ከምከፍለው ዋጋ የበለጠ እንደምከፍል አውቃለሁ፡፡
☞ሪቪል፡ ቤት መኪናና ሌሎች አያስፈልጉም ብለሽ ነው የምታምኚው?
☞ዘሪቱ፤ እኔ የማምነው ከሆነ ቦታ ተነስተህ የሆነ ቦታ ለመድረስ ትራንሰፖርት እንደሚያስፈልግ ነው፡፡ መኪናው ያንተ ከሆ ጥሩ፤ ካልሆነም መኖርህን ለማታውቅበት ለዛሬ ባለቤትነትህ ያለው ፋይዳ ውስን ነው፡፡ የቤትም አስፈላጊነት መጠለያነቱ፤ትርጉሙም አብረውህ በሚኖሩት ሰዎች እንጂ በባለቤተረነት ካርታው አይደለም፡፡ የባለቤተረነት ዋስትና ለእኔ ትርጉም የለሽ ነው፡፡እግዚአብሄር ወዶ ለሚጨምርልኝ ለእያንዳንዱ ቀን የሚያስፈልገኝን ሁሉ እንደሚያዘጋጅልኝ አምናለሁ፡፡
☞ሪቪል፤ እንደዚህ ያለ ህወት ግን ላገባችና በተለይም ልጆች እናት ለሆነች ሴት አይከብድም?
☞ዘሪቱ፤ እንደዚህ ያለ ህይወት ለማንም ቀላል አይደለም፡፡ በተለይም እንዳልከው፤ቤተሰብ ላለን ሰዎች ደግሞ የማይታሰብ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በስጋዊ አቅማችን ስንሞክረው ነው፡፡ ሰው የመሆንን ትርጉም ለመረዳት በፈቀድን መጠን ግን ራሱ እግዚአብሄር በእና ውስጥ ይችለዋል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን መከተል ማለት፤ ሰው በሀጢያት ከመውደቁ በፊት ወደ ነበረው ማንነት የመመለስ ጉዞ ማለት ነው፡፡ ያ ማንነት ደግሞ ከእግዚአብሄር የመሆንና ማንነቱን የማንፀባረቅ ህይወት ነው፡፡ በመሬታዊ ገደብ እሱን ማንፀባረቅ አይቻልም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አሰልጣኝነት ከመሬታዊ ገደብ ወደ እሱ ማንነት የሚያሻግረን መመሪያ ሁሉ ደሞ በቅዱስ ቃሉ ወስጥ አለ፡፡ ኢየሱስ ለምን አይነት ክብር እንደጠራን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ከንግዳችን፣ ከቤተሰባችንና ከራሳችን ጭምር በላይ እሱን እንድናስቀድም ነው፡፡ ይህ ሲሆን ብቻ ደቀመዛሙርቶቹ ልንሆን እንምንችል በግልፅ አስቀምጦልናል፡፡ ስለዚህ እሱን በመከተል ውስጥ ምንም አይነት አቋራጭ አልፈልግም፡፡
☞ሪቪል፤ ባለቤትሽ በዚህ ደስተኛ ነው?
☞ዘሪቱ፤ በጣም ደስተኛ ነው እንጂ፡፡ የምተገዛ ሚስት አድረጎለታል፡፡ ከዚህ ህይወት ጋር በተዋወኩባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በእኔ ላይ ባስከተለው የማንነት መናጋት ተከትለው በመጡ ጥፋቶች ብዙ ዋጋ ከፍሏል፡፡ ሚስትህ ፈርሳ እስክተሰራ መታገስ ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ከመጀመሪያዋ የተሻለች ሚስት እንዳለችው እሱ ምስክር ነው፡፡
ጌታ ይባርክሽ ዘሪቱ!!
@የእውነት ቃል
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45476#sthash.bBT1znLx.dpuf

“ዘፈኑን እየተውኩ ወደ ዝማሬው ዓለም እየገባሁ ነው” – ድምፃዊት(ዘማሪት) ዘሪቱ ጌታሁን [ቃለ-ምልልስ]

  • 707
     
    EmailShare
ዘሪቱ ከበደ ዘፈን አቁማለች ወይንስ አላቆመችም የሚሉ አናጋጋሪ ጉዳዮች በርካታ ጊዜያት ሲነሱ ቆይተዋል፡፡ ይሄንን ጉዳይ በተመለከተ ከእርሷ አንደበት ይህ ነው የሚባል ቁርጥ ያለ ምላሽ ሳይሰጥበት በመቆየቱ በበርካቶች ዘንድ አከራካሪ ጉዳይ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ዘሪቱ በየወሩ በአማርኛ ቋንቋ ታትሞ ለገበያ በሚበቃው ሪቪል (REVEAL)መፅሄት ባደረገችው ቃለ ምልልስ ከዘፈኑ አለም በመውጣት መንፈሳዊ ጉዞ ላይ መሆኗን አስታውቃለች፡፡ መፅሄቱ ከቀረበላት ጥያቄዎች መካከል ዋና ዋናዎች አለፍ አለፍ ብይ በመቃኘት ላስነብባችሁ፡፡
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45476#sthash.bBT1znLx.dpuf

Monday, July 13, 2015

Health: የሴትን ልጅ ልብ ለመማረክ እና ቀጣይነት ያለው ግንኙነት ለመመስረት የሚረዱ 6 ነጥቦች


ሴቶች በፍቅር ውስጥ አጥብቀው የሚፈልጉት ምንድነው?

በጥንዶች መካከል ለሚኖር የተሳካ የፍቅር ግንኙነት የፍላጎት መጣጣም እጅግ አስፈላጊ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ በዚህ ረገድ የሰው ልጆች በአጠቃላይ፣ ተመሳሳይ የሚመስል መሰረታዊ ፍላጎቶች ቢኖራቸውም ወንዶችና ሴቶች በየግል ከፍተኛ ቦታ የሚሰጧቸው የተለያዩ የስሜት ፍላጎቶች ይኖሯቸዋል፡፡
በግንኙነት መስክ ውስጥ ከምንጠቀምባቸው ክህሎቶች ሁሉ የመጀመሪያውና ጠቃሚ ነገር፣ የተጓዳኛችንን ጥልቅ ፍላጎት እና ተግባራት አስቀድሞ መረዳት ሲሆን፣ ይህ ማስተዋል አብሮን ያለውን ሰው ጠንቅቀን እንድንረዳ ስለሚያግዘን ችግሮች ከመሰከታቸው በፊት እንድንታደጋቸው ብሎም ከተፈጠሩ በኋላ በንቃት እና በጥበብ መለስ እንድንል ይረዳናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሰዎችን መሻት ሳይነግሩን የማወቅ ክህሎትን መማርና መለማመድ፣ አታካችና አድካሚ ቢመስልም ውጤቱ ግን እጅግ አመርቂ እንደሚሆን አያጠያይቅም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ በጥንዶች መካከል ተቀራርቦ ፍላጎቶችን ማውራት፣ ስሜትን መጋራትና ምክንያትን መግለጽ፣ የተሻለ ቅርርቦሽን በመፍጠር በትዳር ላይ መተማመንን ስለሚጨምር መልካም የሚባል ውጤትን ሊያስገኝልን ይችላል፡፡

ብዙውን ጊዜ ሰዎች ጥምረት የሚገቡት በዘርፉ በቂ የሚባል ዝግጅት ሳይኖራቸው እንደሆነ በተደጋጋሚ በዚህ አምድ ላይ የተነሳ ጉዳይ ነው፡፡ ይህም ትዳርን ውስብስብ እና አታካች እያደረገ መጥቷል፡፡ ከስልጣኔ ጋር ተያይዞ የመጣውም የሰው ልጅ ፍላጎት መጨመርና በትንሽ ነገር ያለመርካት አባዜ፣ በትዳር ውስጥ ተስፋ መቁረጥ የራሱን የሆነ ሚና ይጫወታል፡፡
በአንድ ወቅት ኖራ ሃይደን የተባለች የማህበራዊ ህይወት ተመራማሪ በመጽሐፏ እንዳለችው፣ አብዛኛው ወንዶች ስለ ሴቶች ያላቸው አተያይ እጅግ አስደንጋጭ ነበር፡፡ በወንዶች ዓይን ሴቶች ማለት፣ በዚህች ምድር ላይ ካሉ ነገሮች ሁሉ በላቀ ደረጃ እጅግ ውስብስብና፣ ፍላጎታቸው የማይታወቅ በቀላሉ የማይረኩ ፍጡሮች እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡
በዚሁ ጥናት ላይ የሴትን ልጅ ፍላጎት ከመረዳትና፣ ሴትን ልጅ ደስተኛ ከማድረግ ይልቅ (ኑዩክለር ፊዚክስ ማጥናት እንደሚቀል ገልጧል)
ይህ በእውነቱ ከእውነታው ጋር እጅግ የሚጣረስና ለሴቶች እጅግ አስደንጋጭ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ እሳቤ የሚመነጨው ሁላችንም በራሳችን ግለኛ ዓለም ውስጥ ተከልለን የራሳችንን ተፈጥሮና ፍላጎት ብቻ ስለምናዳምጥና የሌሎችን ማንነት ለማወቅና ተጣጥሞ ለመኖር ምንም አይነት ጥረት ስለማናደርግ ይመስለኛል፡፡
በተለያየ ጊዜ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች፣ ስለወንዶችና ሴቶች ረቂቅ ባህሪያትና ፍላጎት ለማወቅ በርካታ ጥናቶችን አካሂደዋል፡፡ ከእነዚህ ጥናቶች የተውጣጣውን መደምደሚያ መሰረት በማድረግ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ሴቶች የሚስማሙበትንና፣ ሴቶች ከትዳር አጋራቸው ወይም ፍቅረኛቸው አጥብቀው የሚሹትን 6 ነጥቦችን ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡

የሴትን ልጅ ልብ ለመማረክ እና ቀጣይነት ያለው ግንኙነት ለመመስረት የሚረዱ 6 ነጥቦች
(Caring) እንክብካቤ
1. በጥናቱ ውስጥ ከተካተቱ አብዛኛዎቹ ሴቶች በፍቅር ለሚንከባከብ ወንድ በቀላሉ እንደሚሸነፉ ገልፀዋል፡፡ ይህም የሚሆነው ሴቶች በተፈጥሮ ካላቸው የእንስትነት ባህሪ የተነሳ ከወንዶች ስሜት እና ፍቅርን ብቻ ሳይሀን፣ ከለላን፣ አለኝታነትን እና እክብካቤን አጥብቀው እንደሚሹ ተናግረዋል፡፡ ይሄም ምኞት እና ደህንነት እንዲሰማው ስለሚያደርግ ህይወትን ለቀቅ አድርገው በመመልከት የበለጠ ደስተኛ ያደርጋቸዋል፡፡

2. ትኩረት
ይሄንን ፍላጎት በሁለት ከፍለን ልናየው እንችላለን፡፡
2.1 መደመጥ
Joeu Barton የተባለ የስርዓተ ፆታ ተመራማሪ በጥናቱ ላይ እንዳሰፈረው፣ ሴቶች በቀን ውስጥ በአማካኝ 20,000 ቃላቶችን ሲጠቀሙ፣ በተቃራኒው ወንዶች ደግሞ 7,000 ቃላትን በመጠቀም ሀሳባቸውን ያስረዳሉ፡፡ ይህም በግልፅ እንደሚያስረዳን አንደኛ ሴቶች ለቋንቋ እና ለንግግር ፈጣን የሆነ አዕምሮ እንዳላቸው ሲሆን፣ ሌላው እና ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ፣ ሴቶች በንግግር ራሳቸውን በመግለፅ የበለጠ ነፃነት እንደሚሰማቸው ሲሆን ችግር በገጠማቸውና በጨነቃቸውም ጊዜ በማውራት ብቻ ያለ ምንም ተጨማሪ ምክርና መፍትሄ የተሻለ እፎይታና እረፍት እንደሚሰማቸው ሲሆን፣ በዚህም ጊዜ ንግግራቸውን በትኩረት ለሚያዳምጣቸው ወንድ የተለየ ፍቅርና አክብሮት ይኖራቸዋል፡፡
2.2 አንዲሰት ሴት አብሯት ካለ ወንድ ከፍቅርና እንክብካቤ ባሻገር አትኩሮ ትሻለች
በርካታ የህይወት ተሞክሮዎች እንደሚያመለክቱት፣ ሰዎች በተሰበሰቡበት ግብዣ ላይ አንድ ወንድ ፍቅረኛውን ወይም የትዳር አጋሩን ከሰዎች ጋር በሚኖረው ጨዋታ እጇን በማሻሸት ወይም በመሳም፣ አብሮነቱን ቢያረጋግጥላት በቀላሉ ልቧን በፍቅር በማቅለጥ የጥሩ ስሜት ባለቤት እንድትሆን እንደሚረዳ ይታመናል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ወንዶች በግንኙነት ውስጥ የሚመለከቱት፣ ትልቁን ምስል ብቻ በመሆኑ አብሮነት በራሱ በቂ ነው ብለው ሊያስቡ ይችላሉ፡፡ ሴቶች ደግሞ ባላቸው የተለያየ አፈጣጠር ዝርዝር ነገሮች ላይ ትኩረት ስለሚያደርጉ እያንዳንዱን እንቅስቃሴና ፍሰት ይከታተላሉ፡፡ በመሆኑም ወንዶች ፍቅረኛቸው ወይም የትዳር አጋራቸውን ከመነፈጠሯም ረስተው ለረጅም ሰዓት ከሶስተኛ ወገን ጋር ጨዋታ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በሴቶች አዕምሮ ውስጥ የመተውና አትኩሮት የማጣት ስሜትን ሊያጭር ስለሚችል ወንዶች ትኩረት ሊያደርጉበት ይገባል፡፡ ይሄንን በጣም ቀላል ግን ከፍተኛ ተፅዕኖ ሊፈጥር የሚችል እውነታ በመረዳት፣ በሄዳችሁበት ሁሉ ለሴቶቻችሁ አብሮነት ትኩረትና ዕውቅናን በመስጠት፣ ስሜታቸውን ከመጉዳት ብትታደጉ በምላሹ ፍቅር እና አድናቆትን ትቀበላላችሁ፡፡
እዚህ ጋ ልብ ልንለው የሚገባው እውነታ፣ ይህ ዓለም መስጠትንና መቀበልን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ የሰውን ስሜት ጎድቶ መልካም የስሜት ምላሽ መጠበቅ የዋህነት ስለሆነ፣ የምንፈልገውን ለማግኘት የሚፈለገውን መስጠት ግድ ይለናል፡፡

3. (Security) ጥበቃ
ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው፣ የወንድ ልጅ ከለላ እና መጋ መሆን፣ አሁንም ድረስ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ያለው እውነታ ነው፡፡ በዚህ በሰለጠነው እና የሴቶች እኩልነት በተረጋገጠበት 21ኛው ክፍለ ዘመን እንኳን፣ ሴት ልጅ በግሏ ገቢ በማስገኘት ሀብት ማካበት ብትጀምርም፣ የወንድ ልጅ ግብአት አቅራቢ እና ጠባቂ መሆን የሴትን ልጅ ስሜት ለማረጋጋት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህም በዘለለ ወንድ ልጅ ለሴት ከተለያየ አደጋ ጠባቂ ሆኖ መገኘቱ፣ እምነቷን የበለጠ ስለሚያጠነክረው ፍቅሯ እየጎለበተ ይሄዳል፡፡

4. Blind Loyalty (ፍፁም የሆነ ተአማኒነት)
በአብዛኛው አንዲት ሴት የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ስትሆን ወይም በወንድ ስትፈቀር ራሷን የተለየች ፍጡር አድርጋ እንድታይ ትሆናለች፡፡ ይህም ምን አልባት ከሴቶች ተፈጥሮ በተጨማሪ ወንዶች በፍቅር መብረቅ በተመቱ ጊዜ ያፈቀሯትን ሴት የግላቸው ለማድረግ የሚጠቀሙበት ገደብ የለሽ ሙገሳና ማሞካሸት፣ ሴቶች ለራሳቸው ያላቸውን አመለካከት በማዛባት፣ ውጫዊ መስህብን እንደ ብቸኛ የማንነታቸው መለኪያ አድርገው እንዲወስዱት ሳያስገድዳቸው አልቀረም፡፡
በመሆኑም በግንኙነት ውስጥ አንዲት ሴት የራሷን የመስህብ ደረጃ ጠንቅቃ ብታውቅም ባፈቀራት ወንድ እይታ ስትፈረጅ ‹‹ሁሉን ያስናቀች ቆንጆና ፀባየ ሰናይ መሆኗን እንዲነገራት ትፈልጋለች›› በማንኛውም አጋጣሚ የእሷ ወንድ የሌላዋን ቆንጆ አለባበስ ወይም አቋም ቢያደንቅ እሷን የወሰደባት ያህል ስለሚሰማት መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሰውን ቆንጆ በመቃረም፣ የትዳር አጋራችንን ስሜት ከምንጎዳ፣ ያገባናትን ሴት በትዳር አብረን እንድንኖር ውሳኔ ላይ ያደረሰንን መልካም ሰብዕና፣ ውበት፣ ወይም ተግባር በማስታወስ ከልብ የመነጨ አድናቆታችንን እና ሙገሳችንን መቸርን ብንለማመድ፣ ለትዳራችን ዕድሜ ማራዘሚያነት እንደሚጠቅም ጥናቶች እና ተሞክሮዎች ያመለክታሉ፡፡

5. Understanding (መረዳት)
በርካታ ሴቶች ከተጓዳኛቸው አጥብቀው የሚፈልጉት ተጨማሪው ነገር፣ የትዳር አጋራቸው የእነሱን ሚና እና በቤት ውስጥ ያላቸውን አስተዋፅ እንዲረዳ እና ዕውቅና እንዲሰጥ ነው፡፡ አንዳንድ ወንዶች ሴት ልጅ በቤት ውስጥ የምታከናውናቸውን ረቂቅና እጅግ ወሳኝ ተግባራት ባለማወቅ ዕውቅናን ሲነፍጉ ይስተዋላሉ፡፡ የሴት ልጅ ተፈጥሮ ማለትም በሴትነት የምታልፋቸውን ከባባድ ደረጃዎች፣ እርግዝና፣ ወሊድ፣ ማጥባት እና ልጅን መንከባከብ በምድራችን ካለ ነገር ሁሉ እጅግ ውድ፣ ፈታኝ እና ዋጋ ሊተመንለት የማይችል መሆኑን በመረዳት፣ ሴት ሆነው ያንን መክፈል እንኳን ባይችሉ፣ ክብደቱን በመረዳት እና ርህራሄ በማሳየት ሊያዝኑላቸው፣ ሊንከባከቧቸው እና ሊደግፏቸው ይገባል፡፡ ይሄም በሴት ልጅ ልቦና ውስጥ እስከ መጨረሻው ለመቀመጥ ጥርጊያ መንገድ ይሆናል፡፡

