Search

Showing posts with label Sports. Show all posts
Showing posts with label Sports. Show all posts

Friday, June 21, 2013

በምንያህል ተሾመ ጉዳይ ለህዝብ ይፋ ያልሆነው ምስጢር!!

በቀጣዩ ዓመት በብራዚል በሚደረገው የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ምድብ ማጣሪያ በምድብ አራት የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ባለፈው እሁድ አምስተኛ የምድብ ጨዋታውን በአዲስ አበባ ደቡብ አፍሪካን በማሸነፍ ለመጨረሻው ዙር ውድድር ማለፉን ቢያረጋግጥም በተጨዋችነት ተገቢነት ጉዳይ በእጁ የገባውን ዕድል መልሶ ማጣቱን የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ አረጋግጠዋል። ‹‹ስህተት ፈፅመናል›› ሲሉም ተናግረዋል። የብሄራዊ ቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ከሜዳ ውጪ ከቦትስዋና ጋር በሜዳችን ላይ በተደረገ ጨዋታ ሁለት ቢጫ ካርድ በማየቱ ምክንያት ከቦትስዋና ጋር በተደረገ የመልስ ጨዋታ ማረፍ ሲገባው ተሰልፎ በመጫወቱ ብሄራዊ ቡድኑ በእጁ የገባውን ዕድል መልሶ ሊያጣ መቻሉን አቶ ሳህሉ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት አስረድተዋል። በፊፋ ህግ አንድ ተጨዋች ሁለት ቢጫ ካርድ ከተመለከተ አንድ ጨዋታ ማረፍ ይኖርበታል። ይህን ደግሞ የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተከታትሎ ማስፈፀም አለበት፡፡ ፊፋ በተለያዩ ምክንያቶች ሳይልክ ቢቀር እንኳን አላሳወክም ተብሎ ሊጠየቅ አይችልም።

