Search

Thursday, May 16, 2013

በረከት በቀለ (ፍልፍሉ) ጨምሮ 12 ኮሜዲያኖች ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው

በረከት በቀለ (ፍልፍሉ) ጨምሮ 12 ኮሜዲያኖች ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው ።
እያንጓለለ በሚለው አዲሱ የኮሜዲ(ቀልድ)ስራቸው ክስ የተመሰረተባቸው 13 ኮሜዲያን በመጭው ማክሰኞ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ።አሳቡዮገዳ የሚባል የእምነት ተቋም ውስጥ ክስ የተመሰረተባቸው በረከት በቀለ (ፍልፍሉ) ተመስገን ተመላኩ ፣ጥላሁን እልፍነህ ፣ዋነሶች ፣ሙሉ ቀን ተሾመ (የቴዎድሮስ ተሾመ ታናሽ ወንድም)እና ሌሎችም የሚገኙበት ክስ ነው ።ኮሜዲያኑ የተከሰሱት እያንጓለለ በሚለው አዲስ የፊልም አልበማቸው ላይ የአሳቡዩገዳ የእምነት ተቋምን የዝሙት ማካሄጃ አስመስለው አቅርበዋል በሚል እና የእምነት ተቋሙ አምልኮቱ ይጠቀምባቸዋል የሚላቸውን ስኒ ፣ጀበና፣ ማጨሻ በሚያጣጥል እና በሚያናንቅ መልኩ ተጠቅመውበታል በሚል ነው ክሱ የተመሰረተው።

ኮሜዲያኖቹ የፍርድቤት መጥሪያ የደረሳቸው ሲሆን የፊታችን ማክሰኞ ፍርድቤት ቀርበው ክሱ ጉዳያቸውን የሚታይበትን ሂደን ለመከታተል ነው።በዚህ በጉዳዩ ዙሪያ ያናገርነው እና በሰሜን አሜሪካ ለተወሰነ ጊዜያት ኑሮውን ያደረገው በረከት በቀለ ፍልፍሉ እንደገለጸው ከሆነ የክሱ ሂደትም ሆነ ሁኔታው እሱን እና ጓደኞቹን ያስገረመ ከመሆኑም በላይ ለጉዳዩ ምንም ጥልቀት እውቀት እንደሌለው እና የቀልድ ስራውን ሰርቶ ከሃገር ለስራ ግዳይ መውጣቱን ለማለዳ ታይምስ ዝግጅት ክፍል በስልክ ባደረገው መግለጫ ተናግሮአል። እኛ የማንኛውንም የእምነት ተቋም አንነቅፍም ነገር ግን መቀለድ ማለት ሆኖ መገኘት አይደለም እና ህረተሰብን ለማስደሰት እና ለማዝናናት ስንል የምንሰራቸው ቁምነገር እና ፌዞች ከክፉ ነገር ጋር ተያይዘው ሊቀርቡ የሚታዩ ሊሆን አይገባም ሲል ጠቅሶአል:

No comments:

Post a Comment