6. Sex (ወሲብ)
በተጣማሪዎች መካከል ፍቅር ሰምሮ ኑሮ እንዲደረጅ፣ በሐሳብ እና ፍላጎት መጣጣም ተቀዳሚው መሆኑ የማያጠያይቅ ሀቅ ነው፡፡ መከባበሩ፣ መፈቃቀሩና የሐሳብ መጣጣሙ እንደተጠበቀ ሆኖ በወሲብ አለመጣጣም ባለትዳሮች ከትዳራቸው ውጪ ሌላ ሰው መጎብኘታቸው የተለመደ ተግባር እየሆነ መጥቷል፡፡
ብዙውን ጊዜ ተጣማሪዎች፣ የሐሳብ አለመጣጣምን አቻችለውና ተቻችለው ኑሮን ሲገፉ ይስተዋላል፡፡ በአሁኑ ዘመን እየተስተዋለ የመጣው እውነታ እንደሚያመለክተን ግን በወሲብ አለመጣጣምን ማስታመም ስለሚያቅታቸው ወይም ከሌላ ጋ ሲማግጡ ወይም ከነጭራሹ ትዳርን ሲያፈርሱ ይታያሉ፡፡
በአብዛኛው በርካታ ወሲብ ነክ ፅሑፎችና ጥናቶች አንድን ወንድ እንዴት ለወሲብ ማነሳሳት እንዳለብን እና እንዴት እርካታ ላይ እንዲደርስ መርዳት እንዳለብን የሚገልፁ ናቸው፡፡ ይህም የሚያሳየው የሴት ልጅ ስሜት ይሄ ነው የሚባል አትኩሮት ከማህበረሰቡ ጭምር እንዳልተቸገረው ነው፡፡
Nora Hayden (How to satisfy a women every time) በተሰኘው መጽሐፏ ላይ እንደገለፀችው 80% የሚሆኑት ሴቶች፣ እውነተኛ እርካታ ላይ እንደሚደርሱ ሆኖም የትዳር አጋራቸውን ለማስደሰት ሲሉ ብቻ እርካታ ላይ እንደደረሱ እንደሚያስመስሉ ይናገራሉ፡፡ ይህም የሚሆነው ወንዶች በወሲብ ጊዜ የሴትን ልጅ ፍላጎት እና የስሜት ምስጢር መረዳት ስለሚያቅታቸው እነሱ በሚረኩበት መንገድ ይረካሉ ብለው በማሰብ ዘልማዳዊ የሆነውን ግንኙነት ያደርጋሉ፡፡ ሆኖም ፈጣሪ ወሲብን በትዳር መካከል እንድትደሰትበትና ትውልድን እንድናስቀጥልበት የሰጠን ታላቅ ፀጋ በመሆኑ፣ የሴትም ልጅ ስሜት መጠበቅ እና በባሏ መደሰት እንዳለባት በመረዳት በግልፅ በመወያየትም ሆነ በዘርፉ የተፃፉ ጽሑፎችን በማንበብ፣ ደስታውን የጋራ የማድረግ የወንዶች ተቀዳሚ ኃላፊነት ነው፡፡
በመጨረሻ ማንሳት የምፈልገው ነጥብ፣ ብዙዎች በትዳር ላይ በግንኙነት ዙሪያ በመርህ ደረጃ የሚነሱ ጠቃሚ ምክሮችን ማንበብ ፋይዳ ቢ መሆኑን ሲናገሩ ይታያል፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያትነት የሚያነሱት መከራከሪያ የፀሐፊዎቹ ወይም አነበብን የሚሉ ሰዎችን ግለ ህይወት በናሙናነት በማንሳት፣ በትዳር ህይወታቸው ስኬታማ አለመሆናቸውን ነው፡፡ እዚህ ጋ መረዳት ያለብን ቁም ነገር፣ ችግሩ ያለው ከዕውቀቱ ወይም ከንባቡ ሳይሆን ያወቅነውን እና የሰማነውን በልቦናችን አኑረን መተግበር ስለሚሳነን መሆኑን ነው፡፡ በመሆኑም ተፈጥሮ የለገሰችን ሰብዕና፣ በህይወት ተሞክሮ እና ዕውቀት በማዳበር፣ ያካበትነውን ዕውቀት በመተግበር እና ለውጥ በማምጣት ትዳራችን በግምት ሳይሆን፣ በጥበብ የምንመራትን ልቦና ይስጠን፡፡

ሴት ልጅ ምን መስማት አትሻም!
ሴቶች ስለ ሌላ ሴት ወይም ስለ ቀድሞ ጓደኛህ ስታደንቅ መስማት አትፈልግም፡፡ ከሌላ ሴት ጋር እንድታወዳድራትም እንዲሁ፡፡ ስለ ሰውነት ቅርጽና ውበቷ አድናቆት እንጂ ነቀፌታ ቅር ያሰኛታል፡፡ በድንገት ተሳስተህ የሌላ ሴት ስም ማንሳትም አይኖርብህም፡፡ በሌላ መንገድ ያስጠረጥርሃልና፡፡ ከአሁን ቀደም በነበረህ የሴት ልጅ ትውውቅ ውስጥ አላግባ ያደረካቸውን ነገሮች ማውራትህ ከባድ ግምት ውስጥ ይጥልሃልና በተቻለ መጠን ከኋላ ፈቅር ታሪክህ ውስጥ ጥሩ ጥሩውን እንጂ የሚያስተችህን ለመርሳት ወይም ላለማንሳት ጥረት አድርግ፡፡ በሌላዋ ላይ ይህን ያደረገ በእኔም ላይ ማድረጉ አይቀርም የሚል እምነት ይኖራታልና፡፡ ሴቶች ስለ አንተ ማወቅ የሚፈልጉትን ሲጠይቁህ እውነቱን መናገሩን ብቻ ነው የሚያዋጣው፡፡ ብዙ ጊዜ ሴቶች ለማወቅ በሚመስል መልኩ ይጠይቃሉ እንጂ የሚጠይቁትን ነገር ቀድሞውኑ ያውቁታልና አትዋሽ!
በተቻለ መጠን ከአሁን ቀደም ከነበረህ የፍቅር ትስስር እንዴት እንደተለያየህ ምክንያትህን አሳማኝነት ያለውና ከአንተ በኩል ከፍተኛ ጥረት ማድረግህ ላይ ያነጣጠረ ይሁን እንጂ ኃላፊነትህን ስላለመወጣትህ የሚያንፀባርቁ ምክንያቶችን ወይም ደግሞ ቀድሞውኑ ለመለያየት የማያበቁ ምክንያቶችህን ሴቶች መስማት አይፈልጉም!! ቢሰሙም ትዝብት ውስጥ ይጥሉሃልና ጠንቀቅ በል!!

source: www.zehabesha.com

Wednesday, July 8, 2015

የግል ባንኮች ትርፍ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል

የግል ባንኮች ትርፍ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል

የግል ባንኮች ትርፍ ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን ይጠበቃል
-ንግድ ባንክ ከታክስ በፊት 12 ቢሊዮን ብር ማትረፉ ተሰምቷል
በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ 16 የግል ባንኮች በ2007 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ እንደሚያገኙ ሲጠበቅ፣ አንዳንድ ባንኮችም የትርፍ ምጣኔያቸውን ከእጥፍ በላይ ማሳደጋቸው ታወቀ፡፡ 
የ2007 ዓ.ም. የባንኮቹ የመጀመሪያ ደረጃ ጥቅል መረጃ እንደሚያሳየው ሁሉም ባንኮች በአትራፊነታቸው ዘልቀዋል፡፡ ከአምናው የበለጠ ትርፍ ማግኘትም ችለዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ሁሉም ባንኮች ከታክስ በፊት አትርፈውት የነበረው ግርድፍ ትርፍ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ መሆኑ ይታወሳል፡፡
ሁሉም የግል ባንኮች በ2007 በበጀት የሒሳብ ሪፖርት ተቀናናሽ ሒሳብ ቢኖርባቸውም፣ ጥቅል ትርፋቸው ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ ይሆናል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት ከፍተኛ ትርፍ በማግኘት ዘንድሮም ከግል ባንኮች ከፍተኛውን ትርፍ ያስመዘገበው ዳሸን ባንክ ሲሆን፣ ከታክስ በፊት ከ950 ሚሊዮን ብር በላይ ማትረፉ ተጠቁሟል፡፡ በ2006 ዓ.ም. ባንኩ ከታክስ በፊት 928 ሚሊዮን ብር ማትረፉ አይዘነጋም፡፡
አዋሽ ባንክም ወደ 890 ሚሊዮን ብር ገደማ ማትረፉ እየተነገረ ነው፡፡ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ከግል ባንኮች በትርፍ መጠኑ ወደ ሦስተኛ ደረጃ ላይ የመጣው የኦሮሚያ የኅብረት ሥራ ባንክ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በማትረፍ ደረጃውን ይዞ መቀጠሉ ታውቋል፡፡
በበጀት ዓመቱ በትርፍ ምጣኔው ከፍተኛ ዕድገት ካሳዩ ባንኮች መካከል እናት ባንክ አንዱ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ ከ72 ሚሊዮን ብር በላይ ማትረፍ ችሏል፡፡ ይህ ትርፍ ባለፈው በጀት ዓመት ካገኘው ትርፍ ጋር በንፅፅር ሲቀመጥ ከእጥፍ በላይ ማደጉን ያሳያል፡፡ ባንኩ በ2006 በጀት ዓመት አስመዝግቦት የነበረው ትርፍ 31 ሚሊዮን ብር እንደነበር ይታወሳል፡፡
እንደ እናት ባንክ ሁሉ ከአምናው የትርፍ ምጣኔ ጋር ሲነፃፀር ከ50 በመቶ በላይ ብልጫ ያለው ትርፍ ያስመዘገበው አንበሳ ባንክ ነው፡፡ እንደ ምንጮች ገለጻ የአንበሳ ባንክ በ2007 ዓ.ም. ያልተጣራ ትርፍ 275 ሚሊዮን ብር ደርሷል፡፡ ይህ ትርፍ አምና አስመዝግቦት ከነበረው 127 ሚሊዮን ብር ጋር ሲነፃፀር ከ145 ሚሊዮን ብር በላይ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ 
አንበሳ ባንክ በትርፍ ዕድገቱ ብቻ ሳይሆን 580 ሚሊዮን ብር የነበረውን የተቀማጭ ገንዘብ አቅሙን ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር በማድረስ ከፍተኛ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉ ይጠቀሳል፡፡
ብርሃን ኢንተርናሽናል ባንክ በ2006 ዓ.ም. 131 ሚሊዮን ብር የነበረውን ትርፍ ወደ 140 ሚሊዮን ብር ማድረስ ችሏል፡፡ ንብ ባንክ ከ430 ሚሊዮን ብር በላይ እንዳተረፈ ሲነገር፣ አምና 350 ሚሊዮን ብር ያተረፈው አቢሲኒያ ባንክ ደግሞ ከ365 ሚሊዮን ብር በላይ ማትረፉ ተጠቁሟል፡፡ ደቡብ ግሎባል ባንክም ከአምናው በተሻለ ከታክስ በፊት 31 ሚሊዮን ብር ማትረፍ ችሏል፡፡ ይህ ትርፍ ከሁሉም ባንኮች ያነሰ ነው፡፡ ባንኩ አምና ያገኘው ትርፍ 19 ሚሊዮን ብር ነበር፡፡
ሌሎቹም ባንኮች የትርፍ ምጣኔያቸው ዕድገት የተለያየ ቢሆንም፣ የትርፍ ዕድገት በማሳየታቸው በአጠቃላይ የግል ባንኮችን የትርፍ መጠን አምና ከነበረበት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ያሳድገዋል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡ 
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2007 በጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር ከታክስ በፊት ማትረፉ ተሰምቷል፡፡ ንግድ ባንክ ባለፈው ዓመት 9.7 ቢሊዮን ብር ከታክስ በፊት ማትረፉ ይታወሳል፡፡ የዘንድሮው ግን ትልቅ ትርፍ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ 

Wednesday, July 1, 2015

ባዶ እግር መሄድ ለጤና የሚያስገኘው ጠቀሜታ

ከብዙ ዘመናት በፊት ጫማ የሚባለው የእግር ልባስ ከመሰራቱ በፊት ሰዎች እግራቸውን ባዶ ነበር የሚሄዱት።
በአሁኑ ጊዜም ቢሆን በገጠራማ አካባቢ ያሉ ሰዎች ያለ ጫማ በባዶ እግር ሲጓዙ ይስተዋላል።
ታዲያ በባዶ እግር መጓዝ ለጤናቸን በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተመራማሪዎች ያስታወቁ ሲሆን፥ ከነዚህም ውስጥ እግራችን የተስተካከለ እና ጤናማ የመንካት ስሜት እንዲሁም ከተፈጥሮ ጋር ቀጥታ ግንኙነት እንዲኖረው ያደርጋል።
በቀን ውስጥ ቢያንስ ለ5 ደቂቃ ያክል በባዶ እግር በመሄድ ወይም በመንቀሳቀስም ሰውነታችንን ተገቢውን ሀይል እንዲያገኝ እንደሚረዳንም ተመራማሪዎች ተናግረዋል።
በተጨማሪም በባዶ እግር መንቀሳቀስ ጥሩ ስሜት እንዲሰማን እንደሚያደርግም ተመራማሪዎቹ አስታውቀዋል።
በባዶ እግራችን በምንራመድበት ጊዜም የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖረን የሚያደርግ ሲሆን፥ በዚህ ጊዜም ከደም ዝውውሩ ጋር ሰውነታቸን በቂ ሀይል በማግኘት የሰውነታችን ክፍሎች እንዲነቃቁ ያደርጋል።
በቀን ውስጥ ቢያንስ ለ5 ደቂቃ ያከል በባዶ እግራችን መጓዝ ለልብ ህመህ እንዳንጋለጥ የሚረዳን መሆኑ የተነገረ ሲሆን፥ በተጨማሪም የምግብ መፈጨትን ለማስተካከል፣ የጭንቀት ስሜትን ለማሰወገድ እና የሰውነታችንን አቅም ማጣት ለመከላከል ይረዳናል።
በባዶ እግር ለመሄድ ጊዜ የማናገኝ ከሆነ ወይም የማንቸል ከሆነ ደግሞ እግራችንን እና እጃችንን ጠዋት እና ማታ በደንብ መታሸት /ማሳጅ/ መደረግ ይመከራል።
በዚህ መንገድ በመጠቀምም እግራችንን ባዶ በመሄድ የምናገኘውን የጤና ጠቀሜታዎች ማግኘት ይቻላል።
ተተርጉሞ የተጫነው፦ በሙለታ መንገሻ
Tran : FBC

Thursday, June 25, 2015

ዕንቁላል፣ ድንችና ቡና ---- share share if

ዕንቁላል፣ ድንችና ቡና
ልጁ ሁልጊዜ እየመጣች ታማርራለች፡፡ ኑሮ አልተሳካልኝም፣ አልሞላልኝም፣ ባሌ ያስቸግረኛል፣ ሥራ ቦታ ሰላም የለኝም፣ ጎረቤቶቼ ረበሹኝ፣ ሕመሙ በረታብኝ፣ ገንዘቤ አልበረክት አለ፤ ጓደኞቼ ያሙኛል፣ ልጆቼ ይበጠብጡኛል፡፡ ስለ ሸረኛ፣ ስለ መጋኛ፣ ስለ ምቀኛ፣ ስለ መተተኛ የማትለው ነገር የላትም፡፡ አባቷ የተለያዩ ታሪኮችን እየጠቀሰ ሊመክራት፣ ሊያጽናናትና ሊያበረታት ሞከረ፡፡ እርሷ ግን ማማረሯን፣ መማረሯንም አላቆመቺም፡፡ እንዲያውም ምሬቷ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ፤ ኑሮዋንም እየጠላቺው፣ ፈተናዋንም እየፈራቺው መጣቺ፡፡
አንድ ቀን መኖር አስጠልቷት፣ ችግሩና መከራም በርትቶባት፣ ምሬቷም ጫፍ ደርሶ መጣቺ፡፡ ‹‹በቃ ከዚህ በኋላ መኖር አልፈልግም፤ ይህንን ያህልስ እኔ ለምን እፈተናለሁ፤ ለምንስ ችግር ይበረታብኛል፤ ለምንስ ሁሉም ነገሮች ይጠሙብኛል፤ በቃ እኔ መኖር የለብኝም›› እያለች ታለቅስ ነበር፡፡
አባቷ ምክሩ ሁሉ እንዳልሠራ፣ የነገራትንም ሁሉ እንደዘነጋቺው ተረዳ፡፡
‹‹ተከተይኝ›› አላትና ወደ ማዕድ ቤት ገቡ፡፡
ወንበር ሰጣትና እርሱ ወደ ምግብ ማብሰያው ሄደ፡፡ ኮመዲኖውን ከፈተና ዕንቁላል፣ ድንችና የተፈጨ ቡና ይዞ መጣ፡፡ እርሷ ግን ትዕግሥቷ አልቆ ነበር፡፡ በልቧም ‹‹እኔ ኑሮ መርሮኝ እርሱ ምግብ ሊጋብዘኝ ይፈልጋል›› ትል ነበር፡፡ ‹‹አባቴ ችግሬን አልተረዳውም ማት ነው፤ ርቦኝ የተነጫነጭኩ መሰለው›› አለቺ፡፡ ‹‹እኔ ምግብ አልፈልግም፣ ቡናም አልጠጣም፤ በቃ እንዲያውም እሄዳለሁ›› አለቺው፡፡ ዝም አላት፡፡
ሦስቱ ምድጃዎች ላይ የሻሂ ማፍያዎችን ጣደ፡፡ በአንደኛው ላይ ዕንቁላሉን፣ በሌላው ላይ ድንቹን፣ በሦስተኛውም ላይ የተፈጨውን ቡና ጨመረው፡፡ ከዚያም ወደ ልጁ መጣና ከጎኗ ተቀመጠ፡፡ ‹‹ምን እየሠራህ ነው፤ የኔ ችግርና ምግብ ምን አገናኛቸው፤ ቤቴ ውስጥ ሞልቷልኮ፤ ሕጻን አደረግከኝ እንዴ፤ ዕድሌ ነው፣ አንተ ምን ታደርግ›› ትነጫነጫለች፣ ትቆጣለች፣ ታማርራለች፡፡ አባቷ ግን ዝም ብሎ ያዳምጣታል፡፡ ማልቀስ ጀመረች፡፡ ትከሻዋን እየደባበሰ ዝም አላት፡፡ ቃል ከአፉ አልወጣም፡፡
ውኃው መንፈቅፈቅ ጀመረ፡፡ አልፎ አልፎም ውኃው ከመክደኛው ወጥቶ እሳቱ ላይ ሲንጠባጠብ ‹ትሽ› የሚለው ድምጽ ይሰማ ነበር፡፡ አባቷ ድንገት ቆመ፡፡ ደንግጣ እንደተቀመጠች አቅንታ አየቺው፡፡ ‹‹በይ ተነሺ› አላት፡፡ ዘገም ብላ ተነሣቺ፡፡
‹‹ሦስቱንም የሻሂ ማፍያዎች ክፈቻቸው›› አላት፡፡
‹‹ለምን?›› አለቺ ግራ ተጋብታ፡፡
‹‹ግዴለም እሺ በይኚ››
መንቀር መንቀር እያለቺ ወደ ማንደጃው ሄደቺ፡፡
‹‹ሦስቱም ማፍያዎች ውስጥ ያሉትን ነገሮች አውጫቸው›› አላት፡፡ ዕንቁላሉንና ድንቹን በጭልፋ አወጣቺና ሰሐኖቻቸው ላይ አደረገቻቸው፡፡ ቡናውን ስኒ ላይ ቀዳቺው፡፡
‹‹እና ምን ይሁን?›› አለቺው ልጁ፡፡
‹‹ድንቹን ተጫኚው፣ ዕንቁላሉን ላጭው፣ ቡናውንም ቅመሺው››
‹‹ተመልከቺ፤ ድንቹ ውኃ ውስጥ ከመግባቱ በፊት ጠንካራ ነበረ፡፡ የፈላው ውኃ ግን ጠንካራውን ድንች ፈረካከሰው፡፡ ዕንቁላሉ የፈላው ውኃ ውስጥ ከመግባቱ በፊት ውጩ ጠንካራ ውስጡ ግን ፈሳሽና ስስ ነበረ፡፡ ውኃው ሲፈላ ግን ውስጡ ፈሳሽና ስስ የነበረው አስኳሉ ጠንካራ ሆነ፡፡ ቡናው ሲፈላ ቤቱን በመዓዛው ዐወደው፣ የአካባቢውንም ጠረን ቀየረው፤ ጣዕሙም ልዩ ሆነ፡፡
‹‹ሦስቱም በተመሳሳይ ማፍያ በተመሳሳይ ዓይነት እሳት ነበር የተጣዱት፡፡ ችሀግራቸው አንድ ነው፤ ለአንድ ዓይነት ችግር የሰጡት ምላሽ ግን የተለያየ ነው፡፡ ድንቹ ጥንካሬውን አጣ፣ ዕንቁላሉ አስኳሉ ጠነከረ፣ ቡናው መዓዛውና ጣዕሙን ይበልጥ እንዲያወጣው አደረገው፡፡ ልጄ ያንቺም ችግር ያለው ከገጠመሽ ችግርና ፈተና አይደለም፡፡ ለገጠመሽ ችግርና ፈተና ከምትሰጪው ምላሽ እንጂ፡፡ የተለያዩ ሰዎች አንድ ዓይነት ፈተና ሊገጥማቸው ይችላል፤ እንዲያውም በኑሮው ውስጥ የማይፈተን ሰው የለም፡፡ ነገር ግን ሰዎች ለችግርና ለፈተና የሚሰጡት ምላሽ የተለያየ ነው፡፡
‹‹ፈተና አንዳንዱን እንደ ድንች ጥንካሬውን አጥቶ እንዲፈረካከስ ያደርገዋል፡፡ አንዳንዱን ሰው ደግሞ እንደ ዕንቁላሉ ውስጡን ያጠነክርለታል፤ ሞራሉን ገንብቶ፣ መንፈሱን ያበረታዋል፡፡ እሳት የብረትን ዝገት እንዲያስወግድ ፈተናም የአንዳንዱን የስንፍና ዝገት ያስወግድለታል፣ ውስጡን ጠንካራ ያደርግለታል፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ችግርና መከራው፣ ፈተናና ስቃዩ ውስጣዊ መዓዛውንና ጣዕሙን እንደ ቡናው እንዲያወጣ ያደርገዋል፡፡ ውስጣዊ ችሎታውን፣ ዕምቅ ዐቅሙን፣ የተዳፈነ ተሰጥዖውን፣ ለሌሎች ሊተርፍ የሚችል ጸጋውን ያወጣለታል፡፡
‹‹ውሳኔው በእጅሽ ላይ ነው ልጄ፤ ችግር እንዳይመጣ፣ ፈተናም እንዳይኖር፣ መከራም እንዳይገጥም ተግዳሮትም እንዳይደርስ ማድረግ አይቻልም፡፡ ራስን ወይ ድንች፣ ወይ ቡና ወይም ደግሞ ዕንቁላል ማድረግ ግን ይቻላል፡፡››
ልጁ ጉንጩን ስማው አንገቷን እየነቀነቀች ወጣች፡፡ ውስጧም ‹ዕንቁላል፣ ድንችና ቡና› ይል ነበር፡