ይህም ሆኖ ግን ፊፋ ከቦትስዋናው ጨዋታ 14 ቀን ቀደም ብሎ ምንያህል በቅጣት መሰለፍ እንደሌለበት ለፌዴሬሽኑ አስታውቋል። ባለፈው ረቡዕ ደግሞ መከራከሪያ ነጥብ ካላችሁ በማለት ጉዳዩን በድጋሚ ለማየት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ይሁን እንጂ ፌዴሬሽኑ የመከራከሪያ ነጥብ በማጣቱ ዝምታን መርጧል፡፡ በፊፋ ህግ ለጥያቄው በሁለት ቀን ውስጥ ምላሽ ካልተሰጠ ቅጣቱ ትክክል እንደሆነ ተቆጥሮ ለተጋጣሚው ቡድን ፎርፌ ይሰጣል። በዚህ ህግና ስርዓት መሰረትም ኢትዮጵያ ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ የመጨረሻውን የምድብ ጨዋታ ውጤት መጠበቅ ግድ ሆኖባታል፡፡ ኢትዮጵያ አሁንም ከምድቡ ለማለፍ የተሻለው ዕድል አላት። ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በመረጃ ልውውጥ ችግር ምክንያት ስህተት ሊፈፀም እንደቻለና ለዚህም የቡድን መሪው አቶ ብርሃኑ ከበደ፤አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻውና የአሰልጣኝ ቡድኑ፤ምንያህል ተሾመና አቶ አሸናፊ እጅጉ በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ ቢጫና ቀይ ካርድን ተከታትሎ የማስፈፀምና የማሳወቅ ሀላፊነት ግን የማን እንደሆነ በግልፅ አልተገለፀም። በዋናነት ትኩረት ተሰጥቶት ሲነገር የነበረው ከፊፋ የተላከው መረጃ መድረስ ላለበት አካል ደርሷል አልደረሰም ነው። በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሁሉም ሃላፊነቴን ተወጥቻለው ከማለት ውጪ ችግሩ የእኔ ነው የሚል ወገን ግን አልተገኘም። በዚህም ምክንያት ፌዴሬሽኑ ጉዳዩን ይበልጥ አጠናክሮ በመመርመር በቅርቡ የቅጣት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አስታውቋል። በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ምንያህል ሁለት ቢጫ ለማየቱ መረጋገጫ ሆኖ የቀረበው ከፊፋ የተላከው መረጃ ብቻ ነው። ከኢትዮጵያ ወገን የቀረበ ወይም የተያዘ ምንም መረጃ የለም። እንደ ፊፋ ሁሉ የብሄራዊ ቡድኑ የአሰልጣኝ ቡድን ለፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ወይም ቴክኒክ ክፍል ቢጫና ቀይን በተመለከተ መረጃ ሊሰጥ ቢገባም አልሰጠም። ዋና መረጃ ሊሆን ይገባ የነበረውም ይህ የአሰልጣኝ ቡድኑ የሚያቀርበው መረጃ ነው። ይህ መረጃ ተይዞ ቢሆን ኖሮ ይህ ሁሉ ችግርና ውዝግብ ባልተፈጠረ ነበር። የመረጃ ልውውጡ ባህልና ስርዓት እንዲሁም የጋራ ተጠያቂነቱ ስለሚኖር ምንያህልን በቦትስዋና ጨዋታ ለማሳረፍ የፊፋን ደብዳቤ ባልጠበቅን ነበር፡፡ ቀድሞውኑ መረጃው ስለሚኖር ሰጥተኸኛል አልሰጠኸኝም የሚል ክርክር ባልተነሳ ነበር። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች ሁሌም ቢጫ ለማየታቸው እንደማረጋገጫ እየተደረገ ሲያዝ የነበረው ከፊፋ የሚላከው ደብዳቤ ነው። ግን ስህተት ነው፡፡ ፊፋ ዕሮብ ዕለት ለፌዴሬሽኑ የመከራከሪያ ነጥብ ካላችሁ በማለት ደብዳቤ የላከው ሀገሮች የራሳቸውን ቢጫና ቀይ ካርድ የመያዝ ሃላፊነትና ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ ምናልባት የዕለቱ ዳኛ እና ኮሚሽነር ሪፖርት ሲያደርጉ ቁጥር ወይም ስም ተሳስተው ከሆነ በሚል ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት ለማጣራት ነው። እዚህ ጋር ነገሩን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ዘንድሮ በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ቡና ክለብ ላይ የተከሰተውን እናንሳ ፌዴሬሽኑ የ1ኛ ዙር መጠናቀቅን አስመልክቶ በተደረገ ግምገማ ወቅት እያንዳንዱ ክለብ የተመለከተውን ቢጫ ካርድ ለየክለቦቹ ሰጠ በዚህ ሰነድ ላይ የቡናው ሲሳይ ደምሴ የተመለከተው ሦስት ቢጫ ነው ይላል የቡድኑ አሰልጣኞች የያዙት ደግሞ አራት ቢጫ ይላል ክለቡ ፅህፈት ቤት ጋር ያለው ሰነድ ጋር ሲጣራ ደግሞ በርግጥም አራት ቢጫ ሆነ እናም በቀጣይ ጨዋታ ሲሳይ ደምሴ ቡና ከጊዮርጊስ ሲጫወት ሌላ ቢጫ በማየቱ እንዲያርፍ ተደረገ። ይህ ሲሆን ታዲያ ፌዴሬሽኑ ሲሳይ ማረፍ አለበት ብሎ ደብዳቤ አላከም። ነገር ግን በደንቡ መሰረት ቡና ራሱ ተከታትሎ ማሳረፍ ስለነበረበት እንዲያርፍ አድርጓታል፡፡ የምንያህል ጉዳይም መሆን የነበረበት እንዲህ ነው። ከፊፋ በላይ መረጃው ሊኖር የሚገባው ፌዴሬሽኑ ጋር በተለይም የአሰልጣኝ ቡድኑ ጋር ነው፡፡ ምንያህል በቦትስዋና ጨዋታ ተገቢ ተጨዋች እንዳልሆነ ለማወቅ የፊፋን ደብዳቤ መጠበቅ ባላስፈለገ ነበር። ይህ ሃላፊነት በዋናነት ደግሞ ሊሆን የሚገባው የዋና አሰልጣኙ ነው፡፡ በየትኛውም ክለብ ያለው አሰራር ይህ ነው፡፡ ዋናው አሰልጣኝ ይህን ሃላፊነት መዝግቦ እንዲይዝ የጨዋታ ቀን ለረዳት አሰልጣኙ ወይም ለቡድን መሪው ይሰጣል። ከጨዋታው በኋላም ያንን በመቀበል በራሱ ሰነድ ላይ ያሰፍራል ግልባጩንም ከሌሎች የጨዋታ ሪፖርቶች ጋር አያይዞ ለቴክኒክ ክፍሉ ወይም ለፅህፈት ቤቱ ያሳውቃል፡፡ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ውስጥ የነበረው አሰራር ግን ከእዚህ የተለየ ነው፡፡ ዋናው አሰልጣኝም ሆነ ረዳቱና የቡድን መሪው የጨዋታ ቀን ቢጫና ቀይን በተመለከተ ምንም አይነት መረጃ እንደማይዙና ይህ ብቻ አይደለም ስለ እያንዳንዱ ጨዋታና ተጨዋች በተመለከተ ለፌዴሬሽኑ ሪፖርት እንደማያቀርቡና በፌዴሬሽኑ በኩልም የመጠየቁ ባህል እንደሌለ ባደረግነው ማጣራት ለማረጋገጥ ችለናል፡፡

አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው የብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ከሆኑ ሁለት ዓመት የሞላቸው ቢሆንም ማን ምን ያህል ተጫወተ የሚሉና መሰል ጥያቄዎች ቢጠየቁ መረጃ በግለሰቦች እንጂ በፌዴሬሽኑ የለም፡፡ ለብሄራዊ ቡድኑ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ይወጣል ያ ሁሉ ብር የወጣበት ውድድርና መረጃ ግን በስርዓትና በተደራጀ መልኩ ተይዞ አይቀመጥም፡፡ የብሄራዊ ቡድኑ ሃላፊነት ሙሉ ለሙሉ ለአቶ ሰውነት ቢሰጥም በተመዘገበው ጥሩም ሆነ መጥፎ ውጤት ዙሪያ የፌዴሬሽኑ ሃላፊዎች ከአሰልጣኙ ጋር በየጊዜው ግምገማና ውይይት አያደርጉም፡፡ እንዲያውም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን የብሄራዊ ቡድኑን የአሰልጣኞች ቡድን እንቅስቃሴ በቅርብ የሚከታተለው ከፌዴሬሽኑ ይልቅ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ነው፡፡ የፌዴሬሽኑ ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ ሰኞ ዕለት ከቀኑ 10፡00ሠዓት እስከ ምሽት 2፡30 ሠዓት ድረስ በጉዳዩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ውይይትና ግምገማ አድርጓል፡፡ በዚህ ወቅትም የምንያህልን ቢጫ በተመለከተ ፊፋ ከላከው ውጪ በአሰልጣኝ ቡድኑ አባላት ወይም በፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት የተያዘ መረጃ እንዳለ ጠይቋል። ከማንም ምንም ሊቀርብ ግን አልቻለም፡፡ የፌዴሬሽኑ አመራሮች በቁጣ የአሰልጣኝ ቡድኑን አባላት እና ፅህፈት ቤቱን እንዴት የራሳችሁን መረጃ አትይዙም ሃላፊነቱስ የማን ነው ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ በዚሁ ወቅትም ይህ ሃላፊነት የአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው መሆኑ ተገልፆል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ከቅጥር ውላቸው ጋር ተያይዞ በተሰጣቸውና ሐምሌ 1/2004ዓ.ም ፈርመው በወሰዱት የስራ መዘርዝር ተራ ቁጥር 20 በኢንተርናሽናል ውድድር ወቅት ቢጫና ቀይ ካርድን በተመለከተ ተከታትሎ መዝግቦ የመያዝና የማስወሰን ሃላፊነት የእሳቸው መሆኑ ሰፍሯል። አሰልጣኝ ሰውነት ግን የስራ መዘርዝሩን እንዳላዩትና ሃላፊነቱም የእሳቸው ሊሆን እንደማይገባ ይዘው እንደማያውቁና ወደፊትም እንደማይዙ ተናግረዋል የፌዴሬሽኑ ሃላፊዎችም በአሰልጣኙ ንግግር ክፉኛ በመቆጣት አምርረው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የእኛን ተጨዋቾች ብቻ ሳይሆን የተጋጣሚ ተጨዋቾችን ቅጣት ሳይቀር ተከታትለህ ልትይዝ ይገባል በማለት ሁሉም አቋም ሲይዙ አቶ ሰውነት ጉዳዩን እንዳለሳለሱት ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በጉዳዩ ዙሪያ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንቶችና ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው አስተያየት እንዲሰጡን ተንቀሳቃሽ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ብንደውልም ምላሽ ልናገኝ አልቻልንም። ሰኞ ዕለት በተደረገው ውይይትና ግምገማ ቢጫና ቀይ ካርድን መዝግቦ የመያዙ ሃላፊነት ለማን እንደተሰጠና መሠረታዊ ችግሩ ምን እንደሆነ ቢታወቅም ይህ ግን በትናንቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ይፋ አልተደረገም፡፡ በማንም በኩል ይፋ እንዳይደረግና በምስጢር እንዲያዝም ትዕዛዝ እንደተሠጠ ከታማኝ ምንጮቻችን ለማወቅ ችለናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በተፈጠረው ስህተት ዙሪያ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ትናንት የፌዴሬሽኑን ከፍተኛ ሃላፊዎች ጠርቶ አነጋግሯል፡፡ የስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አብዲሳ ያደታ ትናንት ረፋድ ላይ የፌዴሬሽኑን ሃላፊዎች በፅህፈት ቤታቸው ረዥም ሰዓት በመውሰድ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያና መረጃ እንዲሰጡዋቸው ጠይቀዋል። ይሁን እንጂ ምን ውሳኔ እንዳሳለፉ ጥረት ብናደርግም ለማወቅ አልቻልንም።

