Search

Monday, May 11, 2015

አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ የሩጫ ውድድርን በይፋ አቆመ


ዛሬ በኢንግሊዝ በተካሄደው ታላቁ የማንቸስተር ሩጫ ላይ የተሳተፈው አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ በውድድሩ ማብቂያ ላይ የሩጫ ውድድር ማቆሙን ይፋ አደረገ።
ሀይሌ የዛሬውን ሩጫ ካጠናቀቀ በኋላ ለ25 ዓመታት የቆየበትን የሩጫ ውድድር ማቆሙን  ቢገልፅም፥ ሩጫን ግን አላቆምም ነው ያለው።
አትሌት ሀይሌ ከአምስት ዓመት በፊት የሩጫ ውድድርን ሊያቆም እንደሚችል ተናግሮ እንደነበር እናስታውሳለን።
የ42 ዓመቱ አትሌት ሀይሌ ሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ያገኘ ሲሆን፥ 25 ጊዜ የዓለም ክብረወሰኖችን በተለያዩ ርቀቶች ሰብሯል።
በአሁኑ ወቀትም የ20 ሺህ ሜትር ሩጫ ክብረ ወሰን ባለቤት ነው።
አትሌቱ በአሁኑ ወቅት በአገሩ በተለያዩ የኢንቨሰትመንት ዘርፎች ተሰማርቶ በመስራት ላይ ይገኛል።

What Your Heart Line Says About Your Love Life and Relationship With Others -



Do you know that you can find the line of the heart’s at your fingertips? The line of your heart is an important indicator of your feelings and everything that revolves around love

What Your Heart Line Says About Your Love Life and Relationship With Others
A) If your heart line begins below the middle finger you were born to be a leader – an ambitious, independent, intelligent person, and have expressed qualities of judgment and decision making. You are less sensitive and cold to others.

B) If your heart line begins between the middle finger and index finger then you areconsiderate and kind to others. In addition, you are also hesitant and cautious when others are concerned, but you are a person of trust. You have the common sense when deciding. 


C) If your heart line begins below the index finger have the same characteristics as the person to whom your heart line begins below the middle finger (A).

D) If your heart line begins between the index finger and thumb, you are full of patience, caring, well-intentioned and soft-hearted. These words best describe you.




Friday, May 8, 2015

ኢትዮጵያ ቡና ዳዊት እስጢፋኖስን በዲሲፕሊን ጉድለት ከክለቡ አሰናበተ


የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ዳዊት እስጢፋኖስን አሰናበተ።

ክለቡ ተጫዋቹ በተደጋጋሚ ባሳየው የዲሲፕሊን ጥሰት ምክንያት  ሊያሰናበተው እንደቻለም  ገልጿል።

ተጫዋቹ ምንም አይነት የጤና እክል ሳይገጥመው አሞኛል በሚል ሰበብ ለአንድ ሳምንት ከልምምድ መራቁ እና በህክምና ምርመራም ጤነኛ መሆኑ መረጋገጡን ክለቡ ከዲሲፕሊን ጥሰቶቹ መካከል ይጠቅሳል።

በተጨማሪም ተደራራቢ የዲሲፕሊን ጥሰቶችን ሲፈፅም መቆየቱን የጠቀሰው ክለቡ፥ ለተጫዋቹ የስንብት ደብዳቤ ሰጥቷል።

ከተጫዋቹ ጋር  ተይዞ የነበረውን ውልእና የውል አፈፃፀም  በተመለከተም ክለቡ እየመከረበት ይገኛል።

ዳዊት እስጢፋኖስ ክለቡ አሉኝ ከሚላቸው ተጫዋቾች እንደነበር  ይታወቃል።

በቶማስ ሰብስቤ
source ;FBC

ግብፅ ኢትዮጲያውያንን ከአስፈሪው የ ሊቢያ በረሀ አወጣች።

ለወሲብ ጠቃሚ እና የማይጠቅሙ የምግብ አይነቶች እጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነብርሃን በታዲያስ አዲስ

Wednesday, May 6, 2015

አስተዳደሩ ሰማያዊ ፓርቲ መስቀል አደባባይ ላይ ህዝባዊ ስብሰባ ማድረግ እንደማይችል ገለጸ

አስተዳደሩ ሰማያዊ ፓርቲ መስቀል አደባባይ ላይ ህዝባዊ ስብሰባ ማድረግ እንደማይችል ገለጸ
• ‹‹ተቀባይነት የሌለው ተልካሻ ምክንያት ነው›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 9/2007 ዓ.ም መስቀል አደባባይ ላይ ለማድረግ ያቀደውን ህዝባዊ ስብሰባ እውቅና እንደማይሰጠው ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ ገልጾአል፡፡ አስተዳደሩ በላከው ደብዳቤ ‹‹መስቀል አደባባይ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት ከመሆኑም በላይ በርካታ የተከማዋ ነዋሪ የሚተላለፍበት እና የከተማው ነዋሪ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥር›› ነው ሲል ለህዝባዊ ስብሰባው እውቅና እንደማይሰጥና ሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባውን መስቀል አደባባይ ማድረግ እንደማይችል ገልጾአል፡፡
በሌላ በኩል የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ አስተዳደሩ የሰጠው መልስ ‹‹ተቀባይነት የሌለው ተልካሻ ምክንያት ነው›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ኃላፊው አክሎም ‹‹አደባባዩ የተሰራው እንደዚህ አይነት ተግባራት ሊከናወኑበት ነው፡፡ ኢህአዴግ ሲጠራ ትራፊክ ተጨናነቀ ተብሎ አያውቅም፡፡ ሰማያዊ ሰልፍና ስብሰባ ሲጠራ ግን እንዲህ አይነት ተልካሻ ምክንያት ያቀርባሉ፡፡ በመሆኑም ይህን ተልካሻ ምክንያት ሰማያዊ ፓርቲ አይቀበለውም›› ብሏል፡፡
ከትራፊክ መጨናነቅ ባሻገር አስተዳደሩ ሰማያዊ ለሚያደርገው ህዝባዊ ስብሰባ የፀጥታ ኃይል ለመመደብ እንደሚቸገርም የገለጸ ሲሆን አቶ ዮናታን ተስፋዬ በበኩሉ ‹‹ለጥበቃ የለንም ያሉትን የፀጥታ ኃይል ንፁሃንን ለመደብደብ ሲያሰማሩ በተደጋጋሚ አይተናል፡፡ አሁንም የጥበቃ ኃይል የለንም የሚሉት ስብሰባውን ለማስተጓጎል ነው፡፡ ያኔ ግን ሰላማዊ ዜጎችን ለመደብደብ ይልኩታል፡፡ በመሆኑም የአስተዳደሩ ውሳኔ በምክንያት ያልተደገፈና ተቀባይነት የሌለው ነው›› ብሏል፡፡