Thursday, December 27, 2012

Marvelous Tower


Crescent Moon Tower in Dubai (project under construction)

JANO BAND



Music that transcends culture and time with a new Rock edge has a name: JANO. Jano formed in 2011 with the mission to transform traditional African music and to shape the future of rock ‘n roll. Born and raised in Ethiopia, the band’s ten members share a musical passion with them since early childhood days. In January 2012, JANO completed their first full LP titled, ERTALE, written in the Ethiopian language of Amharic. Their soulful music focuses on the topics of love, adventure, loss and the journeys we all take through life, played with the African rhythm of their youth as the backdrop to a new, vibrant rock sound. 


Rocking the music industry at home in Africa and abroad, JANO’s music has been heralded as “totally new” with “exceptional vocals and production quality.”

JANO is produced by the team who brought Ziggy Marley & the Melody Makers over 15 years of musical success, including five Grammy’s and American Music awards, lead by Addis Gessesse and now Rock the World Music.

All it takes is a listen to know that the future of rock is JANO.


Monday, December 24, 2012

ዚአሊያንስ ትራንስፖርት ሰርቪስ አክስዮን ማህበር አውቶቡስ አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው

ዚትራንስፖርት ዋጋው ኚታክሲ ዋጋ ያነሰ ነው ተብሏል
አሊያንስ ትራንስፖርት ሰርቪስ አክስዮን ማህበር በአዲስ አበባ ዹግል ዹኹተማ አውቶብስ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርና ሃያ አምስት አውቶቡሶቜን ባለፈው ሚቡዕ ወደ አገር ውስጥ እንዳስገባ ተገለፀ፡፡ እያንዳንዳ቞ው 2 ሚሊዮን ብር ገደማ ዚተገዙት አውቶቡሶቜ ባለፈው ታህሣሥ 10 ቀን 2005 ዓ.ም አዲስ አበባ ሲገቡ አቀባበል ተደርጐላቾዋል፡ ሙሉ በሙሉ በአውሮፓ ሞተር ዚተሰሩትና ቻይና ውስጥ ዚተገጣጠሙት አውቶቡሶቜ፤ 100 ሰው ዚመጫን አቅም እንዳላ቞ውና ደሹጃቾውን ዹጠበቁ እንደሆኑ አቶ አዲል አብደላ ዚአሊያንስ ትራንስፖርት ሰርቪስ አክስዮን ማህበር ዚዳይሬክተሮቜ ቊርድ ሰብሣቢ ለአዲስ አድማስ ተናግሹዋል፡፡ 
አውቶቡሶቹ ዚ቎ሌቪዥን ስክሪን ያላ቞ው፣ ዹመንገደኛውን ም቟ት ዚሚጠብቁና ለአገራቜን አዹር በሚስማማ መልኩ ዚተገጣጠሙ መሆናቾውንም አቶ አዲል ገልፀዋል ፡፡ ድርጅቱ በመጀመሪያው ዙር ሃያ አምስት አውቶቡሶቜን ወደ አገር ውስጥ ያስገባ ሲሆን በቀጣዮቹ አራትና አምስት ወራት ሌሎቜ ሃያ አምስት አውቶቡሶቜን ለማስገባት እንዳቀደ ተገልጿል፡፡
አውቶቡሶቹ ዚሚሰማሩበት መስመርና ዚትራንስፖርት ዋጋው በቀጣዩ ሣምንት ይፋ ዹሚደሹግ ሲሆን ዚአገልግሎት ክፍያው ዚህብሚተሰቡን ዹመክፈል አቅም ያገናዘበና ድርጅቱንም አትራፊ በሚያደርግ መልኩ እንደሚተመን ዚተናገሩት አቶ አዲል፤ ዋጋው ኹሃይገር ባስ ኹፍ ያለ፣ ኚታክሲ ያነሰ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡
አሊያንስ ትራንስፖርት ሰርቪስ አክስዮን ማህበር ኚአመት በፊት በአዲስ አበባ ኹተማ ውስጥ ዚሚታዚውን ዚትራንስፖርት ቜግር ዹመቅሹፍ አላማ አንግቩ ዹተቋቋመና ታዋቂ ባለሀብቶቜና አርቲስቶቜ ዚሚገኙበት አክሲዮን ማህበር ነው፡፡
በአዲስ አበባ በተለይ በስራ ሰዓት መግቢያና መውጪያ ላይ ኹፍተኛ ዚትራንስፖርት እጥሚት እንዳለ ዚሚታወቅ ሲሆን በዚህም ዚተነሳ ነዋሪዎቜ ኹፍተኛ እንግልት እዚደሚሰባ቞ው መሆኑ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

soldier

Soldier's Duties
·         A soldier must be loyal to his country
·         All soldiers have a moral and legal obligation or duty to obey the lawful orders of the officers and leaders appointed over them.
·         Soldiers have unique responsibilities based on rank, duty position and even geographical location. They must treat all people with respect and dignity. It is recognized that everyone has something to offer to the success of the unit.
·         Service is done without the thought of reward or recognition