Tuesday, June 18, 2013

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፊፋን ክስ አመነ




አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሰኔ 1 ቀን 2005 ዓ.ም ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡
ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ  አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ከፊፋ ደብዳቤ ደርሶት እንደነበርም ገልጿል፡፡
የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህ መሰረት የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ ፣ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ፣ ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ እና የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች ጥፋተኛ ተብለዋል።
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በጥፋተኞቹ ላይ በቅርቡ ተገቢውን ቅጣት በመውሰድ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የቡድኑ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ፥ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በጨዋታውም አሸንፈን ወደ አለም ዋንጫ እንደምንሳተፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል አሰልጣኙ፡፡
በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ እና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣትም ያስጥላል፡፡

Monday, May 20, 2013

ቅዳሜ ኢትዮጵያ ከ ሱዳን ጋር ለምታደርገው ጨዋታ የተጫዋቾች ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ
ግንቦት 12 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ አፍሪካ ህብረት የተመሰረተበትን 50 ኛ አመት  ክብረ በአል ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያ ከሱዳን በምታደርገው ጨዋታ ላይ የሚካፈሉ ተጫዋቾችን ስም ዝርዝር የኢትዮጵያ  ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ይፋ አደረጉ ፡፡
በዚህም መሰረት የተመረጡት ተጫዋቾች ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ደጉ ደበበ ፣አበባው ቡጣቆ፣ቢያድግልኝ ኤልያስ፣አሉላ ግርማ፣ሽመልስ በቀለ ፣አዳነ ግርማ ፣ያሬድ ዝናቡ፣ዮናታን ብርሀነና ተስፋዬ አለባቸው ናቸው ፡፡
ከ ደደቢት ሲሳይ ባንጫ ፣ ስዩም ተስፋዬ ፣ብርሃኑ ቦጋለ፣አይናለም ሃይሉ፣አክሊሉ አየነው ፣አዲስ ህንጻ፣በሃይሉ አሰፋ ፣ጌታነህ ከበደ ፣ምን ያህል ተሾመ ፣ዘነበ ከበደ(አዩካ) ና ዳዊት ፍቃዱ ሲሆኑ ፥
ከ ኢትዮጵያ ቡና ጀማል ጣሰው፣አስቻለው ግርማ ፣ፖክ ጅምስ እና ኤፍሬም አሻሞ፥
ከ መብራት ሃይል አስራት መገርሳ እና መስፍን ወንድሙ፥
ከ መከላከያ ጥላሁን ወልዴ ፥
ከ ኢትዮጵያ መድህን ሳለሃዲን ባርጌቾ፥
ከ ሀዋሳ ከነማ ወንድሜነህ ዘሪሁን፥
ከ ሰበታ ከነማ ደረጀ አለሙ እና ከ ሲዳማ ቡና ደግሞ ሞገስ ታደሰ  ሆነዋል ፡፡
ተጫዋቾቹ ከነገው ግንቦት 13 ማለዳ ጀምሮ በ ፌዴሬሽኑ ጽህፈት ቤት ተገኝተው ሪፖርት እንዲያደርጉም  አሰልጣኙ ጥሪያቸውን አስተላለፈዋል፡፡