Friday, June 19, 2015

ህልም ምንድን ነው? ለምን እናልማለን?

 
ህልሞች በምንተኛበት ወቅት አዕምሯችን የሚፈጥራቸው የምስሎችና ታሪኮች ውህዶች ናቸው።

ህልሞች የሚያዝናኑ፣ የሚረብሹ፣ ቀልዶች፣ የፍቅር ግንኙነቶች፣ የሚያስፈራሩና አንዳንድ ጊዜም ያልተለመዱ ክስተቶች ሊሆኑ ይችላሉ።

ህልም ለምን እናያለን? ህልም አለማየትስ እንችላለን? ትርጓሜያቸውስ ምንድን ነው? እነዚህና መሰል ጥያቄዎችን አንስቶ የሚተነትነው ሜዲካል ኒውስ ቱደይ በቅርቡ

ህልምን አስመልክቶ የተደረገ ጥናትን ዋቢ አድርጎ ለእነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል።

የህልም እውነታዎች

- ምንም እንኳን የተወሰኑ ሰዎች ያዩትን ህልም በሙሉ የማያስታውሱ ቢሆንም ማንኛውም ሰው በእያንዳንዷ ሌሊት ከ3 እስከ 6 ጊዜ ያህል ህልም ያያል ተብሎ ይታመናል።

- እያንዳንዱ ህልም ከ5 እስከ 20 ደቂቃ ቆይታ እንደሚኖረውም ይነገራል።

- ካየነው ህልም 95 በመቶ የሚሆነው ከመኝታችን ስንነሳ እንረሳዋለን።

- ህልም ማለም የረጅም ጊዜ ትዝታዎቻችን ለማስታወስ ይረዳል።

- ሴቶች ከወንዶች ጋር ሲነጻጻሩ ስለ ቤተሰብ፣ ልጆች እና በቤት ውስጥ ስለሚከናወኑ ነገሮች ነው ህልም የሚያዩት።

- በህልማችን ከምናያቸው ሰዎች መካከል 48 በመቶ የሚሆኑትን መለየት(ማወቅ) እንችላለን።

- አልኮል እንቅልፍንም ሆነ ህልምን የማዘበራረቅ አቅም አለው።

- አይነ ስውራን ህልም ያያሉ፤ ግን በአብዛኛው ከስሜት እና ድምጾች ጋር የተያያዙ ናቸው።

ህልሞች ምንድን ናቸው?

ህልሞች ማንኛውም የሰው ዘር ልጆች በእንቅልፍ ሰአት የምንመለከታቸው ከየእለት ኑሮአችን ጋር የሚገናኝም ሆነ ምንም ግንኙነት የሌላቸው ታሪኮች ወይም ምስሎች እንዲሁም ስሜቶች ቅይጠይ ውጤቶች ናቸው።

ህልሙ የተፈጠረበትና አደረጃጀቱ ማለትም የታሪኩ ፍሰት በአንድ በኩል፤ የህልሞቹ ምንነትና ከአላሚው ጋር ያላቸው ዝምድና ደግሞ በሌላኛው ጠርዝ በሁለት ጎራ የተከፈሉ የህልም አጥኝዎች በህልም ላይ ለሚያደርጉት ጥናት በመነሻነት ያስቀምጡታል።

የኒዩሮ ሳይንስ አጥኝዎች አምስት የእንቅልፍ ደረጃዎችን በማስቀመጥ ህልም የሚከሰተው አይናችን በደንብ በሚርገበገብበት (step 5) ላይ መሆኑን ይናገራሉ።

የእንቅልፍ ምዕራፎች

1. የመጀመሪያው ምዕራፍ - ቀላል እንቅልፍ፣ አይናችን በዝግታ ይንቀሳቀሳል፣ እንዲሁም የአጥንቶቻችን እንቅስቃሴዎች ይቀንሳሉ። ይህ ምዕራፍ ከጠቅላላ እንቅልፋችን ከ4 እስከ 5 በመቶውን ይሸፍናል።

2. 2ኛው ምዕራፍ -  የአይን እንቅስቃሴ ይቆማል፣ የአዕምሮ ሞገዶች እንቅስቃሴ ይዘገያል፣ ከ45 እስከ 55 ከመቶ ይይዛል።

3. 3ኛው ምዕራፍ - በጣም የተዳከሙ የአዕምሮ ሞገዶች (delta waves) ይፈጠራሉ፣ ከ4 እስከ 5 በመቶ የእንቅልፍ ክፍልን ይሸፍናል።

4. 4ኛው ምዕራፍ - በ3ኛው እና 4ኛው ምዕራፍ ተቀስቅሶ የመንቃት እድሉ ዝቅተኛ ነው። ሁለቱም ምዕራፎች የጥልቅ እንቅልፍ (deep sleep) ጊዜያቶች ናቸው። በዚህ ምዕራፍ ምንም አይነት የአይን እና የጡንቻ እንቅስቃሴ አይኖርም።

በዚህ ስአት የሚቀሰቀሱ ሰዎች በፍጥነት የመንቃት እና የመደበት ችግር ያጋጥማቸዋል። ይህም ከአጠቃላይ እንቅልፍ ከ12 እስከ 15 በመቶውን ይሸፍናል።

5. 5ኛው ምዕራፍ - በዚህ ጊዜ የአተነፋፈስና የአይን እርግብግቦሽ ይፈጥናል፤ የቅንድብ ጡንቻዎችም ስራቸውን ያቆማሉ።  የደም ግፊት እና የልብ ትርታም ይጨምራል።

በ5ኛው ምዕራፍ የእንቅልፍ ጊዜ የሚቀሰቀሱ ሰዎች የተለያዩ ያልተለመዱ እና ቅዠት መሰል ታሪኮችን (ህልሞችን) የሚያወሩ ሲሆን፥ ከ20 እስከ 25 በመቶ የእንቅልፍ ጊዜን ይሸፍናል።

የህልሞች ጭብጥ

ወደ መኝታ ክፍላችን ከማምራታችን በፊት የምናስበው ነገር በምናየው ህልም ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል።

ለምሳሌ ተማሪዎች ስለሚወስዷቸው ፈተናዎች፣ በፍቅር ግንኙነት ውስጥ የሚገኙ ሰለ ፍቅረኞቻቸው፣ የግንባታ ባለሙያዎች ደግሞ ስለሚያስገነቧቸው ህንጻዎች ሊያልሙ ይችላሉ።

ህልሞች ከዘወትራዊው ህይወታችን ጋር የመተሳሰር እድላቸው ከፍተኛ ነው።

ህልሞችን ማስታወስ የሚከብደው ለምን ይሆን?

ህልም ካየን ከ5 ደቂቃ በኃላ ከ50 በመቶ የሚሆነውን የምንረሳው ሲሆን፥ ከ10 ደቂቃ በኃላ ደግሞ እስከ 90 በመቶውን እንደምንረሳው ነው የሚታመነው።

የህልም አጥኝዎች እንደሚሉት ከ95 በመቶ በላይ የሚሆነው ህልም ይረሳል።

ባለሙያዎቹ በነቃንበት ቅጽበት ያየነውን ህልምን ጽፈን ካልያዝነው የመረሳት እድሉ በጣም ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ።

ህልማቸውን የማያስታውሱ እንዳሉ ሁሉ ያዩትን ህልም በምሽት ለመተረክ የማይቸገሩ አንዳንድ ሰዎችም አይጠፉም።

ከረጅም ጊዜ በኃላ ህልም የማስታወስ ልምድ ያላቸውም ሰዎች አሉ።

ሜዲካል ኒውስ ቱደይ ይዞት የወጣውን ሙሉ መረጃ ለመመልከት ከፈለጉ ሊንኩን ይከተሉ http://www.medicalnewstoday.com/
source : FBXC

ህልም ምንድን ነው? ለምን እናልማለን?

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2007(ኤፍ.ቢ.ሲ) ህልሞች በምንተኛበት ወቅት አዕምሯችን የሚፈጥራቸው የምስሎችና ታሪኮች ውህዶች ናቸው።
ህልሞች የሚያዝናኑ፣ የሚረብሹ፣ ቀልዶች፣ የፍቅር ግንኙነቶች፣ የሚያስፈራሩና አንዳንድ ጊዜም ያልተለመዱ ክስተቶች ሊሆኑ ይችላሉ።

ህልም ለምን እናያለን? ህልም አለማየትስ እንችላለን? ትርጓሜያቸውስ ምንድን ነው? እነዚህና መሰል ጥያቄዎችን አንስቶ የሚተነትነው ሜዲካል ኒውስ ቱደይ በቅርቡ
ህልምን አስመልክቶ የተደረገ ጥናትን ዋቢ አድርጎ ለእነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል።

የህልም እውነታዎች

- ምንም እንኳን የተወሰኑ ሰዎች ያዩትን ህልም በሙሉ የማያስታውሱ ቢሆንም ማንኛውም ሰው በእያንዳንዷ ሌሊት ከ3 እስከ 6 ጊዜ ያህል ህልም ያያል ተብሎ ይታመናል።

- እያንዳንዱ ህልም ከ5 እስከ 20 ደቂቃ ቆይታ እንደሚኖረውም ይነገራል።

- ካየነው ህልም 95 በመቶ የሚሆነው ከመኝታችን ስንነሳ እንረሳዋለን።

- ህልም ማለም የረጅም ጊዜ ትዝታዎቻችን ለማስታወስ ይረዳል።

- ሴቶች ከወንዶች ጋር ሲነጻጻሩ ስለ ቤተሰብ፣ ልጆች እና በቤት ውስጥ ስለሚከናወኑ ነገሮች ነው ህልም የሚያዩት።

- በህልማችን ከምናያቸው ሰዎች መካከል 48 በመቶ የሚሆኑትን መለየት(ማወቅ) እንችላለን።

- አልኮል እንቅልፍንም ሆነ ህልምን የማዘበራረቅ አቅም አለው።

- አይነ ስውራን ህልም ያያሉ፤ ግን በአብዛኛው ከስሜት እና ድምጾች ጋር የተያያዙ ናቸው።

ህልሞች ምንድን ናቸው?

ህልሞች ማንኛውም የሰው ዘር ልጆች በእንቅልፍ ሰአት የምንመለከታቸው ከየእለት ኑሮአችን ጋር የሚገናኝም ሆነ ምንም ግንኙነት የሌላቸው ታሪኮች ወይም ምስሎች እንዲሁም ስሜቶች ቅይጠይ ውጤቶች ናቸው።

ህልሙ የተፈጠረበትና አደረጃጀቱ ማለትም የታሪኩ ፍሰት በአንድ በኩል፤ የህልሞቹ ምንነትና ከአላሚው ጋር ያላቸው ዝምድና ደግሞ በሌላኛው ጠርዝ በሁለት ጎራ የተከፈሉ የህልም አጥኝዎች በህልም ላይ ለሚያደርጉት ጥናት በመነሻነት ያስቀምጡታል።

የኒዩሮ ሳይንስ አጥኝዎች አምስት የእንቅልፍ ደረጃዎችን በማስቀመጥ ህልም የሚከሰተው አይናችን በደንብ በሚርገበገብበት (step 5) ላይ መሆኑን ይናገራሉ።

የእንቅልፍ ምዕራፎች

1. የመጀመሪያው ምዕራፍ - ቀላል እንቅልፍ፣ አይናችን በዝግታ ይንቀሳቀሳል፣ እንዲሁም የአጥንቶቻችን እንቅስቃሴዎች ይቀንሳሉ። ይህ ምዕራፍ ከጠቅላላ እንቅልፋችን ከ4 እስከ 5 በመቶውን ይሸፍናል።

2. 2ኛው ምዕራፍ -  የአይን እንቅስቃሴ ይቆማል፣ የአዕምሮ ሞገዶች እንቅስቃሴ ይዘገያል፣ ከ45 እስከ 55 ከመቶ ይይዛል።

3. 3ኛው ምዕራፍ - በጣም የተዳከሙ የአዕምሮ ሞገዶች (delta waves) ይፈጠራሉ፣ ከ4 እስከ 5 በመቶ የእንቅልፍ ክፍልን ይሸፍናል።

4. 4ኛው ምዕራፍ - በ3ኛው እና 4ኛው ምዕራፍ ተቀስቅሶ የመንቃት እድሉ ዝቅተኛ ነው። ሁለቱም ምዕራፎች የጥልቅ እንቅልፍ (deep sleep) ጊዜያቶች ናቸው። በዚህ ምዕራፍ ምንም አይነት የአይን እና የጡንቻ እንቅስቃሴ አይኖርም።
በዚህ ስአት የሚቀሰቀሱ ሰዎች በፍጥነት የመንቃት እና የመደበት ችግር ያጋጥማቸዋል። ይህም ከአጠቃላይ እንቅልፍ ከ12 እስከ 15 በመቶውን ይሸፍናል።

5. 5ኛው ምዕራፍ - በዚህ ጊዜ የአተነፋፈስና የአይን እርግብግቦሽ ይፈጥናል፤ የቅንድብ ጡንቻዎችም ስራቸውን ያቆማሉ።  የደም ግፊት እና የልብ ትርታም ይጨምራል። 
በ5ኛው ምዕራፍ የእንቅልፍ ጊዜ የሚቀሰቀሱ ሰዎች የተለያዩ ያልተለመዱ እና ቅዠት መሰል ታሪኮችን (ህልሞችን) የሚያወሩ ሲሆን፥ ከ20 እስከ 25 በመቶ የእንቅልፍ ጊዜን ይሸፍናል።

የህልሞች ጭብጥ

ወደ መኝታ ክፍላችን ከማምራታችን በፊት የምናስበው ነገር በምናየው ህልም ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል።

ለምሳሌ ተማሪዎች ስለሚወስዷቸው ፈተናዎች፣ በፍቅር ግንኙነት ውስጥ የሚገኙ ሰለ ፍቅረኞቻቸው፣ የግንባታ ባለሙያዎች ደግሞ ስለሚያስገነቧቸው ህንጻዎች ሊያልሙ ይችላሉ።

ህልሞች ከዘወትራዊው ህይወታችን ጋር የመተሳሰር እድላቸው ከፍተኛ ነው።

ህልሞችን ማስታወስ የሚከብደው ለምን ይሆን?  

ህልም ካየን ከ5 ደቂቃ በኃላ ከ50 በመቶ የሚሆነውን የምንረሳው ሲሆን፥ ከ10 ደቂቃ በኃላ ደግሞ እስከ 90 በመቶውን እንደምንረሳው ነው የሚታመነው።

የህልም አጥኝዎች እንደሚሉት ከ95 በመቶ በላይ የሚሆነው ህልም ይረሳል።

ባለሙያዎቹ በነቃንበት ቅጽበት ያየነውን ህልምን ጽፈን ካልያዝነው የመረሳት እድሉ በጣም ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ።

ህልማቸውን የማያስታውሱ እንዳሉ ሁሉ ያዩትን ህልም በምሽት ለመተረክ የማይቸገሩ አንዳንድ ሰዎችም አይጠፉም።

ከረጅም ጊዜ በኃላ ህልም የማስታወስ ልምድ ያላቸውም ሰዎች አሉ።

ሜዲካል ኒውስ ቱደይ ይዞት የወጣውን ሙሉ መረጃ ለመመልከት ከፈለጉ ሊንኩን ይከተሉ http://www.medicalnewstoday.com/
- See more at: http://www.fanabc.com/index.php/fbc-shows/item/8412-%E1%88%85%E1%88%8D%E1%88%9D-%E1%88%9D%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%8A%95-%E1%8A%90%E1%8B%8D-%E1%88%88%E1%88%9D%E1%8A%95-%E1%8A%A5%E1%8A%93%E1%88%8D%E1%88%9B%E1%88%88%E1%8A%95.html#sthash.WeY5aFyt.dpuf

Friday, May 29, 2015

Election of the next President of the AfDB

Election of the next President of the AfDB

 

The African Development Bank operates under the leadership of the President, who serves as the legal representative of the Bank, the Chairperson of the Board of Directors, and the Chief of Staff of the Bank. The President conducts the current business of the Bank, under the direction of the Board of Directors. The President is elected by the Board of Governors and serves a 5-year term, renewable once.
The current President, Dr. Donald Kaberuka, a national of Rwanda, was elected in July 2005, and commenced his first term on 1 September 2005. Following his re-election in May 2010, he commenced his last 5-year term on 1 September 2010.