በሩብ ዓመት ብቻ ኹ72ሺ በላይ ዜጐቜ ወደ አሚብ አገራት ተጉዘዋል

ኹ1ሺ በላይ ህገወጥ ኀጀንሲዎቜ አሉ ተባለ
ባለፈው ሩብ ዚበጀት ዓመት ኹ72 ሺ በላይ ዜጐቜ ወደ አሚብ አገራት እንደተጓዙ ተገለፀ፡፡ 72ሺ 438 ዜጐቜ ወደ ሳውዲ አሚቢያና ኩዌት ዚተላኩ ሲሆን ኚእነዚህ መካኚል 68ሺ 474 ዚሚሆኑት ሎቶቜ ሲሆኑ 3ሺ 964 ዚሚደርሱት ደግሞ ወንዶቜ መሆናቾውን ዚሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር አስታወቀ፡፡ በሚኒስትር መ/ቀቱ ዚህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሞለመ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ በመ/ቀቱ ተመዝግበውና ህጋዊ ፈቃድ ወስደው ዜጐቜን ወደተለያዩ ዚአሚብ አገራት ዚሚልኩ ህጋዊ ኀጀንሲዎቜ ቁጥር 300 ሲደርስ ኹ1ሺ በላይ በህገወጥ መንገድ ዜጐቜን ዚሚልኩ ደላሎቜ አሉ፡፡
መ/ቀቱ ኚተለያዩ ኀጀንሲዎቜ ዹጉዞ ፕሮሰሳ቞ውን አጠናቀው እና ባጅ ወስደው ዚመጡለትን ተጓዊቜ ተቀብሎ ዚሥራ ውላቾውን ዚማጜደቅና ስልጠና ዚመስጠት አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ታህሣስ 11 ቀን 2005 ዓ.ም በመ/ቀቱ በተደሹገ ድንገተኛ ፍተሻ ኚሃያ በላይ ዕድሜያ቞ው ኹ13 እስኚ 16 ዓመት ዹሆኑ ህፃናት ዹጉዞ ዝግጅታ቞ውን አጠናቀው ለስልጠናው ወደ ሚ/ር መ/ቀቱ መጥተው እንደተገኙ ተገልጿል፡፡
ህፃናቱ ዕድሜያ቞ው 26 ዓመትና ኚዚያ በላይ መሆናቾውን ዚሚያሚጋግጥ ፓስፖርት ይዘው መገኘታ቞ውን ዚጠቆሙት አቶ ግርማ፤ ሕፃናቱ በሰውነት አቋማቾውም ሆነ በስነልቡና቞ው ለሥራ ዝግጁ ዹሆኑ አለመሆናቾው በመሚጋገጡ ጉዟቾው እንዲሰሚዝ ተደርጐ ዚማጣራት ሥራ እዚተኚናወነ እንደሆነ ተናግሹዋል፡፡
ኀጀንሲዎቜ ኹሚ/ር መ/ቀቱ ፈቃድ በሚወስዱበት ወቅት ወደ ውጪ አገር ለሥራ ዚሚልኳ቞ው ዜጐቜ ዕድሜያ቞ው ኹ18 ዓመት በላይ መሆናቾውንና ጠያቂው አገር በሚፈልገው ዚዕድሜ መጠን ላይ ዚደሚሱ መሆናቾውን በማሚጋገጥ መላክ ይኖርባ቞ዋል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ኹህግና አዋጅ ውጪ ህፃናት ልጆቜን ወደማያውቁትና መብታ቞ውን ለማስኚበር ወደማይቜሉበት አገር ለሥራ መላክ ህገወጥ አሠራር መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ይህ ተግባር በዜጐቜ ህይወት መቀለድ በመሆኑ ሚ/ር መ/ቀቱ አጥብቆ እንደሚቃወመውም ተናግሹዋል፡፡
ህፃናቱን በመመልመል ለጉዞ ካዘጋጁአ቞ው ኀጀንሲዎቜ ጋር ግምገማ እያካሄዱ መሆኑንና ጉዳዩን በማጣራትም በቅርቡ እርምጃ እንደሚወሰድ፣ ቁጥጥሩም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ግርማ ተናግሹዋል፡፡
ዜጐቜን ወደተለያዩ አገራት ዚመላኩ ተግባር በኹፍተኛ መጠን እዚጚመሚ ሲሆን ባለፈው አመት ብቻ 198ሺ 667 ዜጐቜ ወደተለያዩ አገራት ለሥራ እንደተላኩ መሚጃዎቜ ይጠቁማሉ፡፡