Tuesday, April 16, 2013

Lelisa Desisa wins men's title

Ethiopia's Lelisa Desisa took the title in the 117th edition of the world's oldest marathon on Monday, winning a three-way sprint down Boylston Street to finish in 2 hours, 10 minutes, 22 seconds and snap a string of three consecutive Kenyan victories.
"Here we have a relative newcomer," said Ethiopia's Gebregziabher Gebremariam, who finished third. "Everything changes."
In just his second race at the 26.2-mile distance, Desisa finished 5 seconds ahead of Kenya's Micah Kogo to earn $150,000 and the traditional olive wreath. American Jason Hartmann finished fourth for the second year in a row.
"It was more of a tactical race, the Ethiopian versus the Kenyans. That fight played out very well," defending champion Wesley Korir, a Kenyan citizen and U.S. resident, said after finishing fifth.
"The Ethiopians run very good tactical races. One thing I always say is, 'Whenever you see more than five Ethiopians in a race, you ought to be very careful.' As Kenyans, we ought to go back to the drawing board and see if we can get our teamwork back."
Rita Jeptoo won the women's race earlier for her second Boston victory. Jeptoo, who also won in 2006, finished in 2:26:25 for her first win in a major race since taking two years off after having a baby.
Desisa, 23, was among a group of nine men -- all from Kenya or Ethiopia -- who broke away from the pack in the first half of the race. There were three remaining when they came out of Kenmore Square with a mile to go.
But Desisa quickly pulled away and widened his distance in the sprint to the tape. It's Desisa's second victory in as many marathons, having won in Dubai in January in 2:04:45.
He is the fourth Ethiopian to win the men's race and the first since his training partner, Deriba Merga, won in 2009. Desisa is the 24th East African to win in the past 26 years.
He is the fourth Ethiopian to win the men's race and the 24th East African to win in the past 26 years.
Lisa Larsen-Weidenbach, who won in 1985, is the last American champion; 1983 winner Greg Meyer was the last American man to break the tape.
A year after heat approaching 90 degrees sent record numbers of participants in search of medical help, temperatures in the high 40s greeted the field of 24,662 at the start in Hopkinton. It climbed to 54 degrees by the time the winners reached Copley Square in Boston.
Japan's Hiroyuki Yamamoto was the first winner of the day, cruising to victory in the men's wheelchair race by 39 seconds over nine-time champion Ernst Van Dyk of South Africa. Tatyana McFadden, a Russian orphan who attends the University of Illinois, won the women's race.
Race day got started with 26 seconds of silence in honor of the victims of the Sandy Hook Elementary School shooting.
The 53 wheelchair competitors left Hopkinton at 9:17 a.m., followed 15 minutes later by the 51 elite women. The men were under way at 10 a.m., followed by three waves that over the next 40 minutes would send the entire field of 27,000 on its way to Copley Square.
Last year's race came under the hottest sustained temperatures on record. About 2,300 runners took organizers up on the offer to sit that one out and run this year instead.

