Search

Wednesday, May 22, 2013

ለ 40 ቀን 40 ለሊት እንጾማለን ብለው ሚስትን ለሞት ዳረጉ ልጆቹም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል

ያለምንም እህል እና ውሃ ጾምን ለ 40 ቀን 40 ለሊት እንጾማለን ብለው ጾማቸውን የጀመሩት የቤተሰብ አባላት ለከፍተኛ ጉዳት እና ለሞት መዳረጋቸውን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።
በጎተራ ኮንደሚኒየም ውስጥ ይኖሩ የነበሩት እነዚህ ሰዎች በሃገራችን እምነት አንጻር ጾም ጸሎትን እያደረግን አምላክን በጸሎት እናስባለን በማለት ጾማቸውን መጀመራቸው ተገልጾአል ።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ ያለው ባል እና ከጂማ ዩኒቨርሲቲ በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቀች ሲሆን ።

ባል በባህርዳር በክሊኒክ ይሰራ የነበር ሲሆን ሚስትም በዚሁ የሙያ ስራ ተሰማርታ ወደ  ባህርዳር ማቅናቷ እና የልጆቿን አባት በፍቅር ግንኙነት ጀምራ ወደ ትዳር አለም አብራው እንደዘለቀች እና ሁለት ልጆችን አፍርተው የ9 አመት እና የስድስት አመት ልጆችንም ማፍራታቸው  የሪፖርተራችን ያጠናቅራል ።

ከምግብ እና ከውሃ ተለይተው ለልጆቻቸው ብቻ በጣም ጥቂት ምግብን በመያዝ በቤታቸው ዘግተው ለቀናቶች ሰንብተዋል ።

ሂደቱ ለ25 ቀናት የተጓዘ ሲሆን ባለቤቷ እያበሰለ ለልጆቹ ከሚያቀርበው ምግብ ለራሱ በጥቂቱ የሚቀምስ ሲሆን ለባለቤቱ ሲሰጣት ግን ምንም አይነት ነገር መመገብ አለመቻሏን እና ምንም አያገባህም በማለት ምላሽ ታክል እንደነበር ዘገባው ያመለክታ.

ሆኖም ግን 40ኛ ቀኑ ከመድረሱ አራት ቀን በፊት የእናት የአፍጠረን መለወጥ ያየችው ህጻን ከወላጅ እናቷ ተለይታ  ከታናሽ እህቷ ጋር በሶፋ ላይ መተኛት መጀመሯን እና ከዚያም በመስኮት እራበን ድረሱልን እያለች መጮኋን እና የጎረቤት ልጅ መጥታ በበር ቀዳዳ በተሰጣት ቁልፍ ከፍታ በመግባት ፣ሁለቱ ህጻናቶች ቆዳቸው ተጣብቆ በምግብ ጉዳት ምክንያት ከስተው የተገኙ ሲሆን ባል እራሳቸውን በመሳት በሆስፒታል በህክምና ክትትል ላይ ናቸው ሚስትዬዋ ግን በህይወት ሊተርፉ አለመቻላቸውን ዘገባው አክሎ ጠቁሞአል.

 

No comments:

Post a Comment