Thursday, December 20, 2012

ዚትያትር መግቢያ ዋጋ ጭማሪ ውዝግብ

ዚትያትር ባለሙያዎ቞ ወደ አዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አዳራሜ ለስብሰባ ሲገቡ
*በ15 ብር ማሳዚት ለመንግሥት ትያትር ቀቶቜም ያንሳል - ዚቢሮው ሃላፊ
*ቢሮው ዹግል ኢንተርፕራይዞቜን ዋጋ ዹመተመን አግባብ ዹለውም - አርቲስት ገነት አጥላው
“ቁርጥ ያለ ምላሜ ስጡን፤ዋናው ማነቆ ያለው እናንተ ጋ ነው - አርቲስት ሜመልስ አበራ
በጐሚቀት ሀገራት እንኳን አርቲስቶቜ በግል አውቶሞቢላ቞ው ይጓጓዛሉ እንጂ ታክሲ አይጠቀሙም ዚሚሉት ዚአገራቜን ዚትያትር ባለሙያዎቜ፤እኛ ግን ስንሞት እንኳን ዚሬሳ ሳጥን መግዣ እዚ቞ገሚን በመዋጮ ነው ዹምንቀበሹው ሲሉ ያማርራሉ፡፡ ባለፈው ሰሞን ዚትያትር ቀት መግቢያ ዋጋ ላይ ዹ100 ፐርሰንት ጭማሪ አድርገው ኚትያትር ቀቶቹ ጋር በተፈጠሹው አለመግባባት ተግባራዊ ሳይሆን ዚቀሚባ቞ው ዹግል ዚትያትር ኢንተርፕራይዞቜ፤ኹዘጠኝ አመት በፊት በነበሹው ዚትያትር መግቢያ ዋጋ አሁን ማሳዚት ዹሚሞኹር አይደለም ባይ ናቾው፡፡ ኚኑሮ ውድነቱ በተጚማሪ ዚትያትር ፕሮዳክሜን ዋጋ፣ ዚማስታወቂያ እና ተያያዥ ወጪዎቜ ኚእጥፍ በላይ በመናራ቞ው ዋጋ ሳንጚምር መስራት አንቜልም ይላሉ፡፡ በነፃ ገበያ ውድድር መርህም ዚሕዝቡን ዹመክፈል አቅም ያገናዘበ ጭማሪ አድርገን 15 ብር በሰው ዹነበሹውን ዚትያትር መግቢያ 30 ብር አድርገናል ሲሉ በአዲስ አበባ አስተዳደር ስር ላሉት ሁለት ትያትር ቀቶቜ እና በፌደራል ባህልና ቱሪዝም ሚኒስ቎ር ለሚተዳደሚው ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ማሳወቃ቞ውን ይገልፃሉ፡፡ ዚመንግሥት አካላቱ ቜግሩን እንደሚጋሩ ቢያምኑም በዚህ መልኩ ዋጋ መጚመሩን አልተቀበሉትም፡፡ በዚህም ሳቢያ በተኚሰቱ አለመግባባቶቜ በግል ኢንተርፕራይዞቜ ዚሚታዩ ትያትሮቜ ተስተጓጉለዋል፡፡ ይህ ደግሞ ሁሉንም ወገን ዚሚጎዳ እንጂ ዹሚጠቅም እንዳልሆነ ባለፈው ማክሰኞ ዹግል ኢንተርፕራይዞቜ ኚመንግስት ሃላፊዎቜ ጋር ባደሚጉት ስብሰባ ኚስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ ዚትያትር ኢንተርፕራይዞቜን ቜግር እንደሚጋሩ ዚገለፁት ዚመንግስት ሃላፊዎቜ፤ ድንገተኛ ዹዋጋ ጭማሪውን ግን አልተቀበሉትም - “ዋጋ ለመጹመር ጊዜ ያስፈልጋል” በሚል፡፡
ዹማክሰኞውን ስብሰባ ዚመሩት ዚቢሮው ኃላፊ አቶ ገብሚፃድቅ ሐጐስ፤ “ዹዋጋ ጭማሪ ዚጠዚቃቜሁት ሥራቜሁን ቀጥላቜሁ ቢሆን ኖሮ ጥሩ ነበር፣ ቢሮው እናንተ ኚመጠዚቃቜሁ በፊትም ጥናት እያደሚገ ነው ዚትያትር መግቢያ ዋጋ ኹፊልም መግቢያ ዋጋ አንሷል፡፡ ኚሥራው አድካሚነት አንፃር ዋጋው ኹፊልም መግቢያ መብለጥ ነበሚበት፤ጥያቄአቜሁ ትክክለኛ ነው” ብለዋል፡፡