Wednesday, March 20, 2013

ሲሳይ ባንጫ በእሁዱ ጨዋታ አይሰለፍም

በ29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ጋር በነበራት 3ኛ የምድብ ጨዋታ ላይ የቀይ ካርድ የተመለከተው ሲሳይ ባንጫ ፥ በካፍ በመቀጣቱ ቡድኑ እሁድ ከቦትስዋና ጋር በሚኖረው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ አይሰለፍም።

በሌላ በኩል ቦትስዋና ማላዊን በሜዳዋ አስተናግዳ 1 ለ 0 በሆነ ውጤትያሸነፈች ሲሆን ፥ ቡድኑ ከኢትዮጵያ አቻው ጋር ላለበት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ነገ አዲስ አበባ ይገባል።
ኢትዮጵያዊው አጥቂ ሳላዲን ሰኢድም ከብሄራዊ  ቡድኑ በቀረበለት ጥሪ መሰረት  ዛሬ ቡድኑን የሚቀላቀል ይሆናል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከትናንት ወዲያ ጀምሮ ልምምድ መጀመሩ የሚታወስ ነው።

Monday, March 18, 2013

ቅዱስ ጊዮርጊስ የማሊውን ጆሊባ 2 ለ 0 አሸነፈ

ለአፍሪካ ሻምፕዮን  ሊግ ማጣሪያ ዛሬ አዲስ አበባ ስታዲየም ቅዱስ ጊዮርጊስና የማሊው ጆሊባ የተገናኙ ሲሆን ፥ ቅዱስ ጊዮርጊስ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል ።

ለቅዱስ ጊዮርጊስ ግቦቹን ያስቆጠሩት ከእረፍት በፊት ዮናታን ብርሃነና ከእረፍት በኋላ ፍፁም ገብረማርያም ናቸው ።
ቡድኖቹ ዛሬ ያካሄዱት ጨዋታ የመጀመሪያ ሲሆን ፥ የመልስ ጨዋታቸውን ከሁለት ሳምንት በኋላ በማሊ ያካሂዳሉ።
በሌላ ዜና ለአፍሪካ ኮን ፌዴሬሽን ዋንጫ ሱዳን ካርቱም ላይ ከአልሃሊ ሸንዲ ጋር የማጣሪያ ጨዋታ ያደረገው ደደቢት 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።
ሁለቱ ቡድኖች ከሁለት ሳምንት በኋላ አዲስ አበባ ላይ የመልስ ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ።

Friday, March 15, 2013

Ethiopia’s Dibaba pulls out of London Marathon


Ethiopia’s Olympic 10,000 metres champion Tirunesh Dibaba has withdrawn from next month’s London Marathon with a shin injury, organisers said on Thursday.

Dibaba had been set for her debut over the 42.195-km distance but an old lower leg problem has flared up during training for the race.

“I have been in training for the London Marathon, but the increase in mileage has caused a flare up of my previous lower leg injury,” she said in a statement.

“As a result, I won’t be able to compete in this year’s London Marathon but I look forward to making my marathon debut there next year.”

Dibaba had been aiming to become the first Ethiopian woman to win the London race since her cousin Derartu Tulu in 2001.

Ethiopia’s challenge in the women’s race will now be spearheaded by Olympic champion Tiki Gelana who is running the London Marathon for the first time.

“Of course, it is disappointing to lose Tirunesh. She has been such a fantastic athlete on the track, and everyone was full of anticipation to see how well she performed in a marathon,” race director Hugh Brasher said.

Dibaba is a three-time Olympic champion, having also won the 5,000 and 10,000 at the 2008 Beijing Games.