Meet the candidates

Akinwumi A. Adesina

Sufian AHMED

Jaloul Ayed

Kordjé Bedoumra

Cristina Duarte

Samura M. W. Kamara

Thomas Z. Sakala

Birama Boubacar Sidibé

The Rules of Procedure Governing the Election of the President of the African Development Bank (Article 1), as amended, require that the Bank hold the election of the President during the Annual Meeting closest to the end of the term of office of the serving President. Accordingly, the Board of Governors will be electing Dr. Kaberuka’s successor on 28 May 2015, during the Bank’s Annual Meeting, scheduled to take place in Abidjan, Côte d’Ivoire, from 25 to 29 May 2015.
By Resolution B/BG/2014/06, adopted by the Board of Governors on 22 May 2014, and subsequent follow-up action by Management, as authorized by the Board of Governors, the following are the timetable and procedure fixed for the election for the Office of President:
Timetable:
  1. 1 July 2014 - Invitation from the Secretary General of the Bank to all Regional Member State (African) Governors for the submission of candidatures.
  2. 30 January 2015, no later than 5:00 p.m., Abidjan, local time - closing date and time for the receipt of candidatures.
  3. 10 – 12 February 2015 - meeting of the Steering Committee in Abidjan for the purpose of verifying and confirming candidatures.
  4. 20 February 2015 - settlement and publication of the list of duly registered candidates.
  5. 20 February 2015 - reminder to all candidates to submit statements of their vision for the Bank in both English and French, the two working languages of the Bank.
  6. 20 March 2015, no later than 5:00 p.m., Abidjan, local time - submission of a written statement by each candidate on her/his vision for the Bank in both English and French, the two working languages of the Bank.
  7. 27 May 2015, during the Annual Meeting of the Board of Governors - dialogue between candidates and members of the Board of Governors.
  8. 28 May 2015, during the Annual Meeting of the Board of Governors - Election for the Office of President of the Bank.
Procedure:
  1. Each candidate for the Office of President of the Bank shall have the profile prescribed in Article 36 of the Bank Agreement, specifically, that he/she shall be a national of a regional member state and shall be a person of the highest competence in matters pertaining to the activities, management and administration of the Bank.
  2. Candidatures for the Office of President of the Bank shall be deposited with the Secretary General of the Bank, for transmittal to the Steering Committee of the Board of Governors (the "Steering Committee"), by the Governor for the regional member State of which the candidate is a national. The candidature shall be presented by way of a letter from the Governor or by means of the attached Nomination Form duly completed and addressed to the Secretary General. The nomination shall be accompanied by a detailed curriculum vitae of the candidate.
  3. Candidatures shall be supported by one or more Governor(s) of regional member State(s). Such support may be given by telefax or electronic mail, addressed to the Secretary General of the Bank, and confirmed by sending a letter or the duly completedForm for Seconding a Nomination, to the Secretary General.
  4. The Steering Committee shall verify all candidatures to ensure conformity with the criteria for eligibility set forth in Article 36 of the Bank Agreement and the conditions of candidature set forth under the Election Rules. The Steering Committee shall then transmit the list of candidates to members of the Board of Governors on 20 February 2015.
All correspondence regarding the election should be sent to the address below:
Vice Presidency General Secretariat
African Development Bank

01 BP 1387
ABIDJAN 01
Côte d’Ivoire
Telefax: +225 20 32 01 70
E-mail: c.akintomide@afdb.org
All email inquiries regarding the process should be directed to prelec@afdb.org

Wednesday, May 27, 2015

ቦርዱ የ5ኛውን ሀገር አቀፍ አጠቃላይ ምርጫ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ5ኛውን ሀገር አቀፍ አጠቃላይ ምርጫ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አደረገ።


በዚህም መሰረት ከትግራይ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ31 መቀመጫዎች ውጤት ህውሃት 31 መቀመጫዎችን፣ ከአማራ ክልል ከደረሱት የ107 መቀመጫዎች ውጤት ብአዴን 107 መቀመጫዎች፣ ከኦሮሚያ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ150 መቀመጫዎች ውጤት ኦህዴድ 150 መቀመጫዎችን፣ በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ16 መቀመጫዎች ውጤት ኢሶዴፓ 16 መቀመጫዎችን፣ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከደረሱት የሰባት መቀመጫዎች ውጤት ሰባቱንም ቤጉዴፓ አግኝተዋል።

ከደቡብ ክልል ከደረሱት የ95 መቀመጫዎች ውጤት ዴኢህዴን 95 መቀመጫዎች፣  በጋምቤላ ክልል ጋህዴፓ ከሶስት መቀመጫዎች ሶስቱንም፣ በሀረሪ ክልል ሀብሊ ከ2 መቀመጫዎች አንዱን ሲያገኝ አንዱን ኦህዴድ፣ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከሁለቱ መቀመጫዎች አንዱን ኦህዴድ ቀሪውን ሶህዴፓ አግኝተዋል።

አዲስ አበባ ላይ ደግሞ ከ23 መቀመጫዎች 23ቱንም አግኝቷል።

በታደሰ ብዙአለም

የተጫነው:- በፋሲካው ታደሰ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ5ኛውን ሀገር አቀፍ አጠቃላይ ምርጫ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አደረገ።
በዚህም መሰረት ከትግራይ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ31 መቀመጫዎች ውጤት ህውሃት 31 መቀመጫዎችን፣ ከአማራ ክልል ከደረሱት የ107 መቀመጫዎች ውጤት ብአዴን 107 መቀመጫዎች፣ ከኦሮሚያ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ150 መቀመጫዎች ውጤት ኦህዴድ 150 መቀመጫዎችን፣ በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ16 መቀመጫዎች ውጤት ኢሶዴፓ 16 መቀመጫዎችን፣ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከደረሱት የሰባት መቀመጫዎች ውጤት ሰባቱንም ቤጉዴፓ አግኝተዋል።
ከደቡብ ክልል ከደረሱት የ95 መቀመጫዎች ውጤት ዴኢህዴን 95 መቀመጫዎች፣  በጋምቤላ ክልል ጋህዴፓ ከሶስት መቀመጫዎች ሶስቱንም፣ በሀረሪ ክልል ሀብሊ ከ2 መቀመጫዎች አንዱን ሲያገኝ አንዱን ኦህዴድ፣ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከሁለቱ መቀመጫዎች አንዱን ኦህዴድ ቀሪውን ሶህዴፓ አግኝተዋል።

አዲስ አበባ ላይ ደግሞ ከ23 መቀመጫዎች 23ቱንም አግኝቷል።
በታደሰ ብዙአለም

የተጫነው:- በፋሲካው ታደሰ
- See more at: http://www.fanabc.com/index.php/news/item/7926-%E1%89%A6%E1%88%AD%E1%8B%B1-%E1%8B%A85%E1%8A%9B%E1%8B%8D%E1%8A%95-%E1%88%80%E1%8C%88%E1%88%AD-%E1%8A%A0%E1%89%80%E1%8D%8D-%E1%8A%A0%E1%8C%A0%E1%89%83%E1%88%8B%E1%8B%AD-%E1%88%9D%E1%88%AD%E1%8C%AB-%E1%8C%8A%E1%8B%9C%E1%8B%AB%E1%8B%8A-%E1%8B%8D%E1%8C%A4%E1%89%B5-%E1%8B%AD%E1%8D%8B-%E1%8A%A0%E1%8B%B0%E1%88%A8%E1%8C%88.html#sthash.eIGsTDvi.dpuf