ዚትያትር መግቢያ ዋጋ 15 ብር ሲደሚግ በህዝብ ተቋማት ደመወዝ ተኹፍሏቾው ዚሚያዘጋጁ ዚትያትር ባለሙያዎቜን እንጂ ዹግል ዚትያትር ኢንተርፕራይዞቜን ታሳቢ ተደርጎ እንዳልሆነ ዚጠቆሙት ዚቢሮው ሃላፊ፤ በ15 ብር ማሳዚት ለመንግሥት ትያትር ቀቶቜም እንደሚያንስ ተናግሹዋል፡፡
ሆኖም ዹግል ኢንተርፕራይዞቜ በእንዲህ ያለው መልኩ ዋጋ መጚመራ቞ው ዚመንግሥት ትያትር ቀቶቜን አላማ እንደሚያንኮታኩት አቶ ገብሚፃድቅ ገልፀዋል፡፡ በዚሁ ስብሰባ ላይ ዚተገኙት ሌላው ዚቢሮው ኃላፊ ደግሞ ትያትሮቜ ኪሳራ ላይ ናቾው ዹሚለው እንደማያስኬድ ጠቁመው፤ ጭማሪ ማድሚግ ካስፈለገም ይሄን ማድሚግ ዚሚቜለው ዹኹተማ አስተዳደሩ ካቢኔ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
ትያትር ፕሮዲዩስ አድርጐ እንዳኚሰሚው ዹተናገሹው ጋዜጠኛና ዚማስታወቂያ ባለሙያ ሳምሶን ማሞ፤እዚህ ዋጋ አትጚምሩ እዚተባለ ዚኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን ዋጋ በመጹመር ለአንድ ዚ቎ሌቪዥን ማስታወቂያ አስር ሺህ ብር ማስኚፈሉ በአንድ ሀገር ሁለት ስርአት አለ ወይ ያሰኛል ብሏል፡፡ “ኚያንያኑ ሲሞቱ ዚሬሳ ሳጥን መግዣ እንኳን ዹላቾውም --- አርቲስቱ ኚማኪያቶ ዋጋ አንሷል” ያለው ሳምሶን፤ ኢህአዎግ ላለፉት ሃያ አመታት ለቜግሩ መፍትሄ ባለመስጠቱ ዚሕዝብ አደራ አልተወጣም ያሰኛል ሲል ወቅሷል፡፡
ቢሮው ዹግል ኢንተርፕራይዞቜን ዋጋ ዹመተመን አግባብ እንደሌለው ዚገለፀቜው አርቲስት ገነት አጥላው በበኩሏ፤ዚመንግሥት ትያትር ቀቶቜ እና ዹግል ትያትር ኢንተርፕራይዞቜ ዹዋጋ አሀድ (Cost component) እንዲሁም ዚአንድ ትያትር ኹሌላ ትያትር ዹዋጋ አሀድ አንድ አለመሆኑን ጠቅሳ፤ ብዙ ሰዎቜ ዚሚተውኑበትን ‘ሕንደኬ’ ትያትርንና አራት ወይም አምስት ሰዎቜ ዚሚተውኑበትን ሌላ ትያትር በአንድ ዹዋጋ ሚዛን ማዚት ይቻላል ወይ በማለት ጠይቃለቜ፡፡ አርቲስት አለማዹሁ ታደሰ ደግሞ ዚትያትር ባለሙያዎቜ ኚዩኒቚርሲቲ ተመርቀው ሲወጡ ምን ይስሩ ዹሚል ጥያቄ ካቀሚበ በኋላ “ሕዝብን ማገልገል ሌላውን ሕዝብ መበደል ነው እንዎ?” ሲል አስተያዚቱን በጥያቄ ገልጿል፡፡
ዚመንግሥትና ዹግል ትያትር ኢንተርፕራይዞቜ በእኩል መታዚት ዚለባ቞ውም ያለው አርቲስትና ጋዜጠኛ ቎ዎድሮስ ተክለአሹጋይ፤ ዹግል ኢንተርፕራይዞቜ ደግ አባት ስላላ቞ው ደመወዝ በነፃ ኹሚኹፈላቾው በርካታ ዚመንግሥት ትያትር ቀቶቜ ባለሙያዎቜ ጋር ሊነፃፀሩ አይገባም ብሏል፡፡ ትያትር በግል ፕሮዱዩስ ማድሚግ እንደማያዋጣም ሲገልፅ፤ ሙስናና መጓተት ባይኖር ኖሮ ዚትያትር ፅሁፎቜን ኹግል ትያትር ኢንተርፕራይዞቜ ይልቅ ለመንግሥት ትያትር ቀቶቜ መስጠት እንደሚመርጥ ተናግሯል፡፡
በፊልምና በትያትር አዘጋጅነቱ ዚሚታወቀው አርቲስት ቢኒያም ወርቁ፤በትያትር መኖር እንደማይቻል እንደውም እዳ ውስጥ እንደሚኚት ካብራራ በኋላ በአዲስ አበባ ትያትር ቀቶቜ ለግል ኢንተርፕራይዞቜ ዚሚሰጡት ቀናት ዚተመልካቜ ቁጥር አናሳ ዚሆኑባ቞ው እንደሆኑ ጠቁሟል፡፡