source:http://gulftoday.ae

Friday, March 8, 2013

አበበ ቢቂላ እና ጋቢው

አበበ በሮም ኦሎምፒክ በማሸነፉና የኢትዮጵያ ስም በማስጠራቱ ትልቅ ኩራት ሆነ ለቶኪዮ ኦሎምፒክ ዝግጅት ተጀምረ፡፡ አበበ በተለያየ ጊዜ ሩጫ ሲያካሄድ እያቋረጠ ይወጣ ጀመር፡፡ ችግር ሲገጥመው ለይድነቃቸው ያማክራል፣ የቡድኑ ሐኪም ዶክተር ፍሬደሪክና ይድነቃቸው በአበበ ጉዳይ ተወያዩና አስመረመሩት ትርፍ አንጀት አለበት፣ እንዲህ ሆኖ መሮጥ አይችልም አሉ፣ ኦፕራሲዮን መሆን አለበት፣ ሁለቱም ወሰኑ ለአበበም ነገሩት፣ ‹‹ እናንተ እንዳላችሁ›› አለ፡፡ ሆስፒታል አስተኙት ኦፕራሲዮን ተደረገ፡፤ጉዳዩ ሌላ ቦታ ተሰማ ጭቅጭቅ ተፈጠረ፡፡ ‹ይድነቃቸውና ፍሬደሪክ አበበን አስቀደዱት›› ተባለ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ኢትዮጵያ ወርቅ እንዳታመጣ በማሰብ ነው ተብሎ ተወገዙ፣ አበበ ግን ‹‹ከማንም በላይ እነሱ ለእኔና ለውጤቱ አስበው ነው›› አለ፡፡
 አበበ ገና ኦፖራሲዮኑ ሙሉ በሙሉ ሳይደርቅ ወደ ቶኪዮ ሄደ አበበ በሽተኛ ነውና ጋቢ ለብሶ መሄድ ነበረበት የጃፓን ሐኪሞቸም ህመሙንና ስፌቱን አዩ እንዲህ ሆነህ መንቀሳቀስ አትችለም አሉት፣ አበበ ግን ልዩ ፍጡር ነበር ሮም በባዶ እግሩ ሮጧላ፡፡ ቶኪዮ ላይ ደግሞ ከበሽታው ሙሉ ለሙሉ ሳያገግም ማራቶንን ሮጠ የጃፓን ጋዜጦች አበበ በሽተኛ መሆኑን ነው የሚያውቁት በመሮጡ ተገረሙ፣ በማሸነፉም ተደነቁ እውነትም ልዩ ፍጡር ነው አሉ፡፡ ለብሶት የሄደው ጋቢ አሁንም ድረስ እዚያው ጃፓን ይገኛል፣ ሰዎች ጋቢውን ይጎበኙታል ገንዘብ ከፍለው ይለብሱና ፎቶ ይነሳሉ አበበ ሮጦ እንዳሸነፈ ወደ ይድነቃቸው ሄደና ‹‹ ወሬኞችን ጭጭ አደረግናቸው›› አለ፡፡ ሮም ላይ ሲያሸንፍ ደግሞ ወደ ይድነቃቸው ጠጋ ብሎ ‹‹ አንጀቶን አላራስኩትም ?›› አላቸው ያን ጊዜ ምንም ለማያመጡ ለምን ሄዱ ተብሎ ከቤተ መንግሥት ወቀሳ ነበር፣ አበበም የመጀመሪያውን ወርቅ በማምጣቱ ይድነቃቸው ተደሰቱ አበበ የሮጠው መስከረም 1 ቀን ነው ይድነቃቸው የተወለዱት ደግሞ መስከረም 1 ቀን ነው፡፡ ይድነቃቸው ሻምፓኝ ይዘው መጡ፡፡ ‹‹ ለኔም ለአንተም›› አሉት መስከረም 1 ለሁለቱም ልዩ ቀን ነበር፡፡
 
Source:librogk.com

Tuesday, February 26, 2013

video-Meseret Defar sets personal best, event record in New Orleans Half Marathon -


“First I start and I saw my competitors were very good," she said. "And I wait until 10 kilometers. After that I feel good, my legs relax and I start to go."

She said although she didn't reach her goal of 1:06 or faster, she felt more prepared for the New Orleans course because she actually trained a little more. Her average pace Sunday was 5:09 per mile; Flanagan averaged 5:14.


Friday, November 9, 2012

Ethiopia 102th place in FIFA world rankings




 In the November World Fifa Rankings of 2012, Ethiopia are in 102 place, up sixteen   from last month . 2010 World Cup winners Spain remain firmly at the top of the rankings for yet another month. Followed by Germany, Argentina, Portugal, Italy then England down from their highest ever ranking of third to six, the Netherlands, Colombia, Russia and Croatia. Copa America winners Uruguay are 11th. Brazil are in 13th up from their lowest ever position of 14th.
Ethiopia  are in  28th position on African Team.Ivory Coast are the top African team in 15th.
Ethiopia Ranking History

Top 20 In FIFA Ranking
Top 20 on African Team

Ethiopia  are in  28th position on African Team



Ethiopia in 102th position