Search

Monday, May 20, 2013

ቅዳሜ ኢትዮጵያ ከ ሱዳን ጋር ለምታደርገው ጨዋታ የተጫዋቾች ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ
ግንቦት 12 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ አፍሪካ ህብረት የተመሰረተበትን 50 ኛ አመት  ክብረ በአል ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያ ከሱዳን በምታደርገው ጨዋታ ላይ የሚካፈሉ ተጫዋቾችን ስም ዝርዝር የኢትዮጵያ  ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ይፋ አደረጉ ፡፡
በዚህም መሰረት የተመረጡት ተጫዋቾች ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ደጉ ደበበ ፣አበባው ቡጣቆ፣ቢያድግልኝ ኤልያስ፣አሉላ ግርማ፣ሽመልስ በቀለ ፣አዳነ ግርማ ፣ያሬድ ዝናቡ፣ዮናታን ብርሀነና ተስፋዬ አለባቸው ናቸው ፡፡
ከ ደደቢት ሲሳይ ባንጫ ፣ ስዩም ተስፋዬ ፣ብርሃኑ ቦጋለ፣አይናለም ሃይሉ፣አክሊሉ አየነው ፣አዲስ ህንጻ፣በሃይሉ አሰፋ ፣ጌታነህ ከበደ ፣ምን ያህል ተሾመ ፣ዘነበ ከበደ(አዩካ) ና ዳዊት ፍቃዱ ሲሆኑ ፥
ከ ኢትዮጵያ ቡና ጀማል ጣሰው፣አስቻለው ግርማ ፣ፖክ ጅምስ እና ኤፍሬም አሻሞ፥
ከ መብራት ሃይል አስራት መገርሳ እና መስፍን ወንድሙ፥
ከ መከላከያ ጥላሁን ወልዴ ፥
ከ ኢትዮጵያ መድህን ሳለሃዲን ባርጌቾ፥
ከ ሀዋሳ ከነማ ወንድሜነህ ዘሪሁን፥
ከ ሰበታ ከነማ ደረጀ አለሙ እና ከ ሲዳማ ቡና ደግሞ ሞገስ ታደሰ  ሆነዋል ፡፡
ተጫዋቾቹ ከነገው ግንቦት 13 ማለዳ ጀምሮ በ ፌዴሬሽኑ ጽህፈት ቤት ተገኝተው ሪፖርት እንዲያደርጉም  አሰልጣኙ ጥሪያቸውን አስተላለፈዋል፡፡

No comments:

Post a Comment