Tuesday, May 26, 2015

ፓስተር ዳዊት ሞላልኝ የተባለ ግለሰብ ህጋዊ የትዳር አጋሬን ባለቤቴን በቁሜ ነጠቀኝ:: አቶ ግርማ ዱሜሶ





ይህንን ጽሁፍ እራሳቸው አዘጋጅተው ከእነ ፎቶግራፋቸው የላኩት ግለሰብ ነዋሪነታቸው በሰሜን አሜርካ በአትላንታ ጆርጂያ ግዛት የሚኖሩት አቶ ግርማ ዱሜሶ የተባሉ ግለሰብ ህጋዊ ባለቤቴን ወ/ሮ ትግስት አበበ ደምሴን ፓስተር ዳዊት ሞላልኝ የተባለ ግለሰብ አስነውሮብኝ ትዳሬን አፍርሶታል:: እኔም እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ባደረሱብኝ ከባድ የህይወት ወንጀል በተደጋጋሚ ሁለቱም ግለሰቦች በቤተክርስትያን በኩል እንዲጠየቁልኝ እና ክርስቲያናዊ ይቅር እንድንባባል በተደጋጋሚ አሜርካ ውስጥ ለሚገኙ የኢትዮጵያናውያን ቤተክርስትያኖችን ጠይቄ ከቤተክርስትያኖቹ ምላሽ አጥቼያለሁ ስለሆነም ውድ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች የሆናችሁ እውነተኛ ክርስቲያኖች ይህንን እውነተኛ ታሪኬን አንብባችሁ ፍርዳችሁን እንድትሰጡኝ በጌታ ኢየሱስ ስም እማጸናችኋለሁ
ቀን 03/16/2015
ለቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲና
አትላንታ ጆርጂያ (USA )
ጉዳዩ ፡ በኔና በትዳሬ ላይ የደረሰውን በደል ፤ ነውርና ጥቃት ይመለከታል!
በእግዚአብሔር የተወደድክና በጣም የማከብርህ መንፈሳዊ አባቴ ( ፓስተሬ ) ነህና “አንተ “ ብልህ እንደ ድፍረት እንደማትቆጥርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ ። ተወልጄ ባደኩበት ማህበረሰብና እንዲሁም በእግዚአብሄር ቃል ውስጥም ቢሆን ሰው ፈጣሪን የሚያህል አምላኩና የሥጋ ወላጅ አባቱን “አንተ “ እንጂ “እርስዎ አምላኬ ሆይ “ ብሎ ስጣራ አልሰማሁም ።
በመሆኑም በሚገባኝ መንገድ ከልቤ በሆነ አክብሮት የጌታ ሰላም ፤ ምህረት ፤ጥበቃና ቸርነት እየተመኘሁልህ ፤ እንዲሁም ረጂም ዕድሜና በረከት ይብዛልህ ለማለት እወዳለሁ።
ፓ/ር ፡
ምንም እንኳን አንተን ማድከምና ማሰልቸት ቢሆንም ከዚህ ቀደም በአካልና በሰልክ ደጋግሜ ያጫወትኩህን (በሰፊው የተነጋገርንብትን ) እና አሁንም ድረስ የተቸገርኩበትን ብርቱ ጉዳዬን ከዚህ እንደምከተለው እንደገና ልገልጽልህ ወደድኩ ። ያም ጉዳይ ቀደም ሲል አንተም የሚታውቀውና በቅርቡም በቢሮህ ተገኝቼ በዝርዝር ገልጬልህ በተነጋገርነው መሰረት ሚስቴ የነበረችው ወ/ሮ ትግስት አበበ ደምሴና ፓ/ር ዳዊት ሞላልኝ አበጋዝ የሚባሉ ግለሰቦች ያደረሱብኝን በደልና ጥቃት የሚመለከት ነው ፡፤
እነዚህ ግለሰቦች እንደ ሌሎቹ ቅዱሳን አማኞች መልካምና ጥሩ ስነ-ምግባር ያላቸው እውነተኛ አገልጋዮች መስለውኝ አመንኳቸውና በቅንነትና በየዋህነት በልበ-ንጽህና ቀረብኳቸው እንጂ ከኋላዬ ዞረው ፈጣሪን በመዳፈር ለብቻቸው የተደበቀ እና ስውር የሆነ የግል ሚስጢርና ግንኙነት ኖሮአቸው ነውርን በትዳሬ ላይ ሊሰሩ ይችላሉ ብዬ ለማሰብ አንዳች ስጋትና ግምት አልነበረኝም ፤ ትዳሬን አፍርሰው ህይዎቴን አደጋ ላይ ይጥሉኛል ፤ ለከፋ ብስጭትና ኪሳራ ይዳርጉኛል ፤ ያዋርዱኛል ብዬ ጨርሶ አላሰብኩም ነበር ።
ይሁን እንጂ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች በመሆናቸው እምነት ጥዬባቸው ሳለ በገርነቴና በቀናነቴ በነዚህ በእግዚአብሔር አገልጋይ ተብዬዎች በደል ደረሰብኝ ፤ ተጎዳሁ ፤ ተጠቃሁ ።በዚህ በተፈጸመብኝ በደል የተነሳ እጅግ በጣም አዝኛለሁ ። በዋናነት የበደለኝም ብልጣ-ብልጡ አፈ-ጮሌ ፤ አስመሳይ መንፈሳዊ ሰው መሳይ ዳዊት ሞላልኝ የተባለ የ “FBI “ ቤተክርስቲያን ፓ/ርና መሪ ግለሰብ ነው ።
ይህ ያለንበት ዘመን በተለያየ ስፍራ በሃይማኖታዊና በመንፈሳዊነት ስም የምመላለሱ መንፈሰዊ ዱሪዬዎች እጅግ የበዙበት ወቅት በመሆኑ በእግዚአብሄርና በአገልግሎት ስም እያመኻኙ ባለቤቱ የከደነውን አለፈቃድ የሚከፍቱ ፤ ያስቀመጠውን አንስተው የሚወስዱ ፤ የሰውን ኑሮ የሚያናጉ ንጹሕ ፍቅር ባላቸው ጥንዶች መካከል እየገቡ በሰላምና ደስታ ፋንታ ጭቅጭቅንና ሃዘንን የሚያደርሱ የፍቅርና የቅድስና ጠላት የሆኑ ጉዶች የፈሉበት ጊዜ ነው ቢባል ያጋነንኩ አይመስለኝም ።
ፓ/ር ዳዊት ከዚህ ቀደም ማንንም ገጥሞት በማያውቅ ሁኔታ በሃይማኖት ተጀቡኖ ፤ በአገልጋይነት ሰበብ ተሸፍኖ፤ በእግዚአብሄር ስም እየነገደ ፤ በንቀት ድፍረት ተሞልቶ የሥጋ ፊላጎቱን ማርኪያና መደሰቻ ሲል ትዳሬን አፈራርሶታል ።ይህንንም ያደረጉት በተጋባን ዕለት ካረፍንበት ሆቴል ሙሽሪት( ወ/ሮ ትግስት) ቬሎ ልብሷን ቀይራ እኔን በሆቴል ውስጥ ጎልታኝ ሁለቱ ግን የግል ሥጋዊ ፊላጎታቸውን ለመፈጸም አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለቴ የድፍረት ሙከራ ፈጽመውብኝ አክሽፈዋለሁ ፤በመቀጠልም በቤተዘመድ በታላቅ እህቴ ቤት በተዘጋጀልን የመልስና ቅልቅል ጥሪ ላይም በዕለቱ የተጠሩት የሥጋ ዘመዶቼ እንኳ ሳይታደሙ በሚያስደነግጥ ሁኔታ እኔን (ሙሽራውንም) ሆነ ዘመዶቼን በንቀት ተመልክተውን ከምንም ሳይቆጥሩን አሳዝነውን እና አሳፍረው ግብዣውን አቋርጠው ተያይዘው መሄዳቸው ፤ በሌላ ቀን ደግሞ ወደ አረፍንበት ሆቴል ድረስ በራሱ መኪና ልወስዳት ሲመጣ ፈቃደኛ አለመሆኔን ለመግለጽ ቢሞክርም ጉልቤው ዳዊትና ሚስቴ ራሷ “ አንተን ያወቅንህ ገና ቅርብ ጊዜ ነው ፤ እኛ ግን የቆዬ ጓደኝነትና የጋራ አገልግሎት አለን ፤ ስለዚህ ከተስማማህ እረፍና ቁጭ በል ካልተመቸህ የራስህ ጉዳይ “ ብለው ዓይኔ እያየ ያለፈቃዴ ሚስቴን ነጥቆኝ ሄዷል ።
እንዲሁም ሌላ ጊዜ ደግም አብረን በአውሮፕላን እየተጓዝን ሳለን እኔን ባሏን “ አንተ መጽሐፍ አንብብ ፤ ዳዊት ብቻውን ነውና እሱ ወደ ተቀመጠበት ወንበር ሄጄ ላጫውተው “ በማለት በአውሮፕላን ውስጥም እንኳ ለብቸኝነት ዳርጋኛለች ። በአንድ ወቅት ደግሞ አንድ
ከተማ ውስጥ አብሬን በተመሳሳይ ሆቴል ውስጥ ባደርንበት ጊዜ (ዕለት) “ከዳዊት ጋር የአገልግሎት ጉዳይ የሆነ የሚናወራው ነገር አለን “ በማለት lab top computer ይዛ ያረፍኩበትን ሆቴል መኝታ ክፍል በር ዘግታብኝ ከሄደች በኋላ የት እንዳደረች ሳላውቅ በ2ኛው ቀን ምግብ መመገቢያው ውስጥ ከግለሰቡ (ዳዊት ) ጋር ቁርስ ስበሉ ለዚያውም ከሩቅ እስካ አየኋቸው ሰዓት ድረስ የትና ምን ሲሰሩ እንዳደሩ እግዚአብሔርና እነሱ ብቻ ናቸው የሚያውቁት ።
በሌላውም የምሳና የእራት ፤ እንዲሁም የቁርስና ቡና ሰዓታት እሷ ሁሌ ከሰውዬው (ዳዊት ) ጋር በመሆን ለብቻቸው ተጣብቀው ስላሉ (ስለምቀመጡ ) ከሙሽራዋ ሚስቴ ጋር ማዕድ ለመቆረስ እንኳ አልታደልኩም ነበር ።የስልክ አጠቃቀሟም ቢሆን ባለሁለት ቀፎ ስለሆነ ከዳዊት ጋር በስልክ ስታወራ ከኔ ርቃ ወይም መኝታ ቤት ገብታ ዘግታ በመቆለፍ ስለሆነ አብሬያት በቆየሁባቸው ጥቂት ወራት የብቸኝነትን ህይዎት ነበር የተጋፈጥኩት ።
አትላንታ ከተማ ተመልሰን በገዛ ቤታችን በእንግድነት ሰውዬውን ( ዳዊትን ) ባስጠጋነው ወቅትም ቢሆን እኔን ሳሎን ( ምግብ ቤት ውስጥ) ትተውኝ “ ስለ አገልግሎት የምንመካከረው ጉዳይ አለን” ወዘተ .. በማለት በራሴ መኝታ ቤት ወይም እንዲተኛበት በሰጠነው መኝታ ክፍል ውስጥ ቢያንስ ለ2 እና ከዚያ በላይ ሰዓታት ያህል በር በመቆለፍ ያደረጉትን አገልግሎት ፈጣሪ ብቻ ይመልከተው ከማለት ሌላ ለማውራት የማይቻለኝ የሚቀፍና ህሊናን የሚያደማ ነገር ነው ።
ይህ ብቻም ሳይሆን ባጋጣሚ እኔ አስቀድሜ ወደ መኝታ ቤቴ ውስጥ ከገባሁ ደግሞ ሌላ ሰበብ ይፈጥሩና “ ከዳዊት ጋር የሚንሰራው አጣዳፊ ጉዳይ አለኝ “ በማለት ኮምፒዩተሯን ይዛ እስከ እኩለ-ሌልት አንዳንዴም እስኪነጋ በሌላው ክፍል ወይም በሳሎናችን ውስጥ አብረው ያድሩ እንደነበር እነሱ ራሳቸው (ዳዊትና ትግስት ) ባሉበት ያንተ ረዳት ፓስተሮችም በተገኙበት ቢሮህ ውስጥ ለበርካታ ሳዓታት ( 7 ሰዓት ) ሙሉ በግልጽ ስንነጋገር አለመካዳቸው የሚታወስ ነው ።
ይህ ድንበርና ገደብ የለሽ መንፈሳዊ ሽፋንና ሃይማኖታዊ ሰበብ ከባል ስልጣንና ፈቃድ ውጪ የተሰወረ ሚስጢራዊ አገልግሎት ሊደረግ ሲታሰብ ምን ሊሆን እንደሚችል ፍርዱን ለፈጣሪና አመዛዛኝ ህሊና ላለው ሰው ሁሉ ትቻለሁ ።
ሌላው ደግሞ በአጋጣሚ እንኳ እግሯን አንድ ነገር ስያደናቅፋት ፤ ዕቃ ስወድቅባት እና ድንገት የሆነ ድንጋጤ ስሠማት በቁልምጫ “ዴቭ ድረስልኝ “ ስትል መስማት፤ እንዲሁም ከወላጆቿ ፤ከሥጋ ዘመዶቿና አብሮ አደግ ጓደኞቿ እንዲሁም ከኔና እሷ ፎቶግራፎች ይልቅ የዳዊትን ፎቶዎዎች በመኝታዬ ራስጌና ግርጌ ፤በሳሎን ቤትና የማድ ቤት ( ኩሽና ) ማቀዝቀዣ ላይ ዘወትር ማየት አዕምሮን የሚያደማና ህሊናን የሚያቆሽሽ ትዕይንት ነበር ። እስቲ አትታዝቡኝና በሷ ልብና አምሮ ውስጥ ይህ ዳዊት ምኗ ይሆን ? እኔስ ምኗ ነበርኩ ?
በአጋጣሚ ይህንን ደስ የማይል ታሪክና ዜና ለሚሰሙትም ሆነ እሮሮዬን ለሚያነቡት ሁሉ ለማለት የሚፈልገው ነገር ቢኖር 1ኛ እንዲህ ያለው እልህን ጭሮ ለከፋ ወንጀል የሚገፋፋው አደናጋሪና አጠያያቂ ክፉ ፈተና በገዛ ቤቴ ስለገጠመኝ እንኳን መሸከምና መታገስ ቀርቶ ለመስማትም ሆነ ለማውራት የማይቻለው የስቃይ ጦርነት እየተፈራረቀብኝ በእግዚአብሔር ጸጋ እስካሁን ድረስ በህይዎት መኖሬ እኔን እራሴ ስገርመኝና ስደንቀኝ የሚኖር የጌታ ጥበቃና ውለታ ነው ። እግዚአብሔር አምላክ የማይቻለውን አስችሎ ከክፉ ሁሉ ጠብቆ ነፍሴን ስላኖራት ክብር ምስጋና ይህንለት እላለሁ ፤ 2ኛ የተወደደች ፤ እግዚአብሔርን የሚታውቅ ፤ የምትፈራ ፤ በቃሉም የምትመራ ፤ ለፈጣሪ ፤ ለባሏ ፤ለህሊናዋ ፤ለኑሮዋ ታማኝ የሆነች መልካም ሴት ( ሚስት ) አግኝቶ አዕምሮው ካልተቃወሰ ( የጤና ችግር ከላጋጠመው ) በቀር ማን በዋዛ ሚስቱን ይጥላል ? ( ይተዋል ) ? ያልታደልኩትን እኔን ካልሆነ በቀር እንዲህ ዓይነቱ ውንብድና ፤ ሃፍረት የሌለው ጥቃት በማን ላይስ ደርሶ ያውቃል ?
ይህ ከመሆኑ በፊት ምንም እንኳን በውቅቱ የገባሁበት አጣብቂኝ ለማውራትም እንኳ የሚቀፍ ፤ ውስብስብ ፤ የከረፋ ቆሻሻና ጸያፍ ከመሆኑ የተነሳ ልታገሱት የማይቻል ቢህንም ፤ ለብዙ ዘመን ተጠምቼ ፤ ተመኝቼና በትዕግስት ጠብቄ ያገኘሁት ፤ ብዙ ዋጋ የከፈልኩበት ትዳሬ ስለሆነ ሙሉ ለሙሉ ከመበላሸቱ በፊት እስቲ ይሁን ብዬ ፤ ይቅር ለእግዚአብሔር በማለት ሁሉን ረስቼ ፤የማይቻለውን ችዬ ፤የማይረሳውን ረስቼ ፤ ነገን ብቻ ተስፋ በማድረግ እንደገና ጠጋግኜ ለማዳን የሞከርኩት ትዳሬ አፈር ድሜ በልቷል ።
እንዲህም እንኳን ሆኖ ወዲያውኑም ውዬ ሳላድር ባንድም ሆነ በሌላ ፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኔ ሰበብ የእግዚአብሔር ቤት መጠቋቋሚያና መሳለቂያ ከሚሆን ፤ሌሎች ቅዱሳንና እውነተኛ ታማኝ የሆኑ አገልጋዮችና መሪዎች ስም በመጥፎ ምሳሌ አብሮ ከሚነሳ ( ከሚጠፋ) ፤አገልግሎታቸው ከሚተች ፤ራዕያቸው ፤ ዓላማቸውና ትጋታቸው ዋጋ እንዳያጣ ፤ሳይጣን ከሚደሰት ፤ ሁላችንም የዓለም አጀንዳ ከሚንሆን፤ እግዚአብሔርንና መንፈሱን ከማሳዘን ፤ በተለይም በእምነታቸው ያልበረቱ አዳዲስ አማኞች ግራ እንዳይጋቡ እኔው ደግሜ ደጋግሜ ልጎዳና የሚቻል ከሆነ እስቲ እንደገና ትዳሩን ወደ ነበረበት ልመልሰው በማለት ያሰብኩት ቀናነት ዋጋና ትኩረት ተነፈገው።
ይህ ሁሉ ሆኖ ሰውየው ( ፓ/ር ዳዊት ) ይህንን ለፈጸመበት ጥፋትና አስነዋሪ ተግባር እስካሁን አልተገሰጸም ፤ አልተወቀሰም ፤ አልተከሰሰም ይቅርታም አልጠየቀም ። ነገር ግን የከበረውን ትዳሬን አፍርሶ እሱ ግን ዛሬም እያሾፈ በሰላም ይኖራል ፤ እንዳውም ይባስ ብሎ ቤተክርስቲያንን ይመራል ፤ የእግዚአብሄርን ቃልና ፈቃድ አስተምራለሁ ፤ የክርስቶስን ዓላማ እያራመድኩ፤ እያስፈጸምኩ ነኝ ይላል ።ግብረ አበሩ የሆነችውም ወ/ሮ ትግስት የራሷን ትዳር ንዳ ዛሬም አብረው በመሆን ሥፍራና ጊዜ እየቀያየሩ በየአብያተክርስቲያናቱ ዘንድ የተለመደውን ተራ ግርግር እየፈጠሩ መንፈሳዊ አገልጋይ ለመባል እየጣሩ ናቸው ። በኔ ላይ በለመዱት ዓይነት አኳኋን በተመሳሳይ ሁኔታ የኔ ዓይነቶቹን ሌሎች የእግዚአብሔር ህዝብ መተራመስ የለበትምና ድርጊቱ ተገላልጦ የማያዳግም ትምህርት ተሰጥቶ ህዝበ-እግዚዝብሔር ከመታለልና ተመሳሳይ ሰለባ ከመሆን መዳን አለበት ።
እነዚህ ፌዘኛ ግለሰቦች ፤ እጥቤ አሿፊ ጩሉሌዎች ሃፍረትና ይሉኝታ የሌላቸው ደንታ-ቢስ ባይሆኑ ነው እንጂ እንኳን በቤተ-እግዚአብሔር ውስጥ ካህን የሆነ ሰው ቀርቶ በዓለም ያሉቱ ካሃዲዎች ዘንድም እንኳ እንዲህ ዓይነቱን ወንጀል ስፈጽሙ ተሰምቶና ተደርጎ አይታወቅም ። እኔ ተራ እቃ ( ንብረት ) ብቻ አይደለም የጠፋብኝ ፤ ገንዘብና ጊዜ ብቻ አልነበረም የባከነብኝ ።ነገር ግን ትዳሬ እኮ ነው የፈረሰው ፤ መተኪያ የሌለውና የዚህ ምድር አስፈላጊ እና እግዚአብሔር ባርኮ ከፈቀደልን እድሎችና መብቶች አንዱ ነው ትዳር::
በሌላ አባባል ትዳር ከእግዚአብሔር ቃልና መመሪያ ውጪ ሌላ ፎርሙላ የለውም ፤ “ ሰው እናት አባቱን ይተዋል ከሚስት (ከባል ) ጋር አንድ ይሆናል፤(ይጣበቃል) “ እንደሚል አንድ ሥጋ ፤አንድ አካል ፤አንድ መንፈስ በመሆን አንድ ዓላማ ይዘው ጥንዶች በፍቅር የሚጣመሩበት ነው ። በዚህ ዓላማ የተጣመሩ ጥንዶች አንዳቸው ከሌላኛው የተለየ ፊላጎት እና የተደበቀ ልዩ ሚስጢርና ፊላጎት ሊኖራቸው አይገባም ፤
ነገር ግን ያልታደለው የኛ ትዳር ግን ገና ስፈጠር ከአጀማመሩ በጨቅላነቱ በአጭር የቀጩት ቢሆንም ትዳሬ ለኔ ህይወትና የከበረ የአምላኬ ስጦታ ነበር ። ትዳር አንዴ ብቻ ነው ፤ ማፍቀርም የምቻለው አንዲትን ሴት ፤ ለዚያውም ከተቻለ አንዴ ጊዜ ብቻ ። ዳስታም ቢሆን ሁሌ የለም፤ በየዓመቱ ሠርግ ለማድረግም የማይታሰብ ነው ። የሆነው ሆኖ ለአንዲት ደቂቃ ( ዕለትም ) እንኳ ቢሆን ያፈቀርኳትን ሴትና የከበረውን ትዳሬን በቀላሉ በፓ/ር ዳዊት ሞላልኝ ምክንያት አጥቻለሁ ።
ስለዚህ የከበረና የናፈቅኩት ፤ የተመኘሁት ጅምር ደስታዬ በእንጭጩ ከመቅጽበት በመቀጨቱ ወደ ሃዘንና ውርደት ተቀይሮ አንገት አስደፍቶኛል ፤እልሀኛ ፤ ቂመኛና በምሬት የተሞላሁ ተናዳጅ አድርጎኝ ሄዷል ።ነገ ደግሞ ምን እንደሚሆንና ምን እንደሚገጥመኝ እርግጠኛ አይደለሁም ።
ይህ ግለሰብ (ዳዊት) ግን ኑሮዬን አፍርሶ ፤ ህይዎቴን አበላሽቶ እንዲህ እንደ ቀልድ እያሾፈ ሊኖር ነው ? ካደረሰብኝ ብርቱ ፈተና የተነሳ በህይወት ለመኖር የማያስችል ፤ ለወንጀል የሚገፋፋ ፤ ለከፋ በሽታና ጥልቅ ሃዘን የምዳርግ ነው የገጠመኝ ። አረ ለመሆኑ በትዳርና በርስት ቀልድ አለ ? በዓይንና በሚስትስ መጫወት ይፈቀዳል ? እንኳን ግፍና በደል በግልጽ በቤቴ ተፈጽሞብኝ ቀርቶ ድርጊቱ ደግሞ ከጥርጣሬ ያለፈ የአደባባይ ጥቃት መሆኑ ይቅርና እንዲሁ በጥርጣሬም እንኳን ቢሆን በሚስቴ የልቅነት ድርጊት የተነሳ የመቅናትም ሆኔ የተጣመመውን የማቅናት መብቱ ለኔ የሚገባኝ ህጋዊ ባል (አባወራ ) አይደለሁምን ?
እስቲ ፍረዱኝ አንድ መንፈሳዊ አገልጋይ በአገልግሎት አሳቦ የራሱን ሚስት እቤቱ አስቀምጦ “ዘመዴ( ካዝኔ) ናት “ እያለ አንዲትን ሌላ ሴት እንደ ኮሮጆ ሸክፏት ፤ እንደ ሻንጣ እየጎተተ ከሀገር ሀገር ፤ ከከተማ ወደ ከተማ በየሆቴሉ ሁሉ አስከትሎ ስጓዝ ትንሽ እንኳን ይሉኝታ አይዘውም ? ያቺስ ሴት ብትሆን የ”ሶሎ ዘማሪ ፤ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች ፤ ወይም በመድረክ ላይ የቋንቋ አስተርጓሚ (ሰባኪ ) ሳትሆን የራሷን መደበኛ ኑሮ ትታ እንደ ጭን ገረድ በየሀገሩና መንደሩ የማንንም ወጠምሻ ጎሮምሳ ተከትላው እየዞረች አብራው በየሆቴሉ አብራው ስታድር ሁለቱም ህሊና የላቸውም ዎይ ?
ሁለቱም በገዛ ህሊናቸው ባይኮረኮሩ ፤በመንፈስ ቅዱስ ለምን አልተወቀሱም ? አዕምሮ ቢደነዝዝ ፤ ህሊናቸው የማይወቅሳቸው ፤ የአውዋቂን ምክርና ተግሳጽ የማይሰሙ ፤የህዝብን ትዝብትና ግልምጫን ከምንም የማይቆጥሩ ቢሆኑም ከነአካቴው ሁሉም ይቅርብኝ እንጂ እኔ ግን ትዳሬን በማንም ማስነካት ፤ ሚስቴንም ከማንም ጋር መጋራት ስላልፈለኩ ሳልወድ በግድ ከመካከላቸው ወጣሁ ።በዚህም በዘመኔ ሁሉ የማልረሳ የህይዎት ጠባሳ እና ስብራት ትቶልኛል ፤ አንዳንዴ ቁጭ ብዬ እያሰላሰልኩ ሳስብ ባልጠፋ ሰው ከነዚህ ቅንነት ከጎደላቸው ሰዎች ጋር እኔ ስገጣጠም እግዚአብሔር ለምን ዝም አለኝ ? ይህ ሁሉ ጉዳት ፤ መቁሰል ፤ መድማት ፤ መፈራገጥ ፤መላላጥ ብሎም ለብርቱ ሃዘን መጋለጥ ለማን ይጠቅም ይሆን ? ማንስ ይከብርበት ይሆን ? ማን ከስሮ ቀርቶ ማንስ ያተርፍ ይሆን ? እንዳው ባጭሩ ይህ ዳዊት የሚባል ሰውዬ እንዲህ አቃጥሎኝ አዋርዶኝ እስከመጨረሻው የሚሳካለት መስሎት ይሆን ? ደስታዬን እንዲህ በአጭር
አጨልሞ እሱ ግን እንደ ፈነጨ ሊኖር ? ለማንኛውም የመጨረሻውን ውጤትና ድምዳሜ በያንዳንዷ ሰኮንድና ደቂቃ ከአምላኬ በትዕግስት እጠብቃለሁ ።
ዶ/ር ፡
ፓ/ር ዳዊት የበደለኝ በብዙ አቅጣጫ ነው ፤ለምሳሌ አስቀድመን በጋራ በተስማማነው መግባባት መሰረት በራሱ ቤተክርስቲያን (FBI ) ባለሙያዎች ተቀርጸው የተሰሩትን የሠርጌን ቪዲዮና ከ5000 በላይ የሆኑ ፎቶግራፎችን ኮፒም ሆነ ኦሪጂናል ቅጂዎችን እስከ ዛሬ ድረስ እንዳለገኝ ከልክሎ በማስቀረቱ እንኳን ለዘመድ አዝማድ ፤ ጎደኞቼና ጎረቤቶቼ ፤ የስራ ባልደረቦቼ ፤ ለአብሮ አደጎቼ ይቅርና እኔ ራሴ የጉዳዩ ባለቤት የሆንኩት የሠርጌን ማስታወሻ የማየትና በታሪክነቱ ለማስቀመጥ ዳዊት ከልክሎኛል ። የጋብቻ ወረቀቴንም (Marriage Certificate ) እስካሁን ድረስ በጉልበቱ አስቀርቶታል ።
እኔ ብቻ ሳልሆን መልካም ትዳር እንዲገጥመኝ ተመኝተውልኝ ለጋብቻችን መሳካት የጸለዩ ፤ የለፉ ወገኖች ፤ የረዱን እና በብዙ የደከሙልን ፤ እሩቅና የተሻለ ደረጃ ላይ እንዲንደርስ ከልባቸው ያማጡ ጓደኞችና የስጋ ዘመዶቼ ሁሉ ጭምር በደረሰብኝ ሁኔታ አፍረዋል ፤ አዝነዋል ፤ተበሳጭተዋልም ።
በቆየው የሀገራችን አባባል “ከምርት እንክርዳድ አይጠፋም” እንዲሉ ጥቂት ግለሰቦች (የነዳዊት ግብረአበሮች ) ካላቸው ተመሳሳይ ሥነምግባር እና ባህሪ፤ የግል ጓደኝነት ፤ ውለታና ቀረቤታ የተነሳ ግድፈትና ነውራቸውን ሊያስተባብሉ ፤ እርኩሰትንና ቅጥፈትን አድበስብሰው ነጻ ናቸው ለማለት ደፋ ቀና ሲሉ ፤ የጥፋተኛውን ወንጀል ሸፋፍነው ነውረኛውን በጉያቸው ወሽቀው በመደበቅ ፤ሃቅን በሃሰት በመጨፍለቅ ፤ እኔን በማግለል ለነገራችን ቅርበት የሌላቸውን ንጹሃንን በማታለል ፤ እውነትን በማፈን ፍትህን ለማዛባት ትርምስ ፈጥረው ቅዱሳንን ግራ ለማጋባት ሞክረው ነበር ።
ነገር ግን እኔን የገረመኝና ያናደደኝ “ በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት “ ዓይነት አባባል ካልሆነ በቀር የገጠመኝ መከራና ፈተና ከመርግ ይልቅ እጅግ የሚከብደው ውርደትና ሃዘን ፤ ጥቃት ሁሉ እነሱን ገጥሞ ቢሆን ኖሮ ( ራሳቸው በኔ ቦታ ቢሆኑ ኖሮ ) ያለማጋነን ነፍሳቸውን በዛፍ ላይ የሚያንጠለጥሉ ፤ ምናልባትም አዕምሮያቸውን ስተው ፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ወይም ደግሞ በንብረትና በሰው ህይዎት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ እንደሚችሉ አልጠራጠርም ። ፓ/ር ዳዊት ራሱ እኔን የገጠመኝ ዕጣ-ፋንታ ገጥሞት ቢሆን ኖሮ ምን ይውጠው ነበር ? ሁሉም ቢጤዎቹ ካንድ ጉድጓድ የተቀዱ ፤ አንድን ጽዋ በጋራ የጨለጡ አሳፋሪዎች እና selfish ስለሆኑ ታዘብኳቸው ።
