Search

Saturday, March 28, 2015

የኢትዮጵያን ተገኘው ጋዝ ክምችት ሀገራችንን በአለም ቁጥር አንድ የተፈጥሮ ጋዝክምችት ያላት ሀገር አድርጓታል

አለም የተፈጥሮ ዘይት ክምችት ታሪክ እስከዛሬ ሩሲያ ላይ
የሚደርስ ሀገር የለም ነበር ሩሲያ 47 ትሪሊዮን 700
ቢሊየን ኪውቢክ ሜትር የሚሆን የተፈጥሮ ዘይት ክምችት
በመያዝ ነበር የአለምን ሪከርድ ተቆጣጥራ የኖረችው ዛሬ
ይህን ቦታ በብዙ ኪውቢክ ሜትር ልዩነት ሀገራችን
ተቆጣጥራዋለች ፣ ይህ በአርባ ምንጭ የተገኘው ጋዝ
ክምችት ሀገራችንን በአለም ቁጥር አንድ የተፈጥሮ ጋዝ
ክምችት ያላት ሀገር አድርጓታል ።
*የጁቡቲ መንግስት በበኩሉ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ጋዝ
ለማከማቸት፣ለማጣራት እና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ በ2
ነጥብ 6 ቢሊዮን ዳላር አዳዲስ ተርሚናሎች እየገነባ ነው።
*ጅቡቲ በዓመት ቢያንስ 10 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተፈጥሮ
ጋዝ ከኢትዮጵያ ወደ ቻይና ለመላክ እየተሰናዳች መሆኑም
ተጠቁሟል።
*በዚሁም መሰረት ከአርባ ምንጭ ወደ ጅቡቲ የ1ሺ 231
ኪሎ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቱቦ ዝርጋታ
ሊጀመር ነው::
ከአርባ ምንጭ ወደ ጅቡቲ የ1ሺ 231 ኪሎ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቱቦ ዝርጋታ ሊጀመር መሆኑ ተሰማ…
የሚዘረጋው የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ከአርባምንጭ ተነስቶ በአዋሳ በድሬዳዋ አድርጎ በመጨረሻም ጁቡቲ ወደብ እንደሚደርስ ታውቋል። ይህን ስራ ለማስጀመር የሚስችል ፈንድ መገኘቱን እንዲሁም በኢትዮጵያ መንግስትና በጅቡቲ መካከል የስምምነት ውል መፈረሙንም የዘገበው ሰንደቅ ጋዜጣ ነው፡፡
በአርባምንጭ የተገኘው የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት በዓለም ከፍተኛ ክምችት ካላት ሩሲያ የሚበልጥ መሆኑ ተገልጿል።
በአርባ ምንጭ የተገኘው የጋዝ ክምችት አዋጭነቱ ከካሉብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ጋር ፈጽሞ የማይገናኝና ለአበዳሪ ሀገራትም ከፍተኛ የሆነ መተማመን የፈጠረ በመሆኑ ለቱቦው ዝርጋታ ፈንድ እንዲለቀቅ አስችሏል።
ኢትዮጵያም በዓለም ደረጃ ቁጥር አንድ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ባለቤት የሚያደርጋት ከመሆኑም በላይ በቀጣይ በኢኮኖሚዋ ላይ አይነተኛ ድርሻ ይኖረዋል ሲል ጽፏል ጋዜጣው፡፡
የጁቡቲ መንግስት በበኩሉ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ጋዝ ለማከማቸት፣ ለማጣራት እና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ በ2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዳላር አዳዲስ ተርሚናሎች እየገነባ ነው። ጅቡቲ በዓመት ቢያንስ 10 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝ ከኢትዮጵያ ወደ ቻይና ለመላክ እየተሰናዳች መሆኑም ተጠቁሟል።
የአርባምንጩን የተፈጥሮ ጋዝ እያለማ የሚገኘው አፍሪካ ኦይል ኮርፖሬሽን የተባለ የካናዳ ኩባንያ ነው። ኩባንያው በነዳጅና በተፈጥሮ ጋዝ ፍለጋና ማምረት ላይ የተሰማራ ሲሆን፤ በአሁኑ ሰዓት ኩባንያው በኬኒያ፣ በኢትዮጵያ እና በፑንትላንድ ሥራዎቹን እያከናወነ ይገኛል..

8 comments:

  1. lela maregagecha minch ale?

    ReplyDelete
    Replies
    1. huhu sakiche motkugn alech alu eritrea!

      Delete
    2. No confirmation. It might be illusion or dream. I believe only if this report is posted by Africa Oil Corp.

      Delete
  2. Source EBC mehon alebet !!!

    ReplyDelete
  3. Total bullshit !!! check this http://www.africaoilcorp.com/s/current-activities.asp

    ReplyDelete
  4. ALE GENA MINU TENEKANA

    ReplyDelete
  5. Ayiiiiiiiiiii on so many levels

    ReplyDelete