ዹሚቀርበው ትያትር ደሹጃውን ዹጠበቀ ነው ወይ ዹሚለውን ኹዋጋ ጋር ማንሳት ተገቢ ነው ያለው ዚኢትዮጵያ ትያትር ባለሙያዎቜ ማህበር ፕሬዚደንት አንጋፋው አርቲስት ደበሜ ተመስገን በበኩሉ፤በዚህ ስብሰባ ላይ ዚትያትር ቀቶቜ ዚሥራ ኃላፊዎቜ ቢገኙ ጥሩ ነበር፡፡
ለደራሲና አዘጋጅ ቁርጥ ክፍያ ኹፍሎ ትያትር ቀቱ በራሱ ዋጋ ማሳዚት ይቜላል ብሏል፡፡በመጚሚሻም ዚቢሮው ኃላፊ አቶ ገብሚፃድቅ ሀጐስ “መሰናክሎቹ ተጠንተው በጋራ ውይይት መፍትሄ እንፈልጋለን፣ ዚትያትር ዋጋውንም ጉዳይ ቢሆን ሰው ስጡንና በጋራ ይጠና” ያሉ ሲሆን ዹሃላፊውን መፍትሄ ተኚትሎ ዹተናገሹው አርቲስት ሜመልስ አበራ፤ “ቁርጥ ያለ ምላሜ ስጡን፤ዋናው ማነቆ ያለው እናንተ ጋ ነው፡፡ ትያትር ቀቶቜ ማቅሚብ ያልቻሉትን ነው ዹግል ኢንተርፕራይዞቜ እያቀሚቡ ያሉት፡፡ ትያትር ቆሟል፡፡ ገቢ ቆሟል፡፡ በዚህ እዚተጐዳ ያለው መንግሥትም ጭምር ነው” ብሏል፡፣
ኃላፊው በሰጡት ምላሜም “ለማቆም እንገደዳለን ማለታቜሁ ስህተት ነው፡፡ መፍትሄ እስኪገኝ በገባቜሁበት ውል ቀጥሉ፡፡ ቜግሩ ይሰማናል፤ ኚምትሰጡን ሰዎቜ ጋር በአጭር ጊዜ እንወስናለን” ቢሉም ጋዜጠኛ ሳምሶን ማሞ “አቶ ገብሚፃድቅ ኮሚ቎ ሳያስፈለገው ዛሬውኑ ብትወስን አርቲስቱ ዘለአለም ያመሰግንሃል” ሲል ተማፅኗል፡፡ አርቲስት ገነት አጥላውም “ይጠና ሲባል አጥኚው ማነው?” ብላ በመጠዹቅ “ዚሚያጠኑት ዚመንግሥት ሠራተኞቜ ናቾው፡፡ እኛ ጉሮሮ ላይ ተቁሟል፡፡ ዹዋጋ ጭማሪው አጥንተን ዚገባንበት ነው፤ ዚመንግሥት ገቢና ሕዝብ ኚትያትር ዚሚያገኘው ጥቅም ታጥቷል” ብላለቜ፡፡ ኚተመልካ቟ቜ መካኚል ትያትሮቜን ተመልክቶ ጋዜጊቜ ላይ በመፃፍ ዚሚታወቀው ዳዊት ንጉሡ ሚታ “ተመጣጣኝ ክፍያ ቢኖር ጥሩ ነው፡፡ ይህ ባለመሆኑም ወጪ ለመቀነስ በሚል ብቻ በትያትር ዚሚሳተፉ ሰዎቜን ቁጥር መቀነስ ዚትያትሮቜን ደሹጃ እያወሚደ ነው፡፡ ኚመግቢያ ዋጋ ጭማሪው በኋላ ይሄ ባይቀጥል ደስ ይለኛል” ያለ ሲሆን ሌላዋ አስተያዚት ሰጪ ብዙነሜ ወንድሙ “ዚትኬት ዋጋ ቢጚምር ጥሩ ነው፡፡ ዚጥበብ ዋጋ ወሹደ፡፡ ዹዋጋው መውሚድ አንዳንዎ ዚተመልካቜ ቁጥር ይቀንሳል፡፡ ጥሩ ትያትር እስካዚሁ ድሚስ ዋጋ ተጚምሮ ኚያንያን ቢጠቀሙ ደስ ይለኛል” ብላለቜ፡፡
በግል ኢንተርፕራይዞቜ ዚሚታዩ ትያትሮቜ በመቋሚጣ቞ው ሌሎቜ ተመልካ቟ቜ ማግኘት አልቻልንም፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር እዚታዩ ካሉ ስምንት ትያትሮቜ አራቱ፣ በሐገር ፍቅር ትያትር እዚተዩ ካሉት ሰባት ትያትሮቜ ሊስቱ በአዲስ አበባ ማዘጋጀ ቀት ትያትርና ባህል አዳራሜ ኚሚታዩት ሰባት ትያትሮቜ ስድስቱ በግል ዚትያትር ኢንተርፕራይዞቜ ዚቀሚቡ ናቾው፡፡
ዚትያትር ባለሙያዎቹና ዚቢሮው ሃላፊዎቜ ዹማክሰኞ ውይይት ባለመግባባት ኹተቋጹ በኋላ “መብታቜን ሆኖ ለምንድነው ዚምንጠብቀው?” ያሉት አርቲስቶቜ ውይይቱን ለብቻ቞ው እንደቀጠሉ ለማወቅ ተቜሏል፡፡