መቼም ቢሆን እንደ ሰው ያልሆነ እግዚአብሔር ጻዲቅና መልካም አምላክ ነውና ምህረት ፤ ቸርነት ፤ ጥበቃው ፤ ፍቅሩ ፤ ርህራሄው ያማያልቅበት ፤ ወረት የሌለው በመሆኑ ራራልኝና አጽናንቶ የማይቻለውን እንዲችል ረዳኝና ከክፉው ሁሉ ጠብቆ እስካሁን በህይዎት አኖረኝ እንጂ የተጋራጠብኝ ፈተና ማንም ብርቱ ነኝ ባይ ልታገሰውና ልቋቋመው የማይቻል ከባድ አደጋ ነበር ። የራራልኝ እግዚአብሄር ይመስገን ፤ ነገንም በርሱ ፈቃድ እኖራለሁ ፤ አሜን ።
ለመሆኑ በማንአለብኝነት ይህንን ሁሉ ጥቃት የሚፈጽም ይህ ጉልቤ ጀብደኛ (ዳዊት ) ማን ነው ? “ከወፈሩ አይፈሩ” ነው ነገሩ ? ወይስ ምንን ተማምኖ ? ይህንን ሁሉ በደልና ግፍ ሰው አይቶ ባይፈርድልኝ እግዚአብሔርስ ይወደዋል ዎይ ? ይህ ግድየለሽ ሰላሜን አደፍርሶ ፤እና ህይዎቴን አበላሽቶ ፤ ኑሮዬን አናግቶ እሱ ግን ልፈነጭ ? አይደረግማ !!
የፈጸመውን ድርጊት ተናግሮ ፤ ጥፋቱ ተዘርዝሮ ስህተቱ ተብራርቶ ነውርና ድፍረቱ ተገልጦ ለአደባባይ መቅረብ አለበት ። ምናልባት በመንፈሳዊ አገልግሎት ሽፋንና ሰበብ ያካባተው ሃብት ፤ ያተረፈው ዝናና ክብር አለኝ ብሎ ስለምያስወራ ፤ እንዲሁም የጥፋቱ ተባባሪ ቢጤዎች ፤ ጓደኛና ምኑንም በውል ያልተረዱ ቅንና የዋሆች ያለእውቀት ደጋፊዎች ልኖሩ ስለምችሉ ከሰው ዘንድ እውነተኛ ፍርድ ላላገኝ እችላለሁ ፤ ቢሆንም ከቲፎዞ (ደጋፊ) ብዛት የተነሳ የፍትህ ዳኛና ሃቀኛ ምስክር ስለማይገኝ ፤ ትዳሬ ፈርሶ ፤ህይዎቴ ተበላሽቶ ፤ ራዕዬ ተጨናግፎ ፤ ተስፋዬ ጨልሞ ከአቅሜ በላይ የሆነ አበሳና ውርደት ተሸክሜ ለመኖር ለኔ እጅግ ከባድ ነው ።
ፓ/ር፡
ከዚህ ቀደም ውድ ጊዜህን ሰውተህ ከረዳቶችህ ጋር በመካከላችን ተገኝተህ ለበርካታ ሰዓታት እኛን ( ዳዊት ፤ ትግስትንና እኔን ) ስታወያየን አንተ ራስህ ሰምተህ ፤ አይተህ ፤ግንዛቤ እንዳገኘሀው (እንዳረጋገጥከው ) ፓ/ር ዳዊት እኔና ሚስቴን ባጋባበት ዕለት ወዲያውኑ ከመቅጽበት ከሚስቴ ጋር እንዲንለያይ ዋና ምክንያት ሆኗል፤ ለዚያውም አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለቴ ሦስቴም እንጂ ።
ይህ ድርጊት በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአበሻ ታሪክ በኔ ብቻ ካልሆነ በቀር የት ሀገር ? መቼ ? በነማን ላይ ደርሶ ያውቃል ? እነዴትስ በጫጉላ ሽርሽር ወቅት ( honey moon time ) ሙሽሪት ሙሽራውን ትታ ፓስተሯን ለመዝናናት በሚል ሰበብና ድፍረት የቃል ኪዳን ሙሽራ ባሏን በሆቴል ውስጥ እንዲሁም በሌላ ጊዜ ደግም በባዶ መኖሪያ ቤት ውስጥ ጥላ ፤ጨርቋን ጥላ እና አዕምሮዋን ስታ ለ7 ቀንና ሌሊት ያህል የምትጠፋው ? በገዛ ቤታችን ውስጥስ ቢሆን ባልን ሳሎን ውስጥ ትቶ ከፓ/ር ጋር መኝታ ቤት ገብቶ በር በመቆለፍ ለሰዓታት ያህል አገልግሎት ላይ ነን ማለትና…ወዘተ ጸያፍና ድፍረት የተሞላባቸው አሳፋሪ ድርጊቶችን መፈጸም የጤና ነው ? ወይስ የእብደት ?
እንዲህ ዓይነቱ ነውርና ልቅ የሆነው ጥፋት ከልክ ያለፈ ፤ መረን የለቀቀ ፤ሚዛኑን የሳተ ፤ ከድንበርም የዘለለ ስለሆነ ልሸከመው የማልችለው በቤቴ ፤ በትዳሬ እየተፈጸመ ነውና የከፋ ነገር ከመምጣቱ በፊት ይታሰብበት በማለት በግልጽ ውይይትና ምክክር አድርገን እናስወግድ ፤ መፍትሄ በመፈለግ እርማት እንውሰድበት የሚል ገንቢ እና ቀና ሃሳብ እንደ አገልጋይ ክርስቲያንና አማኝ በአክብሮት ያቀረብኩላቸው አቤቱታ ና ጥያቄ “ ጌታ ይገስጽህ ! ይህ ሰው (ፓ/ር ዳዊት ) በእግዚአብሔር የተቀባ ፤ የተለቀለቀ መንፈሳዊ ሰው ነው ፤ ስለዚህ ጌታ በቀባው ላይ እጅህን አታንሳ ፤ “ ተብዬ ተኮነንኩ ። ራሱ ዳዊትም ቢሆን “ ያቀረብከው ጥያቄ ለኔ የሚመጥን አይደለም “ በማለት ናቀኝ እንጂ ጆሮውን እንኳ ለጥቂት ለደቂቃ ያህል ልሰጠኝ አልፈለገም ፡፡ በዚህም ተግባሩ የኔን መብት ለራሱ አደረገ ፤ እኔን ግን ለውርደት ለጭንቀት ፤ ለሃዘንና ለኪሳራ ዳረገ። አሁን በዚህች ደቂቃና ሰከንድ ይህንን ደብዳቤ በማዘጋጅበት ሳምንት (ቀናት ) በሀገር ቤት ኢትዪኦጵያ ውስጥ ከዚህቺው ሴት ጋር አብረው ናቸው ። ጨርሰው ልላቀቁ ስላልቻሉ በረቀቀ ሚስጢር ያለሀፍረት አሁንም አብረው እንደተጣበቁ ናቸው ።
ፓ/ር ፡
ምናልባት “ድፍረት ፤ ንቀት ፤ ትዕቢት ወዘተ…የተባሉትን ዓረፍተነገሮች (ቃላት) ለምን ተጠቀምክ ? ለምንስ ደጋገምክ ? ትለኝ ይሆን ?በጣም የሚያናድደው ፤የሚያስገርመውና አሳፋሪው ነገር ይህ ግለሰብ ራሱን ነቢይ እያስባለ መገለጥ ቢጤ እያቀነባበረ የእግዚአብሔርን ቃል እየጠቃቀሰ “ የዓዞ እንቧ “ እንደተባለው የሀገራችን አባባል “ኢየሱስ ያድናል “ ወዘተ….በሚል ቋንቋ የዋሁን ህዝበ-እግዚአብሔር ፊት በእግዚአብሔር ፑልፒት ላይ እየተንጎራደደ መፈክር እያሰማ የትዳርን ክቡርነት ፤ የባልና ሚስትን ህጋዊ ግንኙነት (አብሮነት) ከፈጣሪ የሆነና የተቀደሰ ቃል ኪዳን መሆኑ እንደት ተሰወረበት ? የራሱን ሚስት እቤቱ አስቀምጦ በአፍላ ፍቅራችንና ጅምር ትዳራችን ወስጥ እንደ እርጎ ዝንብ ጥልቅ ብሎ ለምን ገባብን ?
ለነገሩማ ቀድሞውንም ቢሆን ሴራቸው ስላልገባኝ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው በሚል አምኜ ቀረብኳቸው እንጂ እነሱ ግን ያኔም ቢሆን ማስመሰል በተሞላበት የህሰት ትንቢት አደንቁረውኝ ፤በመገለጥ አዋክበውና አጣድፈውኝ ለስውር ዓላማቸውና የግል ጥቅማቸው ማሟያ አቅደው ለይስሙላ ከአጠገባቸው ሊያስቀምጡኝ ፈለጉ እንጂ ያኔ ያላወቅኩት ቆይቼም ቢሆን በኋላ እንዳረጋገጥኩት ለ5 ዓመታት ያህል ዘልቆ የቆየ ግነኝነትና አሳፋሪ ቃል-ኪዳን ነበራቸው ።
በሀገራችን አባባል “ የአይጥ ምስክር ዲንቢጥ ናት “ እንደተባለው ካልሆነ በቀር እነዚያ ቢጤዎቹስ ቢህኑ “ እሱ ዳዊት የፈጸመብህ ድርጊት አግባብ ባይሆንም ጸጥ ፤ ለጥ ብለህ ተቀበልና ዝም በል ። አለበለዚያ ትቀሰፋለህ ፤ ወደ ሲኦል ትገባለህ፤ ለሳይጣን አሳልፎ ይሰጥሃል ፤ ትረገማለህ “ ወዘተ.. እያሉ አስፈራርተው ሲያሸማቅቁ ፤ በሌላ በኩል ደግሞ “ የሚናከብረውና በጌታ የተቀባ ፤የተለቀለቀ ፤በመገለጥና ጥበብ ብሎም የፈውስ ጸጋ ስጦታ አገልግሎቱ እጅግ የጠለቀ ፤ የመጠቀ ነውና የተደረገብህን ድርጊት ሁሉ አሜን ብለህ አርፈህ ኑር” በሚል ማባበል እኔን አታሎ ለማዘናጋት ለሃጥያት ሲተባበሩ ፤በሃሰት ሲመሰክሩ ፤ አንዳች ፈጣሪን ባይፈሩ ፤ለማንም ባይራሩ ፤ ለሃቅ ባይቆረቆሩ ፤ በእግዚአብሔርም ሳይጠሩ ለክብራቸው ፤ ለዝናቸው ፤ ለጥቅማቸውና ለእንጀራቸው ያንን ያህል በድርቅና ከተከራከሩ ትዳሬ ደግሞ ለኔ ከእንጀራና ሆድ የሚበልጥ ፤ ከዝና ፤ ከክብርና ጊዜያዊ ጥቅም ያለፈ ህይዎትና ኑሮዬ መሆኑን ለማወቅ እንዴት ተቸገሩ ?
ስለዚ ይህ መቼም “ በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት “ እንዲሉ ንቀት ፤ ትዕቢት፤ ድፍረትና “ ነጌ በኔ” አለማለት ካልሆነ በቀር ሌላ አንዳችም ምክንያት ሊኖር አይችልም እንዳውም በኔ ቦታ ሆኖ ካዩት ከድፍረት ያለፈ ጭካኔ ነው እላለሁ ። እኔ ደግሞ ተበድዬ ፤ ተጎድቼ ፤ ተጠቅቼ ፤ ተደፍሬና ተንቄ ሽንፈትን አሜን ብዬ በውርደትና በሃዘን የተሞላ ህይዎት ለመኖር ስለማልፈልግ አንድ ስፍራ ላይ ባንድ ወቅት
ባንዴ መቋጨትና መቆረጥ አለበት ። ያንን ለማምጣት ደግሞ እስከ ህይዎቴ ፍጻሜ ድረስ ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ ነኝ ፤ የእውነት አምላክ ፤የቅኖች ወዳጅ ፤ የምስኪኖች አለኝታ የሆነው ፈጣሪዬ ደግሞ ለአረመኔዎችና ለነውረኞች አሳልፎ ስለማይሰጠኝ ፤ ጥቃቴንም ስለማይወድ በሱ እየታመንኩ ላደርገው የወሰንኩትን በአርሱ ታምኜ እፈጽማለሁ ።
አዎን ከዚህ በላይ ያልኩት ሁሉ በኔ ላይ የተፈጸመ እውነት የሆነ ዓይን ያወጣ ጥርሱን ያገጠጠ ብልግናና በቃላት የማይገለጽ ከባድ በደልና ግፍ ነበር ። ዛሬ ዛሬ በየቦታው አፈ-ጮማ አተራማሽ መተተኛና ፈጣጣ ጋጠ-ወጥ ጮሌ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቤት እያጥለቀለቀ የስንቱ ምስኪኖች ትዳር ደቀቀ ? አረ የፍትህ ያለህ ! የጽድቅ ያለህ ! የቅድስና ያለህ ! አለቅን ፤ ደቀቅን !! እባካችሁ ድረሱልን !!!
ለመሆኑ ትዳርን ማፍረስ ቤተክርስቲያንን ማፍረስ አይደለምን ? ለዚያውም የቤተእምነት መሪና አገልጋይ ሆኖ የንጹሃንን ትዳር እያረከሱ ፤ ቤተሰብን እያፈረሱ ቤተክርስቲያንን እያስወቀሱ “የተቀባ ፤የበቃ “ ወዘተ … አገልጋይ መሆን ይቻላል ? ትንቢት እየተናገሩ መገለጥ እየቀበጣጠሩ የትዳርን ክቡርነት እንዴት ዘነጉ ? ሚስት ለባል ፤ ባልም ለሚስት ብቻ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ለነሱ ብቻ ሲባል ሌላ ነቢይ መቅጠር ( ልዩ መላዕክት ከሰማይ ማስመጣት ) አለብን ዎይ ? “እግዚአብሔር እንዲህና እንድያ ብሎሃል” እያለ ሌት ተቀን እየሰበከ እራሱ ግን ለምን አልኖረበትም ? ራሱ ልፈጽመው ያልቻለውን በጉልበት ልያሽክመን ለምን ይጥራል ?
ደግሞስ የኔ አንዲቷ ነጠላ ህይዎት (ነፍስ) ቤተክርስቲያን አይደለችምን ? የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ ፤ የክብሩም መገለጫ ቤተክርስቲያን አይደለሁም ዎይ ? ይህ ዓይኑን በጨው የታጠበ ደፋር ግለሰብ ህይዎቴንና ዕድሌን አበላሽቶ ደስታዬን ወደ ሃዘን ለውጦ ቤተክርስቲያንን ሊመራ ?ህዝብን ሊያገለግል ? “ It is not fair “ (ፍትሃዊና አግባብ አይደለም ) ፤ እሷስ ወ/ሮ ትግስት ብትሆን ልማደኛ ባትሆን ኖሮ ከበፊተኛው ስህተቷ ለምን አልታረመችም ? ከኔ በፊት ጀምሮ ነጋ ጠባ የትዳር ቀበኛና ጸር “Allergy “ (የፓስተሮች ቀማሽ ) ይመስል በበፊቱ ነውርና ስህተቷ ትምህርትም ሆነ ምክር ችግርና ግሳጼው ሁሉ መታረም ስገባት እንዴት እንደገና ለአግልግሎት በቃች ? ከኔ በፊት የነበራትን ትዳሯንም እንዲሁ በተመሳሳይ ተግባር ከሌላኛው ፓስተሯ ጋር በዝሙት ተጠርጥራ ትዳሯ እንደፈረሰ ከኔ በቀር ሁሉም የአከባቢያችን መንፈሳዊ መሪዎች የሚታውቁት የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው ። የራሷን ጽንስ (የኑሮ ጅምር ) አጨናግፋ (አኮላሽታ ) ፤ በተለያየ ጊዜና ወቅት ካገባቻቻው ባሎቿ መካከል አንዱንም እንኳ በአግባቡ ይዛ የራሷ ለማድረግ አቅቷት ሁሉንም በየተራ በየቦታው በአደባባይ እያፈረጠች ፤ እንደገና አዘናግታ ከሌሎች ተረኞች ጋር የምትከንፍ ያልሰከነች ሴት አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ስፍራና ቤተክርስቲያን ቀይራና ለዋውጣ አዳዲሶቹን መሪዎች ጥብቅ ብላ የቤተእምነቱን ቁልፍ እንዴት ተረከበቻቸው ?
ለማስመሰልና ለጉራ፤ ብሎም ለዝና ብሎም ለድብቅ ዓላማ ካልሆነ በስተቀር የራሱን ቤት ያቃተው ሰው የእግዚአብሔርን ቤት ለመጠበቅና ለማገልገል እንዴት ተገባው ? ለማጭበርበር ካልሆነ በቀር የራሱን ጽንስና ራዕይ ገሎ የሰው ቤት ሄዶ የሌላውን ልጅ ተንከባክቦ ለማስተማር ቀርቶ ጉንጭ እንኳን ለመሳም ሃላፊነት የሚጣልበት ስበእና አለው ለማለት አያስችልም ።እንዲህ ዓይነቱ ሰው ካለ ራዕይ ለመጠበቅ ከቶ አይቻለውም ፤ ምክንያቱም እውነተኛ አገልግሎትና ታማኝነት ከራስ ቤትና ትዳር መጀመር ስለምገባው ። እውነተኛዋ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካለች እንዲህ ዓይነቱን ዓይን ያዋጣ ድፍረትና ተራ ቁማር መዋጋት ተጋቢ ይመስለኛል ።
ምክንያቱም በኔ በኩል የችግሩ ሰለባ ከመሆኔም በላይ እንደ ባለ አዕምሮ ሳሰላስል እነዚህ እና ቢጤዎቻቸው ባለቤቱ የከደነውን ያለፈቃድ የሚከፍቱ ፤ አንዱ የገነባውን የሚንዱ ፤በፈጣሪ ስም ፤ በሃይማኖት ሰበብ ተገቢ ያልሆነን ተግባርን የሚሰሩ ፤ለማንም የማይራሩ ከስህተታቸው የማይማሩ ፤ የራሳቸውን ትተው የሰውን ሚስት ( ባል ) ለመቅመስ ሌት ተቀን የሚዞሩ ፤ ለከበረው ትዳርና ጤነኛ ፍቅር እንቅፋት ብቻ ሳይሆኑ ለሰሩት ጥፋትና ስህተት በንቀት ጆሮ ዳባ ብለው (ችላ ባይ ከመሆናቸው የተነሳ )ጉዳቴ ዕለት በዕለት ይበልጥ እየተሰማኝ ስለሆነ የሚወስነው ውሳኔ እየክፋ እንደመጣ ተገንዝቤያለሁ ።
በመሆኑም ስማቸው ከዚህ በላይ በተደጋጋሚ የጠቀስኳችው ግለሰቦች (ፓ/ር ዳዊትና ግብረ አበሩ ወ/ሮ ትግስት ) እንዲሁም ቢጤዎቻቸው በሰው ላይ በደልና ነውር እያደረሱ ፤የንጹሃንን ትዳር እያፈረሱ በእግዚአብሔር ቤትና በቅዱሳን መካከል መሽገው ፤ሃጥያታቸውን ሸሽገው ሚስኪኖችን አንገት እያስደፉ ፤ የሰላማዊ ኑሮን ጣዕምና ትርጉም እያጠፉ መላውን ቅድዱሳን በሃሜትና በአሉባልታ እያተራመሱ ቤተ-እምነቶችን መነጋገሪያ ፤ መሳለቂያ እያደረጉ መቀጠል ተገቢ አይደለምና ጉዳዩን ለህዝብ ሚዲያ እና ለመላው አብያተ-ክርስቲያናት ለማቅረብ ወደድኩ ።
አዎን ፤ በቃ ፤ የእግዚአብሔር ቤት ይህንን ከመሳሰለ የነውር ተግባር ከነዚህ ዓይነቶቹ አስመሳይ ነውረኞች ልጠራ ይገባል ፤እኔም ከእንግዲህ ጥፋተኛው ቅጣቱን እስኪቀበል ፤ ነውረኛው በነውሩ እስኪጸጸት ፤ እግዚአብሔርን ፤ ህዝቡንና ተበዳዩን ይቅርታ እስኪጠይቅ ፤ ቁስሌ እስኪጠገን ፤ህመሜ እስኪፈወስ ፤ ምናልባት ተመሳስለው እና ተደብቀው በየቦታው የተሸሸጉ ነውረኞች ካሉ ያጨለሙት
ተስፋዬ እስኪታደስ ፤ ሃላፊነት የጎደላቸው መንፈሳዊ ጀብደኞች ያኮላሹት ራዕዬ እስኪመለስ ፤ የጌታ ፈቃዱ ሆኖ በህይዎት እስካለሁ ይህንን ስድ አልለቀውም ።
ሌላው ቢቀር እንኳ የዚህን ጨዋ መሳዪ ተግባር ሰው ሁሉ ይስማውና ባላጌዎች ይፈሩበት ፤ ጥፋተኞች ይታረሙበት ፤ ትውልድ ይማርበት ፤ያፈለገው ንሰሃ ይግባበት ፤ዱሪዬዎች አደብ ይግዙበት ፤ ዝንጉዎች ይጠንቀቁበት ፤የተጎዳው አእምሮና መንፈሴ ይታደስበት ፤ እግዚአብሔር ይክበርበት ።
እንዲሁም ተመሳሳይ በደልና ግፍ በሰውር በቅዱሳን የግል ኑሮና ቤተሰብ ህይዎት ላይ እየተፈራረቀባቸው በአጓጉል ኋላ ቀርና በሃይማኖት ስም ማስፈራሪያነት ከደረሰባቸው በደልና ጥቃት ጋር ተሸማቀው “ታሪኬ ከበደለኝ ሰው ጋር አብሮ ከሚጋለጥ ጥቃቱን ተሸክሜ ፤የጎዱኝን ነውረኞች አበሳ ደብቄ ልኑር “ የሚሉት ሳይቀሩ ሌባውን ሌባ ፤ነውረኛውን ነውረኛ ፤ዋሾ አስመሳዩን ቀጣፊ ፤ወዘተ…እያሉ በድፍረት ተናግረው ለማጋለጥ ጉልበት ያግኙበት።
በሌላ በኩል ሰውዬው ( ፓ/ር ዳዊት ) ብልጣ-ብልጥ ፤ አስመሳይ ጮሌ ፤ ምላሱ ቅቤ ፤ልቡ ጩቤ ስለሆነ ፤የገነነ ዝና ፤ እውቅና ፤ ገንዘብና ብዙ ቢጤዎች ስላሉት ብቻ እኔው ተጠቅቼ ፤ፍትህ አጥቼ ፤ በቀሪ ዘመኔ ሁሉ ተቀጥቼ አልኖርምና ሃቀኛ ዳኛ ፤አመዛዛኝ ህሊና ፤ ከአድልዎ የጸዱ ፍትህን የሚያስከብሩ ፤ ለእግዚብሔርና ቤቱ የሚቆረቆሩ ፤ ህዝበ-እግዛብሔርን የሚያፈቅሩ፤ በጽድቅ የሚኖሩ ፤ለሚስኪኖች የሚከራከሩ ፤ነውረኛ ጥፋት ፈጻሚዎችን በድፍረት በመገሰጽ የሚመክሩ የሚያስተምሩ በፍቅር የሚገሩ ፤ ነውርንና እርኩሰትን የሚጸየፉ እውነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋይ ዳኞች አሁንም በአምላኬ ቤት ልኖሩ እንደሚችሉ እርግጠኛ በመሆን ይህንን ጉዳቴን ፤ አበሳዬንና ገበናዬን ዘርዝሬ አቅርቤያለሁ ።
ፓ/ር፡
ይህንንም ሳደርግ አንተ ብቻ ሳትሆን ሌሎች የእግዚአብሔር ሰዎች ፤ የጌታ አገልጋዮች ፤መንፈሳዊ መሪዎችና መላው ቅድሳን ሁሉ “ እኛ በቦታው አልነበርንም ፤ አልሰማንም ፤ አላየንምና አንዳች ነገር ከቶ አያገባንም” ወዘተ… እንዳይሉ ይህንን ደብዳቤና የከዚህ ቀደሞቹን ዝርዝር ጉዳዮች የያዙ ኮፒዎችን ሁሉም በያሉበት አድራሻ በተከታታይ የሚልክላቸው (የማሰራጭ ) መህኑን አልሸሽግም ።
ለዚህም ዋና ምክንያቴ ኪሳራዬ ባይካስም ፤ጉዳቴ ስብራቴ ባይጠገንም ፤ ቁጭት እልሄ በርዶ ቁስሌ ባይፈወስም ትዳሬን እንደሆነ እስከመጨረሻው ያጣሁ፤ የፈራረሰ እና ያከተመለት ፤ የሞተ ነገር ቢሆንም እኔ ተጎድቼ ፤ተዋርጄ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሌላው ትውልድ ዘላቂ መፍትሄና ያማያዳግም ትምህርት ያገኝበታል ብዬ በመገመት ነው ፤ አዎን ከተቻለ የኔ ትዳር ተኮላሽቶ ታሪኬም ተበላሽቶ ከእንግዲህ ግን የምስኪን ወገኖቼን ትዳርና ኑሮ ከሚያኮላሹና ከሚያበላሹ አገልጋይ ተብዬ መንፈሳዊ ዱሪየዎች ለመታደግ ነው።
ፓ/ር ፡ እጅግ በጣም የማከብርህ ትልቅ የእግዚአብሔር አገልጋይና መሪ ነህ ። ፓስተሬ እንደ መሆንህ መጠን በአከባቢዬ አንድ የእግዚአብሔር ሰው የሚለው እና የጉዳዬን ዝርዝር ታሪክ በቅርበት የሚያውቅ ካንተ የበለጠ ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ ማንም የለም ።
ከመነሻው እስከሁን ያለውን ታሪኬን ከሞላ-ጎደል ታውቀዋለህ ፤ በተለይም ጉዳቴን ፤ ስብራቴን ፤ሃዜኔና እንባዬን ፤ እንዲሁም ጥልቅ ቁጭቴን መገመት ከቶ አያቅትህም ብዬ አስባለሁ ። ስለሆነም ከዚህ ቀደም ከአንዴም ሁለቴ በኛ ጉዳይ እንባህን ስታፈስ ደጋግሜ አይቸሃለሁ ።በሌሎች ቅዱሳን ዘንድም ቢሆን የነዚህ ነውረኞች ነውርና ቀልድ ከማንም የተሰወረ አይደለም ፤ ያለንበት ወቅት ከምንጊዜውም በለይ በእርኩሰትና በክፋት የተሞላ ሆኗል ፤ ክህደት በመብዛቱ ቅጥፈት ነግሶ ዘመኑ እጅግ ከባድ ሆኖብናል ።
ስለዚህ እውነት ታፍኖ ሃቅ በመታነቁ ምክንያት ፍትህን አስከብሮ ለጽድቅ የሚፈርድ ዳኛ ይቅርና የቅርብ የሆነ ታማኝ ጓደኛ የታጣበት አስደንጋጭ ወቅት ላይ ደርሰናል። እኔ ያለእግዚአብሔር በቀር ሃብት ፤ ዘመድ፤ ወገንና ደጋፊ የለኝም ።
በዚህ ቁርጥና ፈታኝ ወሳኝ ወቅት አንተ ግን እንደ አባት ፤ የእምነት ሰው ፤ የቤተከርስቲያን መሪና የህዝብ አገልጋይ የመፍትሄ ምክርህ ፤ እገዛህ ፤ አስተያየትና ውሳኔህ ምንድን ነው ?
በተጨማሪም የተፈጸመብኝ በደል ፤ ግፍና ጥቃት ዘርዝሬ ከላይ በጠቀስኩት መሰረት ለሚዲያዎችም ጭምር ለማሰራጨት የወሰንኩ መሆኔን በክብሮት እየገለጽኩ ከፈጣሪዬና ካአንዲት ነፍሴ በቀር አንዳች ለሌለኝ ለኔ ለብቸኛውና ምስኪኑ ሰው አሁንም እንዲትጸልይልኝ ጭምር በጌታ አደራ እላለሁ ።
በጌታ እወደሃለህ
እጅግም አከብርሃለሁ
እግዚአብሔርና ቃሉ ብቻ እውነትና ትክክል ናቸው !
ከእንግዲህ በዘመኔ ሁሉ ማንንም አላምንም !!
እውነት ብትቀጥን እንጂ ጨርሳ ተበጥሳ አታውቅም !!!
ግርማ ዱሜሶ
Email; gelgela09@yahoo.com
ግልባጭ ፡
ለኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት በሙሉየእግዚአብሔር ቅዱሳን ሁሉ በያሉበትአበሻ ነክ ለሆኑ የኢትዮጵያዊያን ሚዲያዎችና ድህረ-ገጾች በሙሉ ።
Petros Ashenafi Kebede's photo.

