Search

Monday, September 23, 2013

የኬኒያ የፀጥታ ሀይሎች በዌስትጌት ታጋቾችን ለማስለቀቅ ዘመቻ ጀምሩ

ኬኒያ  መዲና ናይሮቢ የፀጥታ ሀይሎች በዌስትጌትየገበያ ማዕከል ውስጥ በአሸባሪ ቡድኑ አልሸባብ ታጣቂዎች ተይዘው የሚገኙ  ታጋቾችን ለማስለቀቅ ዘመቻ ጀምሩ ።
በአሁኑ  ወቅት  የፀጥታ ሀይሎቹ የገበያ ማእከሉን  የወረሩ ሲሆን ፥  ከስፍራውም የተኩስ ድምፅ  እየተሰማ ነው ።
ከ10 እስከ 15 የሚጠጉ የአልሸባብ ታጣቂዎች እስካሁን ከገበያ ማዕከሉ እስካሁን እንዳሉ ነው የተመለከተው።
ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ ጥቃት ፈፃሚዎቹን መንግስታቸው የገቡበት ገብቶ እንደሚይዛቸው ተናግረዋል።
አል ሸባብ  ለጥቃቱ  ሀላፊነቱን እንደሚወስድ አስታውቋል ።
ከከተማዋ  እየወጡ ያሉ ዘገባዎች  እንደሚያመለክቱት  እስካሁን  በሽብር ጥቃቱ 69 ዘጠኝ ሰዎች ተገድለዋል ።

በሶማሊያ  የሚገኘው የኬንያ ወታደራዊ ሀይል ጥቃትን ተከትሎ አልሸባብ በኬንያ ጥቃት ሊያደርስ እንደሚችል ለቢቢሲ መናገሩንም ዘገባው  አስታውሷል።
በደቡብ ሶማሊያ እ.እ.አ ከ2011 ጀምሮ አሸባሪውን አልሸባብ ለመታገል ከ4000 የማያንሱ የኬንያ ወታደራዊ ሀይል አባላት መሰማራታቸውንም ዘገባው አስታውሷል።

No comments:

Post a Comment