Wednesday, December 19, 2012

ተቀናቃኞቹ እስራኀልና ኢራን በኀርትራ ወታደራዊ ካምፖቜ መሥርተዋል›› ስትራትፎር ግሎባል ኢንተለጀንስ

ጋዜጣው ሪፖርተር

ለሚዥም ጊዜ ዹቆዹና ሥር ዹሰደደ ዚፖለቲካ ፍጥጫ ውስጥ ዚሚገኙት እስራኀልና ኢራን ዹቀይ ባህር አካባቢን ለመቆጣጠር ዚሚያደርጉት ፉክክር ማዹሉን፣ ለዚህ ፍላጐታ቞ውም በኀርትራ ወታደራዊ ካምፖቜን ማቋቋማቾውን መቀመጫውን በአሜሪካ ያደሚገው ወታደራዊ ዚስለላ ድርጅት ስትራትፎር ግሎባል ኢንተለጀንስ ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት ገለጾ፡፡ ዚስለላ ተቋሙ ዲፕሎማት ምንጮቜን በመጥቀስ እንደገለጞው፣ እስራኀል ወታደራዊ ካምፕዋን በኀርትራ ግዛት በዳህላክ፣ በምፅዋና በአምባ ሳወራ አካባቢዎቜ መሥርታለቜ፡፡

እስራኀል በኀርትራ መሬት ላይ ወታደራዊ ካምፖቿን ዚመሠሚተቜው በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ማንኛውንም ዓይነት ወታደራዊ እንቅስቃሎ ለመሰለል፣ በተለይም ደግሞ በአካባቢው ዚኢራንን እንቅስቃሎ ለመኚታተል አቅዳ ነው ሲል ሪፖርቱ ይተነትናል፡፡

ኀርትራ ኚእስራኀል በተጚማሪ ዚኢራን ወታደራዊ ካምፖቜን ማስጠለሏን ዹሚጠቅሰው ዚስትራትፎር ሪፖርት፣ ዚእስራኀል በዚህ አካባቢ መገኘትም ኢራን በቀይ ባህርና አካባቢው ዚምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሎ በመብለጥ በአካባቢው ተፅዕኖ መፍጠር ዚሚቜል ዹጩር ኃይል መገንባት መሆኑን ያስሚዳል፡፡