Monday, May 25, 2015

መጥፎ የአፍ ጠረን እንዳለብዎ እንዴት ማወቅ ይችላሉ? መንስኤውና መፍትሔውስ?

በዓለማችን ላይ እጅግ በርካታ ሰዎች በመጥፎ የአፍ ጠረን የተነሳ ከፍተኛ መሳቀቅና መሸማቀቅ እንደሚደርስባቸው መረጃዎች የሚጠቁሙ ሲሆን የጉዳዩ አስገራሚ ገፅታ ደግሞ እነዚህ መጥፎ የአፍ ጠረን ያላቸው ሰዎች የገዛ የአፍ ጠረናቸው ችግር እንዳለበት ፈፅሞ አለማወቃቸው ነው፡፡ በሳይንሳዊ አጠራር “halitosis” ሃሊቶሲስ የሚሰኘው መጥፎ የአፍ ጠረን ሰዎች እንዲርቁን እና በራስ የመተማመናችንን እንድናጣ ከሚያደርጉ ችግሮች ዋነኛው ስለመሆኑ የተለያዩ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ በዛሬው የገመና አምዳችን መጥፎ የአፍ ጠረንን በተመለከተ ዝርዝር ፅሁፍ እናቀርባለን፡፡
መጥፎ የአፍ ጠረን ምንድን ነው?



መጥፎ የአፍ ጠረን በአፋችን፣ በምላሳችን ወይም በቶንሲላችን ውስጥ የሚኖሩ አንዳንድ ባክቴሪያዎች የሚፈጥሩት ውጤት ሲሆን እነዚህ ባክቴሪያዎችም በሁላችንም አፍ ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡ ባክቴሪያዎቹ በደህናው ጊዜ ምንም ሳይለወጡ ባሉበት ሁኔታ የሚዘልቁ ቢሆኑም የተለያዩ አካባቢያዊ
ምክንያቶች ግን እንዲለወጡ ሊያደርጓቸው ይችላሉ፡፡ በዚህ የተነሳም የሚያደርጉት ለውጥ የተለየዩ የኬሚካል ውሁዶችን እንዲያመነጩ የሚያስገድዳቸው ሲሆን የእነዚህ ኬሚካሎች ጠረንም ልክ እንደ ሃይድሮጅን ሰልፋይድ የሚከረፋ የበሰበሰ ዕንቁላል ሽታ የሚመስልና እና ሌሎችም አስቀያሚ ጠረኖችን ሊያመነጭ ይችላል፡፡

መጥፎ የአፍ ጠረን ምን ያስከትላል?

• የጥርስ (ድድ) እብጠት ወይም ቁስለት (Abscessed Tooth) ጥርሳችንን ከበው እና አቅፈው የሚገኙ የሰውነት ህዋሳት ቡድኖች (tissues) ላይ የሚፈጠር የቁስል መመርቀዝ (infection) እንደ መግል (pus) ያለ ፍፁም አስቀያሚ ጠረን ያለው ፈሳሽ እንዲፈጠርና የአፍ ጠረንን እንዲቀየር ያደርጋል፡፡

የመጥፎ አፍ ጠረን መንስኤዎች

•የአልኮል ሡሰኝነት (Alcoholism) ከልክ ያለፈ የአልኮል ተጠቃሚነት ዝቅተኛ መጠን ያለው የምራቅ መመንጨት እንዲከተልና አፍ እንዲደርቅ በተያያዥም የአፍ ጠረን እንዲበላሽ ያደርጋል፡፡ የአፍ ድርቀት ከሁሉ በተለየ ቀዳሚ የአፍ ጠረን መበላሸት ሰበብ ነው፡፡
• የአፍንጫ ውስጣዊ ቁስለት
ይህ የአፍንጫችን ንፍጥ አመንጪ አካል በጉንፋን የተነሳ በሚደርስበት ቁስለት የተነሳ በአፍንጫችን ለመተንፈስ እንዳንችል በሚያስገድድ ሁኔታ የሚደፈንበት ክስተት ሲሆን በዚህ ምክንያትም አየርን ደጋግመን በአፋችን የማስገባት ብሎም የማስወጣት አማራጭን እንድንከተል እንገደዳለን፡፡ ይህ ከላይ በተጠቀሰው የአፍ ድርቀት ሰበብ የአፍ ጠረን እንዲለወጥ ያደርጋል፡፡
• ነቀርሳ (cancer)
እንደ የጨጓራ ካንሰር፣ የአፍ ዕጢ፣ የነጭ ደም ሴል መብዛት እና ሌሎች መሰል በሽታዎች ባሉ ህመሞች የሚጠቁ ሰዎች ከፍተኛ የሆነ የመጥፎ የአፍ ጠረን ችግር የሚገጥማቸው ሲሆን የዚህ ምክንያቱ ደግሞ በሰውነት ውስጥ የሚካሄደው የመበስበስ ሂደት እንዲሁም ለበሽታዎቹ የሚሰጡት የህክምና አገልግሎቶች ናቸው፡፡
• የአፍ ቁስለት (Oral Candida)
ይህ በተለይም በህጻናት፣ በስኳር ህመምተኞች እና የኤች አይ ቪ ኤድስ ህመምተኞች ላይ የተለመደ እና በብዛት የሚከሰት ነው፡፡ ይህ አይነቱ በፈንገሶች የተነሳ የሚፈጠር የአፍ ቁስለት ሲሆን ይህም በቀላሉ የአፍ ጠረን እንዲበላሽ ምክንያት ይሆናል፡፡

• የጥርስ መገጣጠሚያ ክፍተቶች (Cavities)
በአንዱና በሌላኛው ጥርሳችን መሃከል ባሉ ክፍተቶች (Cavities) ውስጥ የተለያዩ ነገሮች የሚሰገሰጉና በየዕለቱ ያልተፀዱ እንደሆነም ተከማችተው ወደ ብስባሸነት በመለወጥ መጥፎ የአፍ ጠረንን ያስከትላሉ፡፡

• ሰው ሰራሽ ጥርስ (Dentures)
ሰው ሰራሽ ጥርስ የሚጠቀሙ ሰዎች ጥርሳቸውን እንደ ተፈጥሮ ጥርስ ሁሉ በነፃነት ለማፅዳት የማይችሉ በመሆኑ ጥርሳቸው እንዲቆሽሽና የአፍ ጠረናቸው እንዲበላሽ ይገደዳሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የሰው ሰራሽ ጥርስ ተጠቃሚዎች ተደጋጋሚ በሆነ የአፍ ድርቀት እንደሚቸገሩና ይህም ለአፍ ጠረናቸው መበላሸት ሌላ ተጠቃሽ ሰበብ እንደሆነ ይገለፃል፡፡

•የስኳር በሽታ (Diabetes)
የስኳር ህመምተኛ የሆኑ ሰዎች በመጥፎ የአፍ ጠረን ሊቸገሩ እንደሚችሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ የዚህ ምክንያት ደግሞ ህመምተኞቹ ሊቆጣጠሩት የሚገባቸውን የደማቸውን ግሉኮስ መጠን ለመቆጣጠር ሲሣናቸውና ሲያሻቅብ ነው፡፡ በዚህ የተነሳም የድድ ቁስለት እና የጥርስ ህመም የበርካታ የስኳር ህመመተኞች ችግር ሲሆን ይህም የአፍ ጠረናቸውን ሲያበላሽ ይስተዋላል፡፡

• ደካማ የጥርስ ንፅህና (Poor dental hygiene)

ከላይ የጠቀስናቸው እጅግ በርካታ የአፍ ጠረን መበላሸት ምክንያቶች ቢኖሩም አንዳቸውም ግን የደካማ የጥርስ ንፅህና አጠባበቅን ያሀል ለአፍ ጠረን መበላሸት ግዙፉን ድርሻ አይወስዱም፡፡ ጥርስን ዕለት በዕለት አለመከታተል አለመቦረሽ (አለመፋቅ) ለችግሩ በርን ወለል አድርጎ መክፈት እንደሆነ ጥናቶች ይጠቁሟሉ፡፡

• እርግዝና
በእርግጠኝነት ምክንያቱ ባይታወቅም በእርግዝና ወቅት የአፍ ጠረን ሊለወጥ እንደሚችል ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡
• ሲጋራ ማጤስ (Tobacco Smoking) ሲጋራ ማጤስ አፍን በማድረቅ የባክቴሪያዎችን ጦር በአፍ ውስጥ እንዲያድግና እንዲባዛ በማድረግ የአፍን ጠረን ከተወዳጅነት ወደ አናዳጅነት ይቀይራል፡፡ ለአፍ ጠረን መበላሸት የሚጠቀሱት መንስዔዎች ከላይ የተዘረዘሩት ብቻ አይደሉም፡፡ ሌሎችም ጥቂት የማይባሉ የችግሩ ምክንያቶች አሉ፡፡ የምክንያቱን ጉዳይ በዚሁ እንግታና ወደ ቀጣዩ ነጥብ እናምራ፡፡

መጥፎ የአፍ ጠረን መንስኤውና መፍትሄው ምንድነው?