ሮኬቶቜንና ዚተለያዩ ኚባድ ዹጩር መሣሪያዎቜን ዚጫኑ መርኚቊቜ በቀይ ባህር አድርገው ወደ ሱዳን ኚዚያም ወደ ግብፅ እንደሚጓዙ፣ በመቀጠልም በዚብስ ወደጋዛ እንደሚያመሩ ሪፖርቱ ይጠቅሳል፡፡

ኢራን ወታደራዊ ካምፕዋን በኀርትራ ግዛት ውስጥ መመሥሚቷም ባብ ኀል መንዳብ ዚተባለውን ዹቀይ ባህር ስትራ቎ጂካዊ ቊታና ወደ ስዊዝ ካናል ዚሚወስደውን ዹውኃ መስመር ለመቆጣጠር ዋነኛው ወታደራዊ ፍላጐቷ መሆኑን ይገልጻል ይላል ሪፖርቱ፡፡

ኀርትራም ለሁለቱ ተቀናቃኝ አገሮቜ ግዛቷን በመፍቀድ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ጥቅም እንደምታገኝ ዚስትራፎር ትንተና ያስሚዳል፡፡

በተለይም ኹፍተኛ ዹሆነ ዚገንዘብ ድጋፍና ዹጩር መሣሪያዎቜን እንዲሁም ኚኢትዮጵያ በኩል ሊሰነዘርባት ኚሚቜል ወታደራዊ ጥቃት ራሷን ለመኹላኹል ይሚዳት ዘንድ ዹአዹር ኃይሏን አቅም ለማጐልበት ዚእስራኀልን ድጋፍ በተለዋጭነት ልትጠይቅ እንደምትቜል ሪፖርቱ ያስሚዳል፡፡

በተጚማሪም በእስራኀልና በአሜሪካ መካኚል ያለውን ወዳጅነት በመጠቀም ኚአሜሪካ ጋር ያላትን ዹተበላሾ ፖለቲካዊ ግንኙነት ማደስ ሌላኛው ዚኀርትራ ፍላጐት ሊሆን እንደሚቜል ሪፖርቱ ይገልጻል፡፡

እስራኀል በተለያዩ ጊዜያት ዚሱዳን ወታደራዊ ተሜኚርካሪዎቜን ኹአዹር መምታቷን፣ ኚወራት በፊት ደግሞ በካርቱም አቅራቢያ ዹሚገኘውን ዮርሙክ ዚተባለ ዹጩር መሣሪያ ማምሚቻን ኚግዛቷ ባስወነጚፈቜው ሮኬት ማውደሟን ዚሚገልጹ ዘገባዎቜ መውጣታ቞ው ይታወሳል፡፡

Tuesday, December 18, 2012

ታንዛንያ ኚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ለመግዛት ጥያቄ አቀሚበቜ

Tanzania Request to buy electric power from Ethiopian Electric Power Corporation

ዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ 4.45 ቢሊዮን ብር ብድር ፈቀደ
በውድነህ ዘነበ

ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ታንዛኒያ ኚኢትዮጵያ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ጥያቄ ቀሚበቜ፡፡ ዚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሜን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ምሕሚት ደበበ መንግሥት ዚታንዛንያን ጥያቄ ተቀብሎ ዚሜያጭ ስምምነት ላይ ለመድሚስ ድርድር ይጀምራል ብለዋል፡፡

ታንዛንያ ኚኢትዮጵያ ኃይል ዚምታገኘው ኢትዮጵያና ኬኒያ በጋራ እዚዘሚጉት ካለው 433 ኪሎ ሜትር ኹፍተኛ ዹኃይል ተሞካሚ መስመር ነው፡፡ ኢትዮጵያ ኚታንዛንያ ጋር ዚምትደርስበት ዹኃይል ሜያጭ ስምምነት በራስ ፍላጎት ዹሚኹናወን ሲሆን፣ ዚኀሌክትሪክ መስመሩ በኬንያ ዚሚያልፍ በመሆኑ ግን ኬኒያ ዹተወሰነ ክፍያ ይኖራታል ሲሉ አቶ ምሕሚት ገልጾዋል፡፡

ባለፉት ዓመታት በወሚቀት ላይ ገዝፎ ዹቆዹው ዚምሥራቅ አፍሪካ ኀሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክት ዕውን ወደ መሆን ቀርቧል፡፡ ኢትዮጵያን ኚኬኒያ ዚሚያገናኘውን ዹኃይል መስመር መገንባት ዚሚያስቜለው ፕሮጀክት በርካታ ዚፋይናንስ ተቋማትን እዚሳበ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ኚኬኒያ ጋር ዚሚያገናኛትን ዚኀሌክትሪክ መስመር ለመዘርጋት ኹዓለም ባንክ 243 ሚሊዮን ዶላር (4.45 ቢሊዮን ብር) ብድር አግኝታለቜ፡፡ ይህንን ዚብድር ስምምነት ባለፈው ዓርብ ታህሳስ 5 ቀን 2005 ዓ.ም. ዚገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፊያን አህመድና ዹዓለም ባንክ ዚኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሚስተር ዧንግ ዚ ቌን ተፈራርመዋል፡፡

ዚኀሌክትሪክ መስመር ግንባታው ኚደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ሶዶ ኹተማ ተነስቶ ኬኒያ ድሚስ ዹሚዘሹጋ ነው፡፡ ኬኒያ ዚምሥራቅ አፍሪካ ኀሌክትሪክ መሚብ አካል በመሆኗ፣ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያን ኚምሥራቅ አፍሪካ እስኚ ደቡብ አፍሪካ ኹሚገኙ አገሮቜ ጋር ያገናኛታል፡፡

ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያን ኚኬኒያ ያገናኛል ይባል እንጂ በሁለቱ አገሮቜ ብቻ ዹሚወሰን አይደለም ዚሚሉት አቶ ምሕሚት፣ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ ዚምሥራቅና ዚደቡብ አፍሪካ አገሮቜን ያገናኛል፡፡ ዚምሥራቅና ዹሰሜን አፍሪካ አገሮቜን በኹፍተኛ ዚኀሌክትሪክ መስመርም ያገናኛል፡፡

ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ኚጎሚቀት አገሮቜ ጋር ያላትን ዚመደራደር አቅም እንደሚያሳድግ አቶ ምሕሚት ገልጾዋል፡፡ ምክንያቱም ኚአምስት ሳምንት በፊት ኢትዮጵያ ነዳጅ ለምታቀርብላት ጎሚቀት ሱዳን አንቶ መቶ ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ኃይል መላክ ጀምራለቜ፡፡ ይህ ዚሙኚራ ጊዜ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ ሁለት መቶ ሜጋ ዋት ኀሌክትሪክ ለሱዳን ዚምታቀርብ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ኚጥር ወር በኋላ በሁለቱ አገሮቜ ኹፍተኛ ባለሥልጣናት ይመሹቃል፡፡

ኢትዮጵያ ዚኬኒያ ዹጠሹፍ ኹተማ ለሆነቜው ሞያሌ መጠነኛ ዚኀሌክትሪክ ኃይል መስጠት ዚጀመሚቜ ሲሆን፣ በቅርቡ ዹሚጀመሹው ዚኀሌክትሪክ መስመር ሲጠናቀቅ 400 ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ለኬኒያ ትልካለቜ፡፡ ወደ ኬኒያ ዹሚዘሹጋው ዚኀሌክትሪክ መስመር ግን እስኚ ሁለት ሺሕ ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ኃይል ዹመሾኹም አቅም ያለው መሆኑን ለማወቅ ተቜሏል፡፡

ኢትዮጵያ ለጎሚቀት ጂቡቲም 50 ሜጋ ዋት ዚኀሌክትሪክ ኃይል እዚላኚቜ ነው፡፡ ኹፍተኛ መጠን ኀሌክትሪክ ለጎሚቀት አገሮቜ መላክ መጀመሯ ኚአገሮቹ ጋር ያላትን ዚመደራደር አቅም እንደሚያሳድገው አቶ ምሕሚት ገልጾዋል፡፡

ዚኢትዮጵያና ዚኬኒያ ዚኀሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ወጪ 1.3 ቢሊዮን ዶላር ዹሚፈጅ ሲሆን፣ ለኬኒያ ዹዓለም ባንክ፣ ዚአፍሪካ ልማት ባንክና ዚተለያዩ ዚፋይናንስ ተቋማት ብድር ሰጥተዋል፡፡

ምንጭ: ሪፖርተር

Monday, December 17, 2012

Nature of Plants



The Nature of Plants tells how plants adapt to the challenges of their habitats. Plants may live in places that provide too little rainfall, yet they thrive, either by evading drought, like the animals that live in deserts, or by tolerating the scarcity. There are plants that use other plants, climbing on them, strangling some, living in their leafy canopies, or parasitizing them. And The Nature of Plants explores the love-hate relationships that plants have with animals, some feeding on plants but others drawn into serving plants by pollinating them, scattering their fruits and seeds, or being eaten themselves.

Giant Tea pot Topiary