የመጥፎ አፍ ጠረን መዘዞች ምን ምን ናቸው? በርካቶች ለዚህ ጥያቄ የሚሰጡት ምላሽ “ግለሰቡ የገዛ የአፍ ጠረኑን መበላሸት ማወቁና መሸማቀቁ ነዋ!” የሚል ነው፡፡ ጥናቶች በሚያሣዩት መሰረት ግን የአፍ ጠረናቸው የተበላሸ ሰዎች ስለ ገዛ የአፍ ጠረናቸው አንዳችም ነገር የማያውቁ እና እንዲያውም በአፍ ጠረናቸው የሚተማመኑ ናቸው፡፡ ከልምድ አንድ ሰው የገዛ አፍ ጠረኑን ለማወቅ መዳፎቹን ወደ አፉ በማስጠጋት እና ወደ መዳፎቹ ውስጥ በመተንፈስ ማሽተት እንደሚቻል ቢታመንም ጥናቶች ይህ ዋጋ የሌለው ሙከራ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ሰውነታችን በተፈጥሮ የገዛ ራሳችንን ጠረን የመላመድና የመዋሀድ ባህርይ ስላለው ነው፡፡ በዚህ የተነሳም ማንኛውም ሰው ስለ አፍ ጠረኑ ሁኔታ ለማወቅ ከፈለገ ውስጣዊ ሣይሆን ተከታዮቹ ውጪያዊ ምልክቶች ላይ ሊያተኩር ይገባል፡፡

– የአፍንጫ መደፈን ያጋጥምዎታል?
– የሰውነት መቆጣት (Allergy) ያስቸግሮታል? – ከፍተኛ የሆነ የአፍ ድርቀት ችግርያጋጥምዎታል?
-በአፍዎ ውስጥ የመምረር ስሜት ያጋጥምዎታል? ምላስዎት ላይ እንደ ቅባት ያለ ነገር ያገኛሉ?
– ጓደኞችዎት ማስቲካ እና ሚንት ከረሜላዎች ይሰጡዎታል?
– የተለያዩ ሰዎች እርስዎ በሚናሩበት ጊዜ አንገታቸውን ከእርሶ ዞር ያደርጋሉ?
እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ጥያቄዎች እጅግ መሰረታዊ የሆኑ ሲሆኑ ከጥያቄዎቹ ውስጥ ለብዙዎቹ የሰጡት ምላሽ “አዎ” ከሆነ የአፍ ጠረን ችግር ያለብዎ ለመሆኑ ከፍ ያለ ዕድል እንደሚኖር ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡

ለጥያቄዎቹ የሠጡት ምላሽ “አላውቅም” የሆነ እንደሁ ደግሞ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነገሮችን ልብ በማለት እና ለጥያቄዎቹ ተገቢውን ምላሽ በመስጠት የአፍ ጠረንዎ በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንዳለ ለማወቅ ይጣሩ፡፡ በዓለም ላይ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ከሆነ አንድን ሰው “አፍህ ጠረኑ ተበላሽቷል” ለማለት ወደኋላ የማትለው የገዛ እናቱ ብቻ ነች፡፡ በመሆኑም ከላይ የተዘረዘሩትን ጥያቄዎች መመለስ ከሰው እስኪመጣ ሣይጠብቁ የራስን እርምጃ ለመውሰድ ይረዳል፡፡ አንዳንድ ለየት ያሉ የአፍ ጠረኖች የበሽታ ምልክቶች እንደሆኑ በጉዳዩ ላይ የተደረጉ ጥናቶች ይገልፃሉ፡፡ የተወሰኑትን ለማየት ያህልም፡፡

የፍራፍሬ ሽታ ያለው የአፍ ጠረን ይህ በስኳር ህመምተኞች ላይ ሊከሰት የሚችል ሲሆን በሰውነታችን ውስጥ የኢንሱሊን እጥረት ሲኖርና ስብን ለመተካት ሰውነት ሲጥር የሚከሰት ለህይወትም አስጊ የሆነ ደረጃ ላይ የመገኘት ምልክት ሊሆን ይችላል፡፡ የአሣ ሽታ ያለው የአፍ ጠረን ይህ ዓይነት የአፍ ጠረን አደገኛ ከሆነ የኩላሊት ችግር (Chronic kidney failure) ጋር ሊያያዝ ይችላል፡፡
መጥፎ የአፍ ጠረንን እንዴት ማስወገድ ይቻላል በዚህ ፅሁፍ ለመጠቆም የሚሞከረው የመጥፎ አፍ ጠረን ማስወገጃ ዘዴ የአፍ ጠረን ችግሩ ከልክ አልፎ ስር ላልሰደደባቸውና በመሃከለኛ የችግሩ ደረጃ ላይ ለሚገኙት ብቻ ነው፡፡ በችግሩ ከዚህ በበለጠ የተጠቃ ማንኛውም ሰው የጥርስ ሃኪም ማማከርን ብቸኛ አማራጩ ሊያደርግ ይገባዋል፡፡ የአፍ መታጠቢያ ፈሳሽ (mouth wash) በርካቶች የአፍ ጠረናቸው መበላሸቱን እንዳወቁ የሚጠቀሙት ፈሳሽ ነው፡፡ በዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚገለፀው “mouth wash” በአፍ ውስጥ የሚገኙ ባክቴሪያዎችን የሚገድል እና ለአፍም መልካም ጠረንን የሚሰጥ ቢሆንም በአፍ ውስጥ ያሉ ባክቴሪያዎችን የሚገድለው ግን በውስጡ ያለው አልኮል ነው፡፡ በመሆኑም አልኮል አፍን የማድረቅ ባህርይ ስላለው ዳግም ለባክቴሪያዎች መፈጠርና ለችግሩ ይበልጡኑ ማገርሸት ቀላል ያልሆነ ሚናን ይጫወታል፡፡ በዚህ የተነሳም “የአፍ መታጠቢያ ፈሳሽን (mouth wash) አለመጠቀሙ ተመራጭ ነው፡፡ ፈሳሹን አብዝቶ መጠቀም የድድ መቆጣትንና የምላስ ቁስለትን በማስከተል የአፍ ጠረን መበላሸትን እንደሚያመጣም ይገለፃል፡፡ በመሆኑም የአፍ መታጠቢያ ፈሳሽ (mouth wash) ችግሩን ያጠፋን እየመሰለን እንዲያገረሽ ከማድረግ ውጪ ዘላቂ መፍትሄ ሊሆን እንደማይችል ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ከዚህ ይልቅም የቁንዶ በርበሬ ዘይትን፣ የዝንጅብል ዘይትን፣ የቅርንፉድ ዘይትን ሁለት ጠብታዎች በመጠነኛ ውሃ ቀላቅሎ ለአፍ መጉመጥመጫነት ማዋል ውጤታማ መሆኑ ይታመናል፡፡ ጨውን በውሃ ውስጥ በማሟሟት በውሀው መጉመጥመጥ ደግሞ ሌላው የመጥፎ አፍ ጠረን ማስወገጃ መንገድ ነው ይህ ካልተስማማዎት ደግሞ በጨው ፋንታ በውሃው ውስጥ ሎሚ አልያም ኮምጣጤ በመጨመር ተመሳሳይ ጥቅም ለማግኘት ይችላሉ፡፡

ማስቲካ ማኘክ የመጥፎ የአፍ ጠረንን ለማስወገድ አማራጭ አይሆንም፡፡ ማስቲካ ችግሩ እያለ ግን እንደሌለ ሸፋፍኖ ለማቆየት ካልሆነ በስተቀር ሌላ የሚፈይደው ነገር የለም፡፡ ጥናቶች እንደሚጠሙት ከሆነም አንድ በመጥፎ የአፍ ጠረን የሚቸገር ሰው ችግሩን ለማስወገድ ከማስቲካ ይልቅ ቅርንፉድ ቢያኝክ የተሻለ ውጤትን ሊያገኝ ይቻለዋል፡፡ ፓርስሊ የተሰኘውን የምግብ ማጣፈጫ ቅጠል ማኘክም የሚመከር መፍትሄ ነው፡፡ የጥርስን ንፅህና መጠበቅ ከሁሉ በላይ ወሣኝና ተመራጭ መፍትሄ ሲሆን አንድ ሰው ቢያንስ በቀን ሁለት ጊዜ ያህል ጥርሱን ማጽዳት ይኖርበታል፡፡ ጥርሱን በሚቦረሽበት ወቅት ድድን እንዲሁም ድብቅ የሆኑ የጥርስ ስፍራዎችን ጎን ለጎን ማጽዳት ይኖበታል፡፡ ከእያንዳንዱ ማዕድ በኋላ ጥርስን ማጽዳት በባለሙያዎች የሚመከር ሲሆን ይህን ማድረግ ባይቻል እንኳ በደንብ አድርጎ መጉመጥመጥ አስፈላጊ ነው፡፡ ብዙዎች የማያደርጉት ቢሆንም ምላስን በየቀኑ ማፅዳት (መቦረሽም) የሚመከር ተግባር ነው፡፡ የመጥፎ የአፍ ጠረናችን ዋነኛ መመንጫ የሆነው የምላሳችን የኋለኛው (ወደ ጉሮሯችን) አካባቢ ያለው ክፍል በመሆኑ እስከተቻለው ድረስ ይህን የምላሳችንን ኋለኛ ክፍል ለማፅዳት መሞከሩ ይመከራል፡፡

ሌላው መጥፎ የአፍ ጠረን ማስወገጃ ዘዴ “በተራቡበት ሰዓት ወዲያውኑ መመገብ” ነው፡፡ ምግብ በሆድ ውስጥ ከሌለ የምራቅ እጥረትና የአፍ ድርቀት የሚከሰቱ በመሆኑ ለአፍ ጠረን መቀየር ምክንያት ይሆናል፡፡ ሻይን መጠጣት መጥፎ የአፍ ጠረንን ለማስወገድ እንደሚረዳ በቅርቡ የወጡ ምርምሮች ይጠቁማሉ፡፡ “ፓሊፌኖልስ” (Polyphonies) የተሰኘው በሻይ ውስጥ የሚገኝ ኬሚካል በአፍ ውስጥ የሚገኙ ሰልፈር በማመንጨት የአፍ ጠረንን የሚያበላሹ ባክቴሪያዎችን በመከላከሉ ረገድ ላቅ ያለ ሚና እንዳለው ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ የወተት ውጤቶች በተለያዩ ሰዎች ላይ የተለያዩ የአፍ ጠረን ውጤቶችን እንደሚያስከትሉ የተለያዩ ምርምሮች የሚጠቁሙ ሲሆን አንድ በመጥፎ የአፍ ጠረን የተቸገረ ሰው ለአንድ ሳምንት ማንኛውንም የወተት ውጤት ሣይጠቀም በመቆየት ለውጥ ያገኘና መሻሻልን ያየ እንደሁ ደጋግሞ እንዲሞክር ይመከራል፡፡ በመጨረሻም አንድ የአፍ ጠረን ችግር ያለበት ሰው በምንም ዓይነት አፉ እንዲደርቅ ሊያደርግ አይገባም፡፡ ይህ የነበረው ችግር ክፉኛ እንዲባባስ የሚያደርግ በመሆኑ ግለሰቡ (ቧ) በርከት አድርጎ ውሃ መጠጣት የሚመከር ተግባር ነው፡፡

ምንጭ፡ ለውጥ ከተሰኘው መጽሔት ላይ በአቶ በረታ ወርቁ ማሞ የተጻፈ

Saturday, May 23, 2015

ቀይ ሽንኩርት ከምግብ በተጨማሪ ጤናንም ያጣፍጣል


ከአስምረት ብስራት በየእለቱ የምግባችን ማጣፈጫ ዋነኛ ግብአት አድርገን የምንጠቀመው ቀይ ሽንኩርትን ነው። ታዲያ አብዝተን የምንጠቀመውን ቀይ ሽንኩርት አብስለን ከመመገብ ይልቅ በጥሬው መጠቀም ለጤና እጅግ ጠቃሚ እንደሆነ ያስነብበናል ከጎግል ድረገፅ ያገኘነው መረጃ፡፡ በቀይ ሽንኩርት ውስጥ የምናገኛቸው ክዩርስቲን፣ አላሲን፣ ክሩሚየም የተባሉት ንጥረ ነገሮች ካንሰርን በመዋጋት ወደር የላቸውም። ይህ አትክልት ፈንገስንና ባክቴሪያንም ይከላከላል፡፡ ኢንሱሊንን በመቆጣጠር ከስኳር በሽታ እንደሚታደግ ፣ የደም ግፊትን እንደሚቆጣጠርና ክብደትን ለመቀነስም ጥሩ አማራጭ እንደሆነ ነው መረጃው ያስቀመጠው፡፡
ቀይ ሽንኩርት የሆድ ውስጥ ካንሰርን እንደሚከላከል የደረሱበት አጥኚዎቹ በቀን ግማሽ ቀይ ሽንኩርትን በጥሬው መመገብ በሆድ ውስጥ ካንሰር የመጠቃት እድልን ሃምሳ በመቶ ይቀንሳል ይላሉ።

በቀይ ሽንኩርት ውስጥ የምናገኘው አላሲን የተባለው ንጥረነገር የመተንፈሻ አካል ጤንነትን በመጠበቅ፤ካንሰርን የመከላከልና ህመሙንም የመቆጣጠር፤ከፍተኛ የደም ግፊትን መቆጣጠር ዋንኛ ተግባሩ ሲሆን፤ በተጨማሪም ፈንገስን በመከላከል ከፎረፎርና ቆዳ ላይ ከሚወጡ ጭርት መሰል ነገሮች ይጠብቃል።
 ከቀይ ሽንኩርት የምናገኛቸው ስምንት የጤና ገፀ በረከቶች ብሎ ድረገፁ ያስቀመጣቸውን ስንመለከት በጭማቂ መልክ፣ከሰላጣና ከሌሎች በጥሬያቸው ከሚበሉ ምግቦች ጋር በመቀላቀል መመገብ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው። -
1. ቀይ ሽንኩርት በውስጡ በያዘው የቫይታሚን ሲ ይዘት የሰውነትን ከበሽታ የመከላከል አቅም ያሳድጋል።
2. በውስጡ ክሩሚየም የተባለ ንጥረነገር አለው። ይህ ንጥረነገር የደም ግፊትንና ስኳርን ይቆጣጠራል።
 3. ቀይ ሽንኩርት ገላን የማሳከክና የማቃጠል አይነት ባህሪ ያላቸውን አለርጂዎች ይቆጣጠራል
4. ቀይ ሽንኩርት ጥሬውን መመገብ ኮሊስትሮንን ከመቆጣጠሩ ባሻገር የጤናማ ልብ ባለቤት ያደርጋል።
 5. ክዩርስቲን የተባለው በቀይ ሽንኩርት ውስጥ የምናገኘው ንጥረነገር ካንሰርን የመከላከል ሚና አለው።
6. በንብ በምንነደፍበት ጊዜ ትንሽ የቀይ ሽንኩርት ውሃ ብንቀባ ከስቃዩ እፎይታን እናገኛለን
 7. ቀይ ሽንኩርት በየእለቱ መጠቀም ከጨጓራ አልሰር ይጠብቃል።
8. አረንጓዴ ጫፍ ያለው ለጋ ቀይ ሽንኩርት የቫይታሚን ኤ ይዘቱ ከፍተኛ በመሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው። -

Friday, May 22, 2015

Talk to Al Jazeera - Hailemariam Desalegn: Democracy 'not only an election'

የተሰነጣጠቀ ተረከዝን እንዴት በቀላሉ ማስወገድ እንችላለን? - ማጋራት ደግነት ነው Sharing is caring!



ወይ ማወቅ ደጉ: የጤና አምድ
የተሰነጣጠቀ ተረከዝን እንዴት በቀላሉ ማስወገድ እንችላለን?
(ጤናማ ውበት በቤታችን)
1. ሎሚ glycerin እና ጨው
• ሞቅ ባለ ዉሃ በጥቂቱ የሎሚ ጭማቂ :glycerin: እና ጨው: ከጨመሩ በኃላ እግርን ከ 15-20 ደቂቃ ማቆየት::
• pumice stone ወይም foot scrubber በመጠቀም ቀስ አድርጎ መፈግፈግ::
• 1 ማንኪያ glycerin እና 1 ማንኪያ የሎሚ ጭማቂ በመቀላቀል ተረከዝን መቀባት:: ከዚያ ካልስ አድርጎ መተኛት::
• ጥዋት በሙቅ ዉሃ በደንብ መታጠብ
• ይሄን በየቀኑ ተረከዝ ለስላሳ እስኪሆን መደጋገም::
2. የአትክልት ዘይት
• እግርን ከታጠቡ በኃላ በደንብ ማድረቅ::
• የአትክልት ዘይት ተረከዝን መቀባት:: ከዚያ ካልስ አድርጎ መተኛት::
• ጥዋት በሙቅ ዉሃ በደንብ መታጠብ
• ይሄን በየቀኑ ተረከዝ ለስላሳ እስኪሆን መደጋገም::
3. ሙዝ
• የሙዝ ልጣጭ በመጠቀም የተሰነጣጠቀውን ተረቀዝ መቀባት::
• ከአስር ደቂቃ በኃላ መታጠብ
4. ቫዝሊን እና የሎሚ ጭማቂ
• እግርን ከታጠቡ በኃላ በደንብ ማድረቅ::
• እግርን ለ 15-20 ደቂቃ መዘፍዘፍ::
• 1 ማንኪያቫዝሊን እና 1 ማንኪያ የሎሚ ጭማቂ በመቀላቀል ተረከዝን መቀባት::
• ከዚያ ካልስ አድርጎ መተኛት:: (የሚጠቀሙት ካልስ cotten ቢሆን የመራጭ ነው )
• ጥዋት በሙቅ ዉሃ በደንብ መታጠብ
• ይሄን በየቀኑ ተረከዝ ለስላሳ እስኪሆን መደጋገም::
5. ማር
ማር ከማለስልስ በተጨማሪ ፅረ-ባክቴሪያ ጠቀሜታ አለው (ስለ ማር ጠቀሜታዎች ከዚህ በፊት ያካፈልነዉን መመልከት ይችላሉ)
• የተዎሰነ ማር ሞቅ ካለ ዉሃ ጋር መቀላቀል
• እግርን ለ 15-20 ደቂቃ መዘፍዘፍ::
• ቀስ አድርጎ መፈግፈግ::
ጤናዎ ይብዛልዎት!
ማጋራት ደግነት ነው
Sharing is caring!

Monday, May 18, 2015

My wife is model in my heart – Adams Oshiomhole

The Edo State Governor, Adams Oshiomhole, has described his new wife, Iara, as a model in his heart even as he said his new wife is not a replacement for his late wife, Clara, whom he said is irreplaceable.Speaking at a Thanksgiving Mass held at the Immaculate Conception Cathedral, Auchi, on Sunday, Mr. Oshiomhole debunked reports that his wife is a ‘top model’ saying the speculation might have been generated from her poise and beauty.
He said, “When I read newspaper stories and they say that Comrade has married a ‘top model’ I’m like maybe it’s another person.
“The lady that God has directed to my path and heart to marry is not and was not a model. Of course, she looks beautiful and I understand that is why people assume that this kind of a lady must be a model but of course, she is a model in my heart and we hope and pray that we will be models in the heart of our God and I think that is the most important thing”.
Governor Oshiomhole appealed to the congregation to keep supporting him and his new wife in prayer saying “I ask you to please continue to pray for us. It is not easy. I lost my first wife and it is not possible to replace her. Yes, I have married another but it is not a replacement. You cannot replace a wife especially one you married when you were young and you were anonymous. Nobody knew you from anywhere, you had nothing, no car, no house; now, that you can never replace. But I understand that under the Catholic doctrine I am entitled to have another wife which is what I am trying to do.
“Thank you for your prayers, support and blessings that you have always showered on me and the one you conveyed this morning on me and my new wife and we ask for more and more prayers that this marriage will be my last and that God will help us, to unite us and bond us together with the blood of Jesus”, he prayed.
In a homily entitled, “Communicate the truth in Christ”, the Parish Priest of the Immaculate Concpetion Cathedral, Auchi, Valentine Anavbeokhai, urged Christians to eschew misrepresenting or twisting the truth in their daily communication saying we all have a duty and obligation to speak the truth, live the truth and if the need arises, to die for the truth.
He also used the opportunity to congratulate the governor and his new wife on their marriage and prayed for God’s peace and blessing on them.
The Thanksgiving mass was attended by the governor’s children, Steve, Jane and Adams (Jnr), the parents of his wife, Mr and Mrs Jesus Fortes, government functionaries, and well wishers